The Christian News
5.36K subscribers
3.06K photos
27 videos
722 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#አስደሳች #ዜና #ለኢትዮጵያ #ቤተክርስቲያን

#የአማርኛ #መጽሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት በድል ተጠናቋል።

ይሄንን ዜና እንደሰማው በቅድምያ እግዚአብሄርን አመሰገንኩኝ ምክንያቱም ለቤተክርስቲያን የአሁኑን ጨምሮ ለቀጣዩ ትውልድ የሚሆን በረከት እየመጣ እንደሆነ አምናለሁ።

ዜናው ለ23 ዓመታት ሲለፋበት የነበረው "የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት" በእግዚአብሄር እርዳታ እንደተጠናቀቀ የሚገልጽ ነው።

ምንም እንኳን የሕትመት ስራው በቅርብ ጊዜ የሚከናወን ቢሆንም የአንድ ወጣት እድሜ የሚያክል ተለፍቶበት የተሰራ ስራ እንደመመልከት ግን የሚያስደስት ነገር ያለ አይመስለኝም።

ለማንኛውም መጽሐፉ ገና ስላልታተመ ዝርዝር ጉዳይ የለኝም ነገር ግን ስለጸሃፊው እና ከዚህ ቀደም ስለነበሩት ስራዎች ግን የተወሰነ ልበል።

ጸሐፊው ዘላለም መንግስቱ ይባላል። ብዙዎች በምላቴ #ክርስትና ስራዎቹ ያውቁታል። ላለፉት ከ3 አስርት አመታት በላት #የኢትዮጵያን #ቤተክርስቲያን በበርካታ መልኩ እያገለገለ የሚገኝ ወንድም ነው።

የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረበት ጊዜ ስለ ጌታ ከሰማ በኋላ ከዲያቆንነት እስከ ወንጌላዊነት ... በበርካታ የአገልሎት ስራዎች በኢትዮጵያ ቃለሕይወት ቤተክርስቲያን አገልግሎ ተገልግሎ ዘልቋል።

ወንድም ዘላለም በ1984 የታተመች እና "አዲስ ሕይወትን የማዳረስ ዘዴ" የሚል ርዕስ ያላት በወንጌል ስርጭት እና በደቀመዝሙርነት ላይ የምታተኩር መጽሐፍ ጀምሮ የነህምያ መጽሐፍ ማጥኛ እና ቀላል ማብራሪያ "መፍረስ እና መታደስ" "መጽሐፍ ቅዱስ እና የአፈታት ስሕተቶች " የሚሉ መጽሀፍትን ለቤተክርስቲያን አበርክቷል።

ብዙዎች "መንፈስ #ቅዱስ እና ካሪዝማዊ ቀውሶች" በሚል 1988 ለሕትመት በበቃውን መጽሐፍ ያውቁታል። ምንም እንኳን ይህ መጽሀፍ የዛሬ 27ዓመት ገደማ ቢጻፍም ዛሬም ድረስ መነጋገሪያ ነው።

"ክርስቲያናዊ ኢትዮጰኝነት" "እንዝፍን ወይስ እንዘምር" "የሃሰተኞች እሳተ ገሞራ" የተሰኙት ደግሞ የቅርብ ጊዜ የወንድም ዘላለም ስጦታዎች ናቸው።

አብዛኛው #ሰው ደግሞ በአንድ ወቅት "ይድረስ ለዘማሪዎች" በሚል በወጣው ሲዲ ዛሬም ድረስ ያስታውሱታል። በነገራችን ላይ ወንድም ዘላለም "ይድረስ ለዘማሪዎች" የሚለውን ሃሳብ ዛሬ ባለንበት ሁኔታ ቢሰራው ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት እጅግ ይከብደኛል።

በምካቴ ክርስትና ብዙዎችን ከሃሰተኛ ነብያት እና ትምህርቶቻቸው ለመታደግ ለአመታት ሲታገል ቆይቷል።

መኖሪያውን በባህር ማዶ ላስ ቬጋስ ያደረገው ወንድም ዘላለም ዛሬም ድረስ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የነገ እጣ ፈንታ ዘውትር ሲያስጨንቀው እመለከታለሁ።

ከ30 ዓመት በላይ በመጽሀፍ ስራ ውስጥ የቆየው ወንድም ዘላለም ከሰሞኑ ላለፉት 23 ዓመታት ሲደክምበት የነበረውን ስራ መጨረሱን አብስሯል። ይህ ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እጅግ ትልቅ የምስራች ነው።

ምክንያቱም እስከዛሬ በቤተክርስቲያን ይህን የመሰለ መፅመፍ አልነበረም ታዲያ ለመጽሀፍ ቅዱስ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሃገራችን የቋንቋ እድገትም አንድ ሃሳብ እንዳዋጣ አምናለሁ።

ከዚህ ቀደም #የክርስቲያን #ዜና ወንድም ዘላለምን ቃለ መጠይቅ የማድረግ እድል ያገኘን ሲሆን ምናልባት ለወደፊት በድጋሜ እንደምናገኘው ተስፋ እናደርጋለንን።

ለማንኛውም ለዚህ ድንቅ ስራ ግን እግዚያብሄርን እያመሰገንን በትዕግስት ስለጨረሰው ለወንድም ዘላለም አድናቆታችን ይድረሰው። ምንልባት ጥቂት በሚባል ጊዜ ውስጥ የእርማት ስራው ተጠናቆ ለህትመት እንደሚበቃ እና ሁላችንም ጋር እንደሚደርስ እምነታችን ትልቅ ነው።

ለማንኛውም ስለ ሁሉም #እግዚያብሄር ክብሩን ይውሰድ።
"በዉጪ #ሀገር ሆናችሁ የጥላቻን #ንግግር የምትዘሩ ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ አሳስባለሁ" ፖስተር ፃዲቁ አብዶ

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ይህንን ያሉት በአዲስ አበባ እስታዲየም እየተካሄደ ባለው የአዲስ አመት #ልዩ ፕሮግራም #ላይ ነው።

ፓሰተር ጻዲቁ በመልዕክታቸው 2016 #ሰላም የምንሆንበት አንዳችን ሌላውን የምናንጽበት ፤ የምንገነባበት ለሌላው ውድቀት የማንሰራበት ፤ ወጥመድ የማንዘረጋበት ፤ ድልድይ የምንገነባበት ድልድይ የምንሰራበት #ዘመን እንዲሆንልን #እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ ይርዳን ብለዋል።

ሰላም ለማንም #ሰው እጅግ አስፈላጊ ነው ያሉት መጋቢ ጻዲቁ ከሰላም ውጪ የሚገኝ ምንም ነገር የለም ቢገኝም አይቆይም ስለዚህ ለሁላችንም ሰላም እንዲሆን እለምናለሁ።

እኛ ክርስቲያኖች እንደ አማኝ ሀገራችን ሰላም እንድትሆን እንጸልያለን ምንም #እንኳን እንድምንፈልገው ባይሆንም እግዚአብሔር በሚያውቀው በዘላለማዊ እውቀቱ #ወደ #መልካም ነገር እንደምናልፍ እናምናለን።

እኛ እንደ ሰው ድርሻ ሰላም የሚቀጥልበትን እና የምንተናነጽበትን እንፈልግ ፤ ጥላቻን ከመዝራት እንቆጠብ ፤ ጥላቻ ከልባችን ይወገድ ፤ የቂም በቀል ፍላጎት ከውስጣችን ይጥፋ።

በውጪ ሀገር ሆነው የጥላቻን አረፋ በማሕበራዊ ሚዲያ የሚደፍቁ ሰዎች #ስለ እግዚአብሔር ብለው ጥላቻቸውን ከመዝራት እንዲቆጠቡ በዚህ አጋጣሚ በዚህ ጉባኤ በይፋ መልዕክት አስተላልፋለሁ ብለዋል።

Photo 📷 Hossana Photo & Video Production
#አንድ #ሰው በጌታ ያልሆነ ወዳጁ፣ ወደ ቤተ ክርስቲያናቹ ይዘኸኝ ሂድ ብሎ ይጠይቀዋል።

ይሄ ሰው የራሱን ማህበር እዳይወስደው፣ የምስባኩን ድራማ ፈራ! አሰብ አደረገና ይሻላል ብሎ ወዳሰበበት #ወደ ሌላ ህብረት ይዞት ሄደ። እዚያ የነበረው መድረክና ምስባክም ሰውየውን ከሰቀቀን አላዳነውም። ከዚያ ይሄ ወዳጁ ምን አለው፣ እዚህ #ቦታ አይደለም #እኔ፣ አንተስ ምን ታደርጋለህ አለው?

#እንደ #ክርስቲያን #አንድ አማኝ ያልሆነ #ሰው፣ ወደምትሄድበት ቤ/ክ ውሰደኝ ቢለን የት ይዘነው እንሄዳለን?

ፕሮፌሰር አታላይ አለም
#እይታ
#Opinion

የሰሞኑን #አንድ #ሁለት ዜናዎች ልንገራችሁ።

የቄስ ጉዲና ቱምሳ ባለቤት ጸሃይ ቶሎሳ ግለ #ታሪክ ተመርቋል። መጽሃፉ “በእቶን እሳት ውስጥ” የሚል ነው። የነዚህ ብርቱ እናት ታሪክ እና ምስክርነት ለአንድ አንድ ሰዎች የእምነት መልህቅ ሊሆን ይችላል፣ ቢባል ማጋነን አይሆንም።

ሌላው #ዜና ደግሞ በፌደራል መንግስትና #መንግስት ሸኔ በሚለው እራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ በሚጠራው ቡድን መካከል የተደረገው የሰላም ድርድር አሁንም ሳይሳካ ቀርቷል።

ይሄንን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ ሬድዋን ሁሴን አረጋግጠዋል። ከዚህ የሰላም ድርድር #መልካም ውጤት ይገኛል በሚል፣ ክርስቲያኑ ምነኛ ጓጉቶ እንደነበረ ማሰብ አይከብድም።

በተመሳሳይ ክፍለ ዘመን #ውስጥ ፣ በተመሳሳይ ርዕሳቸው፣ ረግጦ በሚገዛ መንግስት፣ የወንጌልን ነጻ አውጪነት አውጀው፣ የተገደሉ የዘመናት ክስተቶች ላውራችሁ።

#ቄስ_ዴትሪች_ቦንሆፈር በ1906 በጀርመን ብሬስሎው በተባለ ስፍራ የተወለዱ #ሰው ናቸው። እኚህ ሰው ስነ መለኮት አጥኚ ወይም ቲዎሎጂያን፣ ኮንፌሲንግ በተባለች ሉተራዊ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቄስ #እና ጸረ ናዚ ሰው ነበሩ።

የአዶልፍ ሂትለር ተቃዋሚ መሆን የዋዛ ነገር አይምሰላችሁ። ከናዚው አዶልፍ ሂትለር የአስተዳደር እቅዶች መካከል “ኢውታናዢያ” የሚባል ፕሮግራም ነበረ ይባላል። በዚህ ፕሮግራማቸው ሰው ከሚሰቃይ ቀድሞ መሸኘት የሚል ነው።

#ትንሽ የታመመ የመዳን ተስፋ ሳይሆን፣ ከህመሙ ማረፊያ መግደል ያሰበ “በጣም ቅን ሰው ናቸው” ነበረ። ይሁዲዎች #ላይ ያደረገውን ጭካኔ፣ አለም ያወቀው ነው። ቦንሆፈር ይሄንን ስርዓት ነበረ በአደባባይ ቆሞ የተቃወመው። ያው በእሳት ፊት ቆሞ ነበረና እሳቱ በላው። በተወለደ በ39ኛ አመቱ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌልን ሰብኮ ተሰቅሎ ተገደለ።

#ቄስ_ጉዲና_ቱምሳ በ1929 በኢትዮጵያ ወለጋ ቦጂ ከተማ የተወለዱ ሰው ናቸው። ተስፋ አደርጋለው ስለ ቄስ ጉዲና የማያውቅ ወንጌላዊ ክርስቲያን፣ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ማለት ይከብዳል። ግን ዝም ብዬ ታሪኩን ልንገራችሁ።

እኚህ ቄስ የስነ መለኮት አጥኚ #ወይም ቲዎሎጂያን፣ #የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ በተባለች ሉተራዊ ቤ/ክ ውስጥ ቄስ እና በሃያሉ ደርግ መንግስት ፊት የቆሙ ሰው ነበሩ። የደርግ ተቃዋሚ መሆንም የዋዛ ነገር አይደለም።

ኮለኔል መንግስቱ ማለት፣ በርሳቸው ዘመን በለጋ እድሜው አፈር የገባ ወጣት፣ በቀይ ሽብር ስም ያለቀው ተቀናቃኝ ፖለቲከኛና ለገዛ አጋሮቻቸው ያልተመለሱ ባለ ደም እጅ ሰው ነበሩ። ያ ኮለኔል መንግስቱና አገዛዙም ነበር ሆኗል።

እግዜር ደጉ፣ የማያሳልፈው የለም። ቄሱ ጉዲና በዚህ ለአፍሪካ እንኳን አይመለስም በተባለ ወታደር ፊት ቆመው “ወንጌል ነጻ ያወጣል” ብለው ሰብከዋል። እሳቸውም እሳት ፊት ቆመዋልና እሳት በላቸው። በተወለዱ በ50 አመታቸው የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ሰብከው በደርግ ወታደሮች ተገደሉ።

የነዚህ ሁለት በእሳት ፊት የቆሙ ቀሳውስት ህይወት፣ በሄሮድስ ፊት ቆሞ እውነት ተናግሮ አንገቱ የተቀላውን መጥምቁ ዮሃንስን ህይወት ይመስላል። የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት፣ በአስፈሪው የሮማ መንግስት ፊት፣ በአይሁድ ካህናት ፊት፣ በፈሪሳዊያንና ግሪካዊያን ፊት “እናንተ የእፉኝት ልጆች እያሉ”፣ መኖር ሳያሳሳቸው፣ መሞት ሳያስፈራቸው ወንጌልን የሰበኩ ጀግኖች ናቸው።

ቄስ ቦንሆፈርና ቄስ ጉዲናም በአፈ ሙዝ እንጂ በአፉ በማያወራ መንግስት ፊት ቆመው፣ መኖር ሳያጓጓቸው፣ ሞት ሳያስፈራቸው ወንጌልን ሳይቀንሱና ሳይጨምሩበት የሰበኩ የቤተ ክርስቲያን ቅሬታዎች፣ የክርስቶስ ልጆች ናቸው።

ዛሬስ መምህሩ፣ ጳጳሱ፣ ቄሱ፣ ፓስተሩ፣ ነብዩ፣ ሐዋርያው፣ ሼፐርዱ፣ ዳዲው የቱ ጋር ቆመሃል? ጌታ ኢየሱስ በጎቼን ጠብቅ ያለው ስመኦን ጴጥሮስ፣ ከአለም 20በመቶ ህዝብን በሚገዛው ግዙፉ የሮማ መንግስት ተዘቅዝቆ ተሰቀለ።

አንተስ በጎቼን ጠብቅ የተባልከው እረኛ ሆይ ፣ ለበጎቹ ስትል፣ እንደ ስመኦን ጴጥሮስ ተዘቅዝቀህ ለመሰቀል፣ እንደ ቦንሆፈር በናዚ ለመሰቀል፣ እንደ ጉዲና በደርግ ወታደር የአሞራ ሲሳይ ለመሆን #ተዘጋጅተሃል?

ክርስቲያን ሆኖ መኖር እራሱ ዋጋ በሚያስከፍልበት በዚህች ምድር ላይ ለወንጌል ዋጋ ለመክፈል የተዘጋጀህ ነህ ወይስ፣ ለአገልግሎትና ለእረፍት በV8 እና FORD F150 የምትምነሸነሽ #ሆነሃል? አለም ህይወት የሆነውን ክርስቶስን ለመስቀል ካልራራች፣ አንተ እውነተኛውን የርሱን ህይወት የምትሰብከውን የምትምርህ #ይመስልሃልን?

ዙሪያ ገባህን አይተህ ወንጌል የሚሰበክ ከጠፋ፣ ከተኩላ የምትጠብቀው በግ ከሌለ፣ ምናልባት ወንጌሉ የሚያስፈልገው፣ እረኝነቱ የሚያስፈልገው፣ ላንተው እራስህ እንዳይሆን የቆምክበትን አስተውል?
የውክልና #ውጊያ‼️መጋቢ ፃዲቁ አብዶ
#ድንቅ #መልዕክት

ጦርነቱ የውክልና ጦርነት ነው የእውነተኛ አምላክና የአማልእክት ጦርነት ...

    መነሻ ቃል 1ሳሙ 17

👉 ቁጥር 4 በዚህ ስፍራ #ስለ ጎሊያድ ማንነት ይዘረዝራል ስለ ቁመቱ የጌት #ሰው መሆኑን ጀግንነቱን ትጥቁን ይናገራል::

👉 እስራኤልና ፍልስጤም ሁሌም ይዋጋሉ:: #በአንድ ወቅት #ግን  ጎሊያድ ያልተለመደና #እስራኤል ያልተዘጋጁበት የጦር ስልት ይዞ ቀረበ!! #እኔ የፍልስጤማውያንን ወገን ወክዬ አለሁ እናንተም የሚወክላቹ ጀግና ሰው ካላቹ አምጡና እንዋጋ ካሸነፈኝ ህዝቤ #እንደ ተሸነፈ ይቆጠር የሚል::

✝️ ቁጥ 8 " እናንተ የሳኦል ባሪያዎች" ሲል ከእስራኤል ወገን የሆኑትን ወታደሮች ሞራል በሚያወርድ ንግግር ተናገራቸው ከመሪያቸው እንዲሸሹ:: የሰዎቹን #ልብ ለመምታት። #ዛሬም  አንዳንድ #ሰዎች #እግዚአብሔር ከሰጣቹ መሪዎች ለመለየት ሲፈልጉ #እንዲህ አይነት ፕሮፓጋንዳ ይዘራሉ ።

✝️ ሰውዬው ከልጅነቱ ጦርነት የለመደ ተክለ ሰውነቱና ትጥቁ አስፈሪ ነበርና ለአርባ ቀንና ሌሊት ጠዋትና ማታ በተናገራቸው ቁጥር ሳዖልም እስራኤልም እጅግ ይደነግጡ ነበር::

👉ይሄኔ በንጉሡ በሳዖል በኩል ጎሊያድን የሚገድል እንዲህ ይደረግለታል የሚል አዋጅ ቢወጣም አንድም ሰው ግን አልተገኘም ነበር::

ጦርነቱ የውክልና ጦርነት ነው የእውነተኛ አምላክና የአማልእክት ጦርነት ነው:: #ስለዚህ ጎሊያድ ዳዊትን በአማልክቶቹ ስም ነው የረገመው #ነገር ግን ይሄንን እውነተኛ #አምላክ የሚወክል ጀግና ሰው አልተገኘም

👉ቀጥሎ ባሉት ቁጥሮች የእሴይ ስምንተኛና የመጨረሻ ስለሆነው ልጅ ስለ ዳዊት ማስተዋወቅ ይጀምራል::

✝️ እግዚአብሔር በስውር ያዘጋጀው ማንም የማያውቀው ከእግዚአብሔር ጋር ግን የሚተዋወቅ ቤተሰቡ የረሳው ጌታ ድል ያለማመደው:: ዳዊትን ወንድሙ እብሪተኛ አለው ቢያሳድገውም ቀዳሚው ቢሆንም አልተረዳውምና::

✝️ ዳዊት ስለ ጎሊያድ ጥያቄን ሲጠይቃቸው ንጉሱ ሳዖልን ጨምሮ ከራሳቸው በላይ ስለ ጎሊያድ አስፈሪነት እንደሰው አወሩት አትችለውም አሉት የአምላክን ጣልቃ ገብነት እረስተዋል::

✝️ ጎሊያድ ላቀረበው እስራኤል ግን ለማያውቀው አዲስ የጦር ስልት የሚገጥም ጀግና በታጣበት ጊዜ እግዚአብሔር በድብቅ ያዘጋጀውን ሰው አመጣ:: ዳዊትም ይህ ያልተገረዘ ማን ነው? አለ‼️

#ይህም ንግግሩ ለሳዖል ደረሰ ሳዖልም ዳዊትን አስጠራው የራሱን ልብስ አለበሰው ። #ይህ የሚያሳየን #ዳዊት በሚያመጣው ድል ተቀባይነትንና ስምን ለራሱ ለመውሰድ በመፈለግ ነበር ። አንዳንድ ሰዎች አሉ በሰው ድካም ድሉን የነሱ አድርገው የሚወስዱ ። ዳዊት ግን በዚህ መንገድ አልለመድኩም አለ::

እግዚአብሔር ባለማመደው ስልት ገባ በአምላኩ በእግዚአብሔር ስም ሊዋጋው #ወደ ጦር ሜዳው ገባ ገደለው በራሱ ሰይፍ አንገቱን ቆረጠው ።

      👉👉 መልእክቴ ይህ ነው ‼️

✝️ ዛሬም በህይወት ጉዞአችን ውስጥ ያልለመድነው ፣ ያላወቅነው፣ ያልጠበቅነው ፣ ያልተዘጋጀንበት #እኛ በፍጹም የማንችለው #ፈተና  ቢገጥመንም ነገር ግን #ጌታ ከእኛ ጋር አለና ጌታ ባለማመደን መንገድ #ድል ይሰጠናል ያድነናል ይታደገንማል::

✝️ ካፈጠጠብኝ  በአለም ካለው
     እጅግ ይበልጣል በእኔ ያለው
     የፍጥረት ገዢ ተቆጣጣሪው
     ጌታ ኢየሱስ ከእኔ ጋራ ነው‼️

#መጋቢ ጻድቁ አብዶ
#ሰው ሸሽቶ #ቤተክርስቲያን ሲገባ #እንዴት ይገደላል? አገዳደሉ አሳቃቂ ነው። ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ

የመካነ ኢየሱስ ፕሬዝደንት በዚህ ወረ በመካነኢየሱስ ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ #መጽሐፍ #ቅዱስ ግምባራቸው #ላይ ነበር የተገደሉት ምዕመናን ከአንድ #ቀን በኋላ ነው የተገኙት ብለዋል።

ፕሬዝደንቱ አክለው #እንደ ቤተክርስቲያን መረጃው እስኪጣራ ነው ይፋ ያላደረግነው ያሉ ሲሆን በቤተክርስቲያን አካሄድ የቻልነውን ያህል ሄደናል ያሉ ሲሆን #መንግስት የሕዝብ የድህንነት #ጉዳይ በእጁ ነውና አሁንም #ተስፋ የምናደርገው መንግስት ገዳዮችን ለፍርድ እንደሚያቀርብ እናምናለን ሲሉም ተናግረዋል።

#ይህ ጥቃት በማን ነው የተፈጸመው ?

ከአደጋው የተረፉት ትክክለኛው ገዳዮች #ምን እንዳደረጉ እነማን እንደሆኑ ያውቃሉ። #ነገር #ግን ለደህንነታቸው ስለሚሰጉ ለመናገር ፍላጎት የላቸውም። መንግስት ግን ተከታትሎ ለፍርድ እንዲያቀርብልን እንጠይቃለን።
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።
አሜሪካዊው #ፓስተር ለጋዛ #ክርስቲያኖች #ገንዘብ በማሰባሰብ #ላይ ይገኛሉ ተባለ።

ዊሊያም ዴቭሊን የተባለው #ይህ ፓስተር ከ2010 ጀመሮ #ወደ ጋዛ ከ30 ጊዜ በላይ ለሚሽን #ስራ ተመላልሰዋል። በእነዚህ ጉዞአቸውም በጋዛ የሚገኙትን የመጨረሻዎቹን 3 አብያተ ክርስቲያናት ሲያገለግሉ ነው የቆዩት።

በጋዛ ከሚገኙ 2.2 ሚሊዮን ዜጎች መካከል ወደ 1ሺህ የሚጠጉ ብቻ ናቸው ክርስቲያኖች።

በጋዛ በአንዲት የግሪክ ኦሮቶዶክስ #ቤተክርስቲያን ከ500 በላይ ክርስቲያን #እና ሙስሊሞች ተጠልለው የነበረ ቢሆንም በእስራኤል የአየር ጥቃት ቤተ ክርስቲያኗም ፈራርሳ የተጠለሉትም ተሰደዋል።

ሪዲም የተሰኘ የባልቴቶች እና ወላጅ አልባ ሚኒስትሪ በጋዛ የሚያካሂዱት እኚህ ፓስተር ካለፈው የፈረንጆቹ ዲሴምበር #ወር ጀመረው #ወደ 50ሺህ ዶላር መሰብሰብ መቻላቸውን ለክርስቲያን ፖስት ገልጸዋል።

#ምንም #እንኳን ገንዘቡ የተሰበሰበ ቢሆንም ወደ ጋዛ ለመላክ መጀመሪያ ወደ ዌስት ባንክ ከዚያ በጋዛ ላሉ ክርስቲያኖች እንደሚደርስ ነው የተናገሩት።

በጦርነቱ በጋዛ #ብቻ እስካሁን ከ22 ሺህ በላይ ሰዎች ሲገደሉ ወደ 58 ሺህ የሚጠጉ ደግሞ ቆስለዋል። በአንጻሩ በእስራኤል 1200 ሰዎች ህይወት አልፏል። አሁን ለጋዛ ዜጎች የሚያስፍልገው ጸሎት እና ጸሎት ብቻ ነው ብለዋል።

ፓስተር ዊሊያም ዴቭሊን በግብጽ፣ ጋዛ፣ ፓኪስታን፣ አፍጋኒስታን እና ጆርዳን የሚገኙ አናሳ ቁጥር ያላቸውን ክርስቲያኖች የሚያገለግል ሚኒስትሪ ይመራሉ።

ክርስቲያን መሪዎች ወደ ጋዛ ምድር ሄደው ለምን አይረዱም በሚል ጥያቄያቸውም ይታወቃሉ። ለአሁኑ ግጭትም ቢሆን የእስራኤልን ጦር እንዲሁም የሃማስ ጦር ይወቅሳሉ። በቬትናም ጦርነት ተዋጊ ነበርኩ የሚሉት እኚህ #ሰው በጦርነት ዋናዎቹ ተጎጂዎች ንጹሃን ናቸው ብለዋል።
#ቤተክርስቲያን ዉስጥ #አንድ ሰዉ ተገደለ።

እውቁ አሜሪካዊ ፓስተር ጆዬል ኦስቲን የምትመራው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተከፈተ ጥቃት የአንድ #ሰው ህይወት ማለፉ ተሰማ።

ሌክዉድ ቹርች በመባል በምትታወቀው በዚህች ቤ/ክ ውስጥ ነው ትላንት የሰንበት ፕሮግራም ላይ ጥቃቱ የተፈጸመው። ጥቃት አድራሿ #ሴት ስትሆን በወቅቱ ስራ ላይ ባልነበሩ ፖሊሶች ህይወቷ ሊያልፍ ችሏል።

ጥቃቱን ባደረሰችበት ወቅት የ5 #አመት ህጻን #ልጅ ይዛ እንደነበረም ተነግሯል። ህጻኑም ጉዳት ደርሶበት የህክምና ክትትል እየተደረገለት እንደሚገኝ ፖሊስ አስታውቋል። በጥቃቱ እስካሁን አንዲት ሴት #ብቻ ናት እግሯ ላይ በጥይት የመታችው እና ጉዳት የደረሰባት።

የቤ/ክኗ መሪ ፓስተር ጆዬል ኦስቲን እንደዚህ ባለ የጨለማ ጊዜ፣ እምነታችን እንጠብቅ መቼም ቢሆን ጨለማ አያሸንፍም #እግዚአብሔር በብርሃን ይመራናል ሲል ለክርስቲያን ፖስት ተናግሯል። በዚህ ወቅትም በፍቅር እና በመያያዝ አብረን መቆም ይገባናል ብለዋል።

ጥቃት አድራሿ በተኩሱ ወቅት ቦምብ ይዣለው በማለት ስታስፈራራ እንደነበረና መርዝ ነው እያለች ስፕሬይ ስትረጭ ነበረ ብሏል ፖሊስ ባደረገው ምርመራ።

ሌክዉድ ቸርች በአሜሪካ ቴክሳስ ሂውስተን የምትገኝ ሲሆን፣ መሪዋ ጆዬል ኦስቲንም በስህተት ትምህርት ስሙ ደጋግሞ ሲነሳ ይታወሳል። ዘገባዉ የThe Christian Post ነዉ።
#የወንጌል ዘመቻ ሊካሄድ ነዉ።

ጋፕስ አለም አቀፍ አገልግሎት
አንጾኪያ የወንጌል እንቅስቃሴ

ጋፕስ ያለፉትን 14 ዓመታት የአገልጋዮችን የኑሮ ክፍተት መሙላት፡ የመንፈሳዊ ክፍተት መሙላት (ማጎልበት፡ ማስተማር) ላይ ሲሰራ ቆይቷል።

አንጾኪያ የወንጌል እንቅስቃሴ የ10 ቀናት የወንጌል ዘመቻ በነገው እለት ጀምሮ ከሚያዝያ 9-19 ድረስ ይካሄዳል።

ዘመቻው፡ የቡና #ሻይ ሰዓትን ለወንጌል፡ ሙስሊም ኢቫንጀሊዝም፡ የደም ልገሳ፡ የጎዳና ወንጌል፡ #አንድ #ሰው ለኢየሱስ፡ ማህበራዊ ሚድያን ከወንጌል፡ አርትን ለወንጌል፡ በመርዳት ወንጌል መስበክ፡ ሙዚቃን ለወንጌል፡ የርህራሄ አገልግሎት በዘመቻው በየእለቱ የሚሰሩ ስራዎች ናቸው።

የጋፕስ ሚኒስትሪ መስራችና መሪ መጋቢ ዳንኤል ዋለልኝ ሁሉም ሰው የተልዕኮ ሰራተኛ መሆኑን ማወቅ ይኖርበታል፡ በእነዚህ 10 ቀናት ሁሉም #ክርስቲያን አንጾኪያ በሚያደርገው የወንጌል ዘመቻ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የክርስቲያን መገናኛ ብዙሃንም በዚህ የወንጌል ዘመቻ በትልቅ ተሳትፎ እንዲሰራ፡ የክርስቲያን ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዘሪሁን ግርማ ጥሪ አቅርበዋል።

አንጾኪያ ሙቭመንት #አዲስ የወንጌል ተኮር አገልግሎት ነው። አላማው በሐዋ ስራ 11 እንደተገለጸው፡ የአንጾኪያ ቤ/ክ የወንጌል አካሄድ መድገም ነው።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና መግለጫውን በስፍራዉ በመገኘት አሰናዳንላችሁ።
ራስን ማጥፋት

የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፣ Assisted Suicide #ወይም በእገዛ ራስን ማጥፋትን እየተቃወሙ ይገኛሉ።

ይሄንን ያውቁ ነበረ። በአለማችን 15 ሃገራት በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ይፈቅዳሉ። በሃኪም የታገዘ ራስን ማጥፋት ማለት፣ #አንድ #ሰው ራሱን ሲያጠፋ በሃኪም እገዛ ህጋዊ በሆነ መንገድ የህይወት ጉዞውን ማብቃት ማለት ነው።

የስኮትላንድ አብያተ ክርስቲያናት ይሄንኑ ድርጊት በሃገሪቱ ህጋዊ እንዲሆን መጠየቁን ተከትሎ ነው ድምጻቸውን ያሰሙት።

ለ129 የምክር ቤት አባላት በተላከው ደብዳቤ መሰረት፣ በአንድ የምክር ቤቱ አባል የቀረበውን ይሄንኑ አጸያፊ ተግባር ህጋዊ እንዳይደረግ ጠይቀዋል።

በደብዳቤያቸው፣ ይሄ ህግ የሰው ልጅን ሞራላዊነት አሽቀንጥሮ መጣል ነው፣ እንደ ሃገር አለን የምንለውን የሰው ልጆች ዋጋ የሚያሳጣን ነው ብለዋል።

ህጉ የሚጸድቅ ከሆነ ስኮትላንድ ስነምግባር የሌለባት፣ ምክር ቤታችንም ለሰው ልጆች ዋጋ የሌለው አዳራሽ መሆኑ ነው ሲሉ አሳስበዋል።

በእገዛ ራስን ማጥፋት ማለት የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ የሌለው መሆኑን ማሳያ ነው። ዘፍጥረት ላይ #እግዚአብሔር በአምሳያው የሰውን ልጆች መፍጠሩ፣ ሁሉም የሰው #ልጆች በእግዚአብሔር እንደሚወደድ ማሳያ ነው። ስለዚህ የሰው ልጅ ህይወት ዋጋ አለው ብለዋል።

ይሄንን ደብዳቤ የላኩት ቄስ አንድሪው ዶውኒ እና ቄስ ቦብ አክሮይድ የዩናይትድ ፍሪ ቸርች ኦፍ ስኮትላንድ አገልጋዮች ናቸው።

ሃገራችን ስኮትላንድ ሰዎች ራሳቸውን ማጥፋት የማያስቡባት መሆን አለባት ብለዋል። ምናልባት በመሰል ስሜት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎችን ማህበረሰባችን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ፍቅርና እንክብካቤ ማሳየት አለበት ብለዋል።

ስኮትላንድ የ1517ቱ ተሃድሶ እንቅስቃሴ እንዲስፋፋ ያገዙት ጆን ኖክስ ትውልድ ሃገር መሆኗ ይታወሳል።
በኦሮሚያ ክልል ኢሉአባቦራ መቱ ከተማ ለሃይማኖታዊ ስብከት አደባባይ ወጥተው የነበሩ የሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አባላት በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ድብደባ ተፈጽሞባቸው ጉዳት እንደደረሰ ለቢቢሲ ተናገሩ።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እና በወቅቱ በስፍራው የነበሩ ግለሰቦች እንዳሉት ከሆነ የፀጥታ ኃይሎቹ በፈጸሙት ድብደባ የተጎዱት ሰዎች ከ20 በላይ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

የመቱ ከተማ ከንቲባ አቶ ተሻለ ኤጀርሶ በበኩላቸው የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ያካሄዱት የጎዳና ላይ ስብከት ከተገቢው የመንግሥት አካል ፈቃድ እንዳላገኘ ተናግረዋል።

የሙሉ ወንጌል #ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ፓስተር ብርሃኑ ዘለቀ በበኩላቸው ከመቱ እና አካባቢዋ የመጡ የቤተክርስቲያኒቷ አባላት እሁድ ግንቦት 25/2016 ዓ.ም ለጎዳና ላይ ስብከት በወጡበት በፖሊስ ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል።

“ወደ ከተማዋ ጎዳና የወጣነው ወንጌል ለመስበክ ነው። ከአንድ #ሺህ #ሰው በላይ ይሆናል በወቅቱ የወጣው። መንገድ ሳንዘጋ በጎዳናው ላይ እየተንቀሳቀስን እየሰበክን ነበር። ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው። የፀጥታ ኃይሎች መጥተው አስቆሙን” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

የከተማው ከንቲባ በበኩላቸው “በዕለቱ በከተማችን የትኛውም የእምነት ተቋም በከተማዋ ጎዳና ላይ አምልኮ ለማካሄድ በሚል ፈቃድ አልጠየቀም፣ አልወሰደም። በከተማው ጎዳና ላይ ወጥተው የነበሩ ሰዎችን ፖሊስ አስቁሟቸዋል። ፖሊስ ያስቆማቸው ፈቃድ ስለሌላቸው እና የመሰባሰባቸው ምክንያት ባለመታወቁ ነው” ብለዋል።

ፓስተር ብርሃኑ፣ የፀጥታ ኃይል አባላቱ ምዕመናኑን ካስቆሟቸው በኋላ እየዘመሩ የነበሩትን በመኪና ጭነው ወደ ፖሊስ ጣቢያ መውሰዳቸውንም ይናገራሉ።

ዝርዝር መረጃ ያንብቡ https://www.facebook.com/thechristiannews2018

#ወንጌል
#ሰው ተመኑ ስንት ነው?

በጋሽ ሽፈራው ወ/ሚካኤል የተጻፉ #ሁለት መጽሃፍት ተመረቁ።

መጻህፍቱ “የሰው ተመኑ ስንት ነው?” እና “የግለሰብ ሚና (እኔም ቁምነገር ነኝ)” ይሰኛሉ። መጻህፍቱን ያሳተመው አቢጊያ የሰላም ኢኒሼቲቭ ነው።

አቢጊያ የሰላም ኢንሺዬቲቭ፣ በጋሽ ሽፈራው ወ/ሚካኤል ሃሳብ አመንጪነት ከ35 ወንድሞች ጋር በመሆን ስለ ሃገር ሰላም ለመስራት ከጥቂት አመታት በፊት የተቋቋመ ነው። ፥ሁሉ በሰላም፣ ሁሉ ለሰላም በሚል መሪ ቃል የተቋቋመው ኢኒሽዬቲቩ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እውቅና ተቀብሎ እየሰራ ይገኛል።

ኢኒሽዬቲቩ ተቋማት ስለ ሰላም በሰላም የሚለውን መርህ እንዲከተሉ፣ ስለ ሰላም ከሚሰሩ ጋር አብሮ መስራትና ስለ ሰላም በሰላም ለቆሙ እውቅና መስጠት የሚሰራባቸው ስልቶቹ እንደሆኑ አስታውቋል። ስራውንም በወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና የወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት መካከል የነበረውን ልዩነት ለማርገብ በመስራት ጀምሯል።

ኢኒሽዬቲቩ በረጅም ጊዜ እቅዱ፣ ስለ ስላም የሰውኣን የአዕምሮ ውቅር ለመለወጥ በትዕግስት መስራት ላይ አተኩሮ ይሰራል።

#አድዋ ሙዚየም አዳራሽ በተካሄደው ምረቃ መርሃግብር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ #እና የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝን ጨምሮ ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎችና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዘገባውን አሰናዳንላችሁ።