The Christian News
5.32K subscribers
3.06K photos
27 videos
720 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#አዲስ #ዜና

ዩጋንዳ እና ጋናን በመከተል ደቡብ አፍሪካዊቷ ናሚብያ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን ህገ ወጥ ልታደርግ ነው።

#አዲሱ #ህግ ተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪነትን ህገወጥ የሚያደርግና ጋብቻንም በህግ የሚያስቀጣ ያደርገዋል።

በላይኛው ፓርላማ ያለምንም ተቃውሞ ተቀባይነት ያገኘው ህጉ ከታችኛው #ፓርላማ ተቀባይነት ካገኘና የሃገሬው #ፕሬዝደንት #ወደ ተግባር ካሳለፉት ሰሞኑን ህግ ሆኖ ሲጸድቅ ከአፍሪካ ሃገራት #ብቻ ሶስተኛው ነው።

ህጉ በተጨማሪ #ጋብቻ በአንድ ወንድና በአንድ #ሴት መካከል ብቻ የሚኖር ህብረት ነው ብሎ ይደነግጋል። በውጪ ሃገራት እንኳን ተመሳሳይ ጾታ ትዳርን ይዞ ወደ ሃገር #ውስጥ መግባት ድርጊቱን በሃገረ ናሚቢያ ህገወጥ ያደርገዋል።

ምንም እንኳን ከቅርብ #ጊዜ ወዲህ በዚሁ ጉዳይ ላይ ተደጋጋሚ አክቲቪስቶች ወደ ፍርድ #ቤት ቢሄዱም #ምንም ለውጥ ሳይመጣ ቀርቷል።
#አዲስ #ዜና

የካናዳ ፍርድ #ቤት አብያተ ክርስቲያናት ላይ የኮቪድ ወቅት እግድን ይግባኝ ውድቅ አደረገ።

#ፍርድ ቤቱ የካናዳ #ሁለት ግዛቶች #ውስጥ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የኮቪድ 19 ወረርሺኝ በበረታበት ወቅት በአካል መሰብሰብን አግዶ በነበረበት ወቅት በመሰብሰባቸው ምክንያት ነው ጉዳዩን አልመለከተውም ያለው።

በወቅቱ አብያተ ክርስቲያናቱ በካናዳ #መንግስት የተወሰነውን በአካል ተገናኝቶ የማምለክ እገዳን ተላልፈው ሲሰበሰቡ ነበር ተብሏል።

ዘ ቸርች ኦፍ ጋድስ የተሰኘችው ቤተ ክርስቲያኗ ይሄንንም በመተላልፏ 240ሺህ ዶላር ቅጣት በግዛቷ ፍርድ ቤት ተጥሎባታል።

በኦንታሪዮ የምትገኘው የቸርች ኦፍ ጋድ መሪዎች በበኩላቸው ይሄ የፍርድ ቤት ውሳኔ የእምነት ነጻነትን የሚጋፋ ነው ብለውታል።
በሃገሪቱ የፍትህና ነጻነት ታሪክም አሳዛኝ #ቀን ነው ብለውታል።

ሬስቶራንቶችና ስፖርት ቤቶች፣ መክፈት በተፈቀደበት #ጊዜ #ቤተክርስቲያን እንዲዘጋና አቤቱታን አላስተናግድም ማለታቸው የእምነትን ነጻነት የሚጋፋ ነው ብለውታል።

እኛ ሰውን ሰምተን ሳይሆን #እግዚአብሔርን ነው የምንታዘዘው በማለት በወቅቱ በሮቻቸውን ሳይዘጉ የአምልኮ መርሃ ግብሮቻቸውን ሲያካሂዱ እንደነበረ ገልጸዋል።
#ፍትህ ግን ምንድነው? 🤔 የትስ #ነው ያለው? 🤔
#እኛ ጥያቄያችን #አንድ እና ግልጽ  ነው።

#የቤተክርስቲያናችን_ንብረት_ይመለስልን!!! 🙏🙏🙏

37 ዓመታት በእንባ እና በጸሎት የጸሎት ቤቷን ለማስመለስ ፍትሕን ፍለጋ የተነከራተተችው #ቤተክርስቲያን ዛሬም ፍትህን ፍለጋ ላይ ነች።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከ1950ዎቹ #መጀመሪያ ጀምሮ በተለይ ትምህርትን ከማስፋፋት አንጻር #ለሀገር እና #ለሕዝብ ጥቅም ላበረከተችው አስተዋጽዖ በወቅቱ የነበረው የመንግስት ስረዓት ከምስጋና ይልቅ ት/ቤቶቻችንና ጸሎት ቤቶቻችንን መውረስ ቀሏቸዋል።

በደርግ #መንግስት በግፍ የተወረሰው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የኦሎምፒያው ጸሎት ቤታችን በአዲስ አበባ የመጀመሪያው የመሰረተ ክርስቶስ የማምለኪያ ስፍራ ነው።

#ይህ የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ንብረት #ማለት የሙሉ #ወንጌል ምዕመን እና የሙሉ ወንጌል ቤ/ክ ንብረት ማለት ነው። የመካነ ኢየሱስ ማለት ደግሞ የቃለ ሕይወት ነው። የቃለ ሕይወት ማለት የሕይወት ብረሃን የሕይወት ብረሃን ማለት የገነት የገነት ማለት የጉባኤ እግዚአብሔር ... በአጠቃላይ የወንጌል አማኞች #በሙሉ ነው።

ይህ ከ66 ዓመት በላይ የተሻገረው የጸሎት ስፍራ ንብረት ብቻ አይደለም ይልቁንም ለወንጌል የተሰደዱ ፤ ለወንጌል ዋጋ የከፈሉ የወንጌላውያን አማኞች #ታሪክ እና ቅርስም ጭምር ነው።

በ1943ዓ.ም የተመሰረተችው የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከቀደምት የወንጌል አማኞች ቤተዕምነት መካከል አንዷ ብቻ ሳትሆን እውነተኛው የክርስቶስ ወንጌል ለአዲሱ #ትውልድ  እንዲሸጋገር ከ70 ዓመት በላይ #በኢትዮጵያ በሚመችም በማይመችም ሁኔታ #ውስጥ ስትሰራ ቆይታለች።

#ዛሬ ላይ መዲናችን #አዲስ አበባ ከሌሎች #አለም ላይ ከሚገኙ ከተሞች መካከል ለመወዳደር ሌት ተቀን እየተጋች ትገኛለች። በዚህ ውስጥ ታዲያ በከፊሉ አዳዲስ ሲገነባ በከፊሉ ለተቸገሩት ሲደረስ በሌላ አቅጣጫ ግን እንሳኩን ያልተመለሱ #ብዙ ጥያቄዎች እንዳሉ የአደባባይ ሚስጥር ነው።

ታዲያ በመዲናችን #ዛሬም ፍትህን ከሚጠይቁ ተቋማት መካከል አንጋፋዋ የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አንዷ ነች።

ስለዚህ ህጋዊ የሆነው የቤተክርስቲያን ታሪክ ፤ ቅርስ እና ንብረታችን የሆነው የጸሎት ቤቶቻችን ይመለሱልን የማያቋርጥ ጥያቄያችን ነው!!!

ይህ #መልዕክት የሚደረሳችሁ ምዕመናን እና ኢትዮጵያውያን በሙሉ የቤተክርስቲያናችን ንብረት እስኪመለስ ድረስ ሁላችንም #SharePost በማድረግ ለሁሉም እናድርስ!!!

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በዚህ ዙሪያ ተጨማሪ ዘገባዎችን በተለያየ ጊዜ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።

#share #share #share #share
#እይታ
#Opinion

የሰሞኑን #አንድ #ሁለት ዜናዎች ልንገራችሁ።

የቄስ ጉዲና ቱምሳ ባለቤት ጸሃይ ቶሎሳ ግለ #ታሪክ ተመርቋል። መጽሃፉ “በእቶን እሳት ውስጥ” የሚል ነው። የነዚህ ብርቱ እናት ታሪክ እና ምስክርነት ለአንድ አንድ ሰዎች የእምነት መልህቅ ሊሆን ይችላል፣ ቢባል ማጋነን አይሆንም።

ሌላው #ዜና ደግሞ በፌደራል መንግስትና #መንግስት ሸኔ በሚለው እራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ በሚጠራው ቡድን መካከል የተደረገው የሰላም ድርድር አሁንም ሳይሳካ ቀርቷል።

ይሄንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ሬድዋን ሁሴን አረጋግጠዋል። ከዚህ የሰላም ድርድር #መልካም ውጤት ይገኛል በሚል፣ ክርስቲያኑ ምነኛ ጓጉቶ እንደነበረ ማሰብ አይከብድም።

በተመሳሳይ ክፍለ ዘመን #ውስጥ ፣ በተመሳሳይ ርዕሳቸው፣ ረግጦ በሚገዛ መንግስት፣ የወንጌልን ነጻ አውጪነት አውጀው፣ የተገደሉ የዘመናት ክስተቶች ላውራችሁ።

#ቄስ_ዴትሪች_ቦንሆፈር በ1906 በጀርመን ብሬስሎው በተባለ ስፍራ የተወለዱ #ሰው ናቸው። እኚህ ሰው ስነ መለኮት አጥኚ ወይም ቲዎሎጂያን፣ ኮንፌሲንግ በተባለች ሉተራዊ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቄስ #እና ጸረ ናዚ ሰው ነበሩ።

የአዶልፍ ሂትለር ተቃዋሚ መሆን የዋዛ ነገር አይምሰላችሁ። ከናዚው አዶልፍ ሂትለር የአስተዳደር እቅዶች መካከል “ኢውታናዢያ” የሚባል ፕሮግራም ነበረ ይባላል። በዚህ ፕሮግራማቸው ሰው ከሚሰቃይ ቀድሞ መሸኘት የሚል ነው።

#ትንሽ የታመመ የመዳን ተስፋ ሳይሆን፣ ከህመሙ ማረፊያ መግደል ያሰበ “በጣም ቅን ሰው ናቸው” ነበረ። ይሁዲዎች #ላይ ያደረገውን ጭካኔ፣ አለም ያወቀው ነው። ቦንሆፈር ይሄንን ስርዓት ነበረ በአደባባይ ቆሞ የተቃወመው። ያው በእሳት ፊት ቆሞ ነበረና እሳቱ በላው። በተወለደ በ39ኛ አመቱ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌልን ሰብኮ ተሰቅሎ ተገደለ።

#ቄስ_ጉዲና_ቱምሳ በ1929 በኢትዮጵያ ወለጋ ቦጂ ከተማ የተወለዱ ሰው ናቸው። ተስፋ አደርጋለው ስለ ቄስ ጉዲና የማያውቅ ወንጌላዊ ክርስቲያን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ማለት ይከብዳል። ግን ዝም ብዬ ታሪኩን ልንገራችሁ።

እኚህ ቄስ የስነ መለኮት አጥኚ #ወይም ቲዎሎጂያን፣ #የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በተባለች ሉተራዊ ቤ/ክ ውስጥ ቄስ እና በሃያሉ ደርግ መንግስት ፊት የቆሙ ሰው ነበሩ። የደርግ ተቃዋሚ መሆንም የዋዛ ነገር አይደለም።

ኮለኔል መንግስቱ ማለት፣ በርሳቸው ዘመን በለጋ እድሜው አፈር የገባ ወጣት፣ በቀይ ሽብር ስም ያለቀው ተቀናቃኝ ፖለቲከኛና ለገዛ አጋሮቻቸው ያልተመለሱ ባለ ደም እጅ ሰው ነበሩ። ያ ኮለኔል መንግስቱና አገዛዙም ነበር ሆኗል።

እግዜር ደጉ፣ የማያሳልፈው የለም። ቄሱ ጉዲና በዚህ ለአፍሪካ እንኳን አይመለስም በተባለ ወታደር ፊት ቆመው “ወንጌል ነጻ ያወጣል” ብለው ሰብከዋል። እሳቸውም እሳት ፊት ቆመዋልና እሳት በላቸው። በተወለዱ በ50 አመታቸው የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ሰብከው በደርግ ወታደሮች ተገደሉ።

የነዚህ ሁለት በእሳት ፊት የቆሙ ቀሳውስት ህይወት፣ በሄሮድስ ፊት ቆሞ እውነት ተናግሮ አንገቱ የተቀላውን መጥምቁ ዮሃንስን ህይወት ይመስላል። የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት፣ በአስፈሪው የሮማ መንግስት ፊት፣ በአይሁድ ካህናት ፊት፣ በፈሪሳዊያንና ግሪካዊያን ፊት “እናንተ የእፉኝት ልጆች እያሉ”፣ መኖር ሳያሳሳቸው፣ መሞት ሳያስፈራቸው ወንጌልን የሰበኩ ጀግኖች ናቸው።

ቄስ ቦንሆፈርና ቄስ ጉዲናም በአፈ ሙዝ እንጂ በአፉ በማያወራ መንግስት ፊት ቆመው፣ መኖር ሳያጓጓቸው፣ ሞት ሳያስፈራቸው ወንጌልን ሳይቀንሱና ሳይጨምሩበት የሰበኩ የቤተ ክርስቲያን ቅሬታዎች፣ የክርስቶስ ልጆች ናቸው።

ዛሬስ መምህሩ፣ ጳጳሱ፣ ቄሱ፣ ፓስተሩ፣ ነብዩ፣ ሐዋርያው፣ ሼፐርዱ፣ ዳዲው የቱ ጋር ቆመሃል? ጌታ ኢየሱስ በጎቼን ጠብቅ ያለው ስመኦን ጴጥሮስ፣ ከአለም 20በመቶ ህዝብን በሚገዛው ግዙፉ የሮማ መንግስት ተዘቅዝቆ ተሰቀለ።

አንተስ በጎቼን ጠብቅ የተባልከው እረኛ ሆይ ፣ ለበጎቹ ስትል፣ እንደ ስመኦን ጴጥሮስ ተዘቅዝቀህ ለመሰቀል፣ እንደ ቦንሆፈር በናዚ ለመሰቀል፣ እንደ ጉዲና በደርግ ወታደር የአሞራ ሲሳይ ለመሆን #ተዘጋጅተሃል?

ክርስቲያን ሆኖ መኖር እራሱ ዋጋ በሚያስከፍልበት በዚህች ምድር ላይ ለወንጌል ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጀህ ነህ ወይስ፣ ለአገልግሎትና ለእረፍት በV8 እና FORD F150 የምትምነሸነሽ #ሆነሃል? አለም ህይወት የሆነውን ክርስቶስን ለመስቀል ካልራራች፣ አንተ እውነተኛውን የርሱን ህይወት የምትሰብከውን የምትምርህ #ይመስልሃልን?

ዙሪያ ገባህን አይተህ ወንጌል የሚሰበክ ከጠፋ፣ ከተኩላ የምትጠብቀው በግ ከሌለ፣ ምናልባት ወንጌሉ የሚያስፈልገው፣ እረኝነቱ የሚያስፈልገው፣ ላንተው እራስህ እንዳይሆን የቆምክበትን አስተውል?
#መንግሥት በአብያተ ክርስቲያናት ላይ የሚያደርገውን ግፍ ቀጥሏል።

የአልጄሪያ መንግስት በአብያተ ክርስቲያናት #ላይ እየወሰደ ያለውን ስልታዊ እርምጃ ቀጥሏል።

አልጄሪያ 42 ሚሊዮን #ህዝብ እንዳላት የሚነገር ሲሆን 1% ህዝብ በካቶሊኮች እና ፕሮቴስታንቶች የተወከለው የክርስቲያን ማህበረሰብን ናቸዉ።

#እንደ #ክርስቲያን ኮንሰርን ዘገባ ከሆነ በእስራኤል እና በሃማስ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በሰሜን አፍሪቃዊቷ ሀገር ላሉ ክርስቲያኖች ህይወትን አስቸጋሪ አድርጎታል።

"የአልጄሪያ መንግስት በግጭቱ #ውስጥ እስራኤልን እንደሚደግፉ እና የውጭ እና የምዕራባውያን ተፅዕኖዎች የአገሪቱን ብሄራዊ አንድነት እንደሚያበላሹ ይገነዘባሉ" ሲል ICC በሪፖርቱ ገልጿል።

ባለፈው #አመት በአጠቃላይ 16 አብያተ ክርስቲያናት መዘጋታቸውን ተከትሎ የአልጄሪያ መንግስት የክርስቲያን አገልግሎቶች እስከ 10 #ሰዎች #ብቻ እንዲስተናገዱ መወሰኑን ዘገባዉ አክሏል።

በተጨማሪም፣ ICC እንዳለው፣ ባለፉት ሳምንታት በርካታ የአልጄሪያ ፓስተሮች በእምነታቸው ምክንያት ታስረዋል።

ICC (አይሲሲ) በሪፖርቱ "አብዛኞቹ የአልጄሪያ ክርስቲያኖች ከካቢሌ ጎሳ የመጡ በመሆናቸው የክርስቲያኖች ሁኔታ በአልጄሪያ ያለው ሁኔታ የበለጠ የተወሳሰበ ነው" ሲል ገልጿል።

"በአልጄሪያ ውስጥ ያለው ክርስትና ረጅም #ታሪክ ያለው ነው እና በአልጄሪያ መንግስት በአልጄሪያ ክርስቲያኖች እምነት እና በአካባቢው የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች መካከል ያለውን ልዩነት በአልጄሪያ መንግስት መለየት አለበት" ሲል አይሲሲ ተናግሯል.

አልጄሪያ በኦፕን ዶርስ የአለም ለክርስትና አስቸጋሪ ከሆኑ ሀገራት የ2023 ዝርዝር መሰረት ክርስትያኖች ከሚሰደዱባቸው 50 ሀገራት 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።
“ካሁን በኋላ #ሴት #ነኝ የሚሉ ወንዶችን አናስተምርም” ኖተርዳም ስነ መለኮት ኮሌጅ

በአሜሪካ የሚገኘው እውቁ የኖተርዳም ስነ መለኮት ኮሌጅ ከዚህ ቀደም ያስተላለፈውን ውሳኔ ቀለበሰ። በአሜሪካ ኢንድያና ግዛት የሚገኘው የቅድስት #ማርያም ኖተርዳም የሴቶች ስነ መለኮት ኮሌጅ #ነው #ወደ ቀድሞው አቋሜ ተመልሻለው ያለው።

የኮሌጁ ፕሬዝዳንት #እና የቦርድ ሰብሳቢ በጋራ በመሆን “ወደ ካቶሊካዊት እሴታችን ተመልሰናል” ሲሉ መግለጫ አውጥተዋል።

ከወር በፊት ሴት ሆነው ተፈጥረው #ወንድ ነኝ ብለው የሚያምኑ ሰዎችን ኮሌጁ እቀበላለው ብሎ ነበረ። ኮሌጁ በውሳኔው ምክኒያት ትችቶች ተዘንዝረውበታል።

የኮሌጁ ቦርድ እና መሪዎች #ምንም #እንኳን በተለዋዋጭ አለም #ውስጥ ብንኖርም፣ የቤተ ክርስቲያንን አቋም ሳንቀያይር እናስቀጥላለን ሲሉ ተደምጠዋል።

ውሳኔው #ግን በኮሌጁ ተማሪዎች እና መምህራን ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም። ይሄንን አይነት ምላሽ ከኮሌጃችን ማህበረሰብ ባንጠብቅም፣ ካቶሊካዊ ማንነታችንን ግን አስጠብቀን መሄድ አለብን ሲሉ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።

ባለፈው #ወር በወሰንነው ውሳኔ በኮሌጃችን ህብረትን የሚያመጣ መስሎን ነበረ፣ #ነገር ግን ልዩነትን ፈጥረናል፣ ለዚህም #ይቅርታ እንጠይቃለን ብለዋል።
#ቤተክርስቲያን ላይ በተፈጨመ ጥቃት 15 ሰዎች ተገደሉ።

በቡርኪና ፋሶ ታጣቂዎች በቤተ ክርስቲያን ላይ በፈጸሙት ጥቃት በርካቶችን ገደሉ።

ቡርኪና ፋሶ #ውስጥ በአንድ መስጂድ እና ቤተክርስቲያን ላይ በተመሳሳይ ቀን በተፈጸመ ጥቃት በርካታ #ሰዎች መገደላቸው የአገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ።

#እሁድ #ቀን በቡርኪና ፋሶ ሰሜን ምሥራቅ ግዛት ውስጥ በሚገኝ #አንድ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ላይ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 15 ምዕመናን ተገድለዋል።

ኢሳካኔ በተባለው ስፍራ ለእሁድ ጸሎት ሥነ ሥርዓት በተሰባሰቡት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን አባላት ላይ ጥቃቱን የፈጸሙት ተጠርጣሪ ታጣቂዎች ናቸው ሲሉ አንድ የቤተ ክርስቲያኗ ባለሥልጣን ከሰዋል።

በመስጂድ እና በቤተክርስቲያን ላይ በተመሳሳይ ዕለት የተፈጸመው ጥቃት ተያያዥነት ይኑረው አይኑረው በይፋ የታወቀ ነገር ባይኖርም አንድ የቡርኪና ፋሶ የግል ጋዜጣ ጥቃቶቹ የተቀነባበሩ ሊሆኑ ይችላሉ ብሏል።

ቡርኪና ፋሶ ውስጥ በሃይማኖት ተቋማት እና መሪዎች ላይ የሚፈጸም ጥቃት እምብዛም ያልተለመደ አይደለም ሲል ቢቢሲ አስነብቧል።

ከሰሜናዊቷ ጂቦ ከተማ ከአምስት #ዓመት በፊት ተጠልፈው የተወሰዱ #አንድ ቄስ አስካሁን የደረሱበት አልታወቀም። ከሦስት ዓመት በፊት ደግሞ ከዚያው ከተማ በታጣቂዎች የተጠለፉ አንድ ኢማም ከቀናት በኋላ ሞተው ተገኝተዋል። ዘገባው የBBC ነው።
#ሩስያ ወሰነች... የግብረ ሰዶም እንቅስቃሴ የሽብር ድርጊት ነዉ።

ሩሲያ የግብረ ሰዶም እንቅስቃሴን የአክራሪነት #እና የሽብር ድርጊት ዝርዝር #ውስጥ አካተተች

የሩሲያ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ተቆጣጣሪው ሮስፊንሞኒቶሪንግ አለምአቀፍ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን በአሸባሪነት እና በአክራሪነት ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን የሩሲያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ውሳኔው የተደረሰው ሩሲያ ከሞስኮ የፍትህ ሚኒስቴር የቀረበለትን አቤቱታ ተከትሎ የግብረሰዶም ተከራካሪዎች አክራሪ ተብለው እንዲጠሩ በህዳር ወር ላይ የሩሲያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከወሰነ በኋላ ነው ተብሏል።

የሩሲያ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት አክራሪ ወይም አሸባሪ ተብለው የተፈረጁና በዝርዝሩ የሚካተቱ የግብረሰዶም አቀንቃኞችን ወይም ቡድኖችን የባንክ ሂሳቦች የማገድ ስልጣን ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።

#tikvahethmagazine
የቀድሞው የ #አሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መጽሃፍ #ቅዱስ መሸጥ ጀመሩ።

ትራምፕ በራሳቸው ማህበራዊ ትስስር ገጽ (ትሩዝ ሶሻል) ደጋፊዎቻቸው “ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ” የሚል ስያሜ ያለውን መጽሃፍ ቅዱስ እንዲገዙ ጥሪ አቅርበዋል።

#ወደ ፋሲካ በዓል እየተቃረብን ነው፤ ‘ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ’ መጽሃፍ ቅዱስን በመግዛት አሜሪካ ዳግም እንድትጸልይ እናድርጋት” ሲሉም ነው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት።

#ሁሉም አሜሪካውያን በቤታቸው መጽሃፍ ቅዱስ ሊኖራቸው እንደሚገባም ነው ያነሱት።

ትራምፕ ዝርዝር #ውስጥ መግባት ባልፈልግም መጽሃፍ ቅዱስ በህይወቴ ውስጥ ልዩ ቦታ አለው ብለዋል።

“ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ” መጽሃፍ ቅዱስ God Bless The USA Bible.com በተሰኘ ድረገጽ በ59.9 ዶላር ለገበያ ቀርቧል ተብሏል።

ድረገጹ መጽሃፍ ቅዱስ በትራምፕ መተዋወቁ “ምንም አይነት ፖለቲካዊም ሆነ የምርጫ ቅስቀሳ” አላማ የለውም ማለቱንም አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል።

#አዲሱ የመጽሃፍ ቅዱስ ግዙ ቅስቀሳም በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ትራምፕ በቀጣዩ ምርጫ ክርስቲያን ደጋፊዎቻቸውን ለማብዛት ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ተገልጿል።
#ብዙ ዋጋ የተከፈለበት #በኢትዮጵያ ትልቁ የመፅሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት ተመረቀ።

በዘላለም #መንግስቱ ተጽፎ ከ1,300 ገጾች በላይ ተዋቅሮ ከ4,800 በላይ ቃላት ያካተተው ይህ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የጸሀፊው ወዳጆች በተገኙበት በCETC) ኢትዮጵያን ቴዎሌጂካል ኮሌጅ በድምቀት ተመርቆ ለአንባብያን ተሰራጭቷል።

በመድረኩ መጽሀፉን #ሙሉ በሙሉ ጽፎ ለማጠናቀቅ 23 ዓመታት እደፈጀ እና በዚህ ስራ #ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት ምስጋናውን አቅርቧል።

ዘላለም መንግስቱ በንግግሩ ይህ መፅሐፍ ማለት እንደ "ማንኪያ" ነው። ዋናው ምግቡ ግን "መፅሐፍ ቅዱስ" ነው። ያለ ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስን የበለጠ ለመረዳት የሚያግዝ መጽሐፍ እንደሆነ ተናግሯል።

አክሎም ምንም እንኳን እጨርሰዋለሁ ብዬ ባልጀምረውም ለብዙዎች የሚያግዝ በመሆኑ በእግዚአብሄር እርዳታ ተጠናቋል። ይህ መጽሐፍ በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ የተጻፈ እንደመሆኑ መጠን ይህ መጽሀፍ መጽሀፍ ብቻ ሳይሆን አደራም ጭምር ነው ሲል ተናግሯል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉ መሪዎች እረጅም አመታትን በትዕግት በመጻፍ ይህንን መጽሀፍ በዚህ ወቅት ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በማበርከቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ ዘመን ያለን አገልጋዮች ይህንን መጽሀፍ ባንጠቀምበት ፤ እና ባንሰራበት ለእኛ እዳ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ዘላለም መንግስቱ ከዚህ ቀደም መንፈስ ቅዱስ እና ካሪዝማዊ ቀውሶች ፤ እንዘምር ወይስ እንዝፈን ፤ ክርስቲያናዊ ኢትዮጵኝነት ፤ የሐሰተኞች እሳተ ጎመራ ፤ ትንቢተ ዕምባቆም ፤ የይሁዳ መልዕክትን ጨምሮ ወደ 20 የሚደርሱ መጽሀፍትን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አበርክቷል።

#የኢትዮጵያ ቃለ #ሕይወት #ቤተክርስቲያን #ዋና ጸሐፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት #እና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች በጽሎት መጽሀፉን መርቀው ለንባብ እንዲበቃ በይፋ መርቀውታል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ሙሉ ዘገባውን አሰናዳንላችሁ። በቻናላችን ስም ለወንድም Zelalem Mengistu የተሰማንን እጅግ ትልቅ ደስታ እየገለጽን ሁላችሁም ትጠቀሙበት ዘንድ እናበረታታለን።
#እንዴት ልንሆን እንችላለን? #ነገ #ምን ይሆናል ?
ጊዜው የማይገቡን ነገሮች የሚነገሩበት ነው።

አለም የምትለው ሌላ ነው እኛ የምንለው ደግሞ #እግዚአብሔር አለልን ነው።

ጠዋትና #ማታ በሚዲያ የምንሰማው #አለም በብዙ ፍረሃት #ውስጥ ያለችበት #ጊዜ ነው።

#እምነት ሁኔታን መካድ አይደለም ከሁኔታ በላይ የሆነውን #አምላክ ከፍ ማድረግ ነው።

ምንዛሬ ከፍ አለ ዝቅ አለ። ኑሮ ተወደደ እረከሰ ስለዘመኑ የሚወራው አብዛኛው አይገባንም።

#እኔ ግን እንዲህ እላችኋለው ለእግዚአብሔር ዘመን ከፍ አይልም ዝቅ አይልም። ኑሮ ስለረከሰ አልኖርንም ኑሮ ስለተወደደ አንጠፋም።

በሰው ካልኩሌሽን አልኖርንም አሁንም አንኖርም። ምንም እንኳን ምድረበዳ ቢሆን #ኢየሱስ አለ።

ዘመኑ አስጨናቂ ነው ? እውነት ነው ግን ኢየሱስ አለ።
#የትግራይ የሀይማኖት አባቶች ፖለቲከኞች ልዩነቶችን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳሰቡ።

አባቶቹ አክለዉ አለመግባባቶችን ለመፍታት #ውይይት እንዲደረግ ጠይቀዋል።

የትግራይ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ #ቤተክርስቲያን የሀይማኖት አባቶች የህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (#ህወሓት) አመራሮች #እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዩነታቸውን ሊያባብሱ ከሚችሉ መግለጫዎች እንዲቆጠቡ ጠይቀዋል።

በትላንትናዉ #እለት በሰጡት መግለጫ፣ በተለይም በክልሉ ወቅታዊ ፈተናዎች #ውስጥ የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል ሲል #አዲስ እስታንዳርድ አስነብበዋል።

"አባቶቹ ጥሪውን ያቀረቡት የአሜሪካው አምባሳደር ሁለቱንም ቡድኖች በመቀሌ ካነጋገሩ በኋላ ነው"

#Ethiopia #addisababa #news #NewsUpdate #BREAKING #BreakingNews