The Christian News
5.32K subscribers
3.06K photos
27 videos
720 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#እንኳን #አደረሳችሁ

በታላት ጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የነቀምቴ ማህበረ ምዕመናን 100ኛ ዓመት ክብረ-በዓል ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በድምቀት ተካሄደ።

ማህበረ ምዕመኑ ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግበት የቆየው 100ኛው ዓመት የምስረታ #እና የአገልግሎት ቆይታን የሚዘክረው ክቡረ በዓል ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር፣ ማህበረ ምዕመኑ ስድስት ሺህ ሰዎችን እንዲያስተናግድ ባስገነባው አዲሱ የአምላክ አዳራሽ ተካሂዷል።

ከማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ #አንድ #ቀን አስቀድሞ የማህበሩ ምዕመናን በነቀምቄ #ከተማ በነቂስ በመውጣት የከተማ ፅዳት እና የጎዳና #ላይ የወንጌል ስርጭት አድርገዋል።

በዓሉንም ለመካፈል ከመላው #ኢትዮጵያ በርካታ እንግዶች፣ በውጪ ሀገራት የሚኖሩ የማኅበረ ምዕመኑ #ልጆች እና ማህበረ ምዕመኗን ለበርካታ ዓመታት ያገለገሉ ሚሲዮናዊያን ተገኝተዋል።

በዕለቱም በአፋን ኦሮሞ፣ በአማርኛ እና የእንግሊዝኛ ቋንቋዎች የተዘጋጀ እና የማህበረ ምዕመኑን የ100 ዓመታት አገልግሎት የዳሰሰ #መጽሐፍ ተመርቋል።

በዓሉም በተለያዩ መርሀ ግብሮች እስከ ታህሳስ 21/2016 ዓ.ም የሚከበር ይሆናል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በድጋሜ ለማህበረ ምዕመኗ አባላት እና ለመላዉ ክርስቲያኖች እንኳን አደረሳችሁ ብለን #መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን።
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።
#ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየትኛዉም መልክ የተመሳሳይ #ጾታ ጋብቻን አትፈቅድም።

#የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት #ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽ/ቤት ከሰሞኑ ርዕሳነ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች የፈቀዱት ቡራኬ ላይ ማብራሪያ ሰጠ።

ከሰሞኑ የሮማዉ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ቤተክርስቲያኗ ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ቡራኬ እንዲሰጡ ፈቃድ መስጠታቸዉን የተለያዩ #መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ይህንኑ ተከትሎም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ #ጠቅላይ ጽ/ቤት በጉዳዩ #ላይ #መግለጫ አዉጥቷል። ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ከካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ስርዓተ አምልኮ ጋር የሚጻረር ወይንም ዉዥንብርን ሊፈጥር የሚችል ስርዓተ አምልኮን ያወግዛል ብሏል።

ሆኖም የጳጳሱ መልዕክት በተቃራኒው ተወስዷል የሚል ሃሳብ ያለዉን መግለጫ ያወጣ ሲሆን ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ጋብቻን #ግን ጳጳሱ ፈቃድ አልሰጡም ብሏል።

አክሎም የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅስን በማስቀመጥ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየትኛዉም መልክ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን አትፈቅድም ፤ አታጸድቅምም ማለቱን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከመግለጫው ተመልክቷል።

ቤተክርስቲያኒቱ ሀጢያትን አትባርክም ታወግዛለች #እንጂ ያለዉ መግለጫዉ የተመሳሳይ ጾታ #ጋብቻ የኢትዮጵያ ባህል #እና እሴትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት እንደማይኖረዉም በመግለጫው አስታዉቋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል
#አሳዛኝ #ዜና

12ኛ አመቱን በያዘው የሶርያ እርስ በእርስ ጦርነት ምክኒያት የክርስቲያኖች #ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያሽቆለቆለ #ነው ተባለ።

በተለይ በበሰሜናዊ ሶርያ የምትገኘው አሌፖ #ከተማ በርካታ ክርስቲያኖች ይገኙባታል የነበረች ከተማ ነች።

ጦርነቱ ከተጀመረ ወዲህ 250ሺህ የነበረው የክርስቲያኖች ቁጥር፣ አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ #ወደ 50ሺህ ወርዷል።

በከተማዋ ያሉ ክርስቲያኖች አሌፖ በጦርነቱ ፍርስርሷ ከመውጧቷ በተጨማሪ፣ በአይ ኤስ አይ ኤስ፣ የኩርድ ታጣቂዎች፣ አማጺ ሃይሉና የሶርያ #መንግስት መካከል በሚደረግ ጦርነት የመጀመሪያዎቹ ገፈት ቀማሾች መካከል ናቸው።

ከ200ሺህ #በላይ ክርስቲያኖች ከአሌፖ #ብቻ መሰደዳቸው፣ በሃገሪቱ ጥቂት የሆኑ ክርስቲያኖችን ቁጥርን አደጋ #ላይ ጥሎታል ሲል #አለም አቀፉ #ክርስቲያን ኮንሰርን አስነብቧል።

አሌፖ ከጦርነቱ በፊት በሰሜናዊ ሶርያ የንግድ ማዕከል የነበረችና ጥንታዊ ከተማ ስትሆን፣ ከጦርነቱ ማግስት ተከስቶ በነበረው ርዕደ #መሬት ሳቢያም ሁኔታዋ ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል።

በ2023 የኦፕን ዶርስ ዝርዝር መሰረት ሶርያ 12ኛ ለክርስቲያኖች የማትመች ሃገር ናት።
አሜሪካዊው #ፓስተር ለጋዛ #ክርስቲያኖች #ገንዘብ በማሰባሰብ #ላይ ይገኛሉ ተባለ።

ዊሊያም ዴቭሊን የተባለው #ይህ ፓስተር ከ2010 ጀመሮ #ወደ ጋዛ ከ30 ጊዜ በላይ ለሚሽን #ስራ ተመላልሰዋል። በእነዚህ ጉዞአቸውም በጋዛ የሚገኙትን የመጨረሻዎቹን 3 አብያተ ክርስቲያናት ሲያገለግሉ ነው የቆዩት።

በጋዛ ከሚገኙ 2.2 ሚሊዮን ዜጎች መካከል ወደ 1ሺህ የሚጠጉ ብቻ ናቸው ክርስቲያኖች።

በጋዛ በአንዲት የግሪክ ኦሮቶዶክስ #ቤተክርስቲያን ከ500 በላይ ክርስቲያን #እና ሙስሊሞች ተጠልለው የነበረ ቢሆንም በእስራኤል የአየር ጥቃት ቤተ ክርስቲያኗም ፈራርሳ የተጠለሉትም ተሰደዋል።

ሪዲም የተሰኘ የባልቴቶች እና ወላጅ አልባ ሚኒስትሪ በጋዛ የሚያካሂዱት እኚህ ፓስተር ካለፈው የፈረንጆቹ ዲሴምበር #ወር ጀመረው #ወደ 50ሺህ ዶላር መሰብሰብ መቻላቸውን ለክርስቲያን ፖስት ገልጸዋል።

#ምንም #እንኳን ገንዘቡ የተሰበሰበ ቢሆንም ወደ ጋዛ ለመላክ መጀመሪያ ወደ ዌስት ባንክ ከዚያ በጋዛ ላሉ ክርስቲያኖች እንደሚደርስ ነው የተናገሩት።

በጦርነቱ በጋዛ #ብቻ እስካሁን ከ22 ሺህ በላይ ሰዎች ሲገደሉ ወደ 58 ሺህ የሚጠጉ ደግሞ ቆስለዋል። በአንጻሩ በእስራኤል 1200 ሰዎች ህይወት አልፏል። አሁን ለጋዛ ዜጎች የሚያስፍልገው ጸሎት እና ጸሎት ብቻ ነው ብለዋል።

ፓስተር ዊሊያም ዴቭሊን በግብጽ፣ ጋዛ፣ ፓኪስታን፣ አፍጋኒስታን እና ጆርዳን የሚገኙ አናሳ ቁጥር ያላቸውን ክርስቲያኖች የሚያገለግል ሚኒስትሪ ይመራሉ።

ክርስቲያን መሪዎች ወደ ጋዛ ምድር ሄደው ለምን አይረዱም በሚል ጥያቄያቸውም ይታወቃሉ። ለአሁኑ ግጭትም ቢሆን የእስራኤልን ጦር እንዲሁም የሃማስ ጦር ይወቅሳሉ። በቬትናም ጦርነት ተዋጊ ነበርኩ የሚሉት እኚህ #ሰው በጦርነት ዋናዎቹ ተጎጂዎች ንጹሃን ናቸው ብለዋል።
#አስደሳች #ዜና

የወንጌላውያን #ሚድያ ባለሙያዎች ማህበር ተመሰረተ።

በቢሾፍቱ ሊሳክ ሪዞርት በተካሄደ ምስረታ ጉባኤ #ላይ ከተለያዩ የሚድያ ተቋማት የተውጣጡ የሚድያ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።

በመረሀ ግብሩ ምስረታ ወቅት ማህበሩን ለመመስረት የተካሄደባቸውን የስራ ሪፖርቶች ለተሳታፊዎቹ ያቀረበ ሲሆን በመሀበሩ መተዳደሪያ ደንብ ማርቀቅ ዙሪያ ውይይት ተካሂዶ የማሻሻያ ሀሳቦች ቀርበው መተዳደሪያ ደንቡ ጸድቋል።

በእለቱም የማህበሩን ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት እንዲሁም የቦርድ አባላት የተመረጡ ሲሆን በዚህም መሰረት የማህበሩ ፕሬዝዳንት በመሆን ወንድም ዘሪሁን ግርማ ምክትል ፕሬዝዳንት ወንድም መሳይ አለማየሁ የተመረጡ ሲሆን ዘጠኝ የማህበሩ የቦርድ አባላትም ተመርጠዋል።

በእለቱም የጸሎትና #የእግዚአብሄር ቃል በመካፈል ፕሮግራምም ተካሄዷል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በማሕበሩ ምስረታ ሒደት ዉስጥ በበጎ ፍቃደኝነት ከፍተኛ ስራ ለሰሩ አባላት ምስጋናውን እያቀረበ።

በዛሬዉ እለት ማሕበሩን በቀጣይ ለመምራት ሃላፊነት ለተቀበሉ መሪዎች #መልካም የስራ ዘመን እንዲሆን እንመኛለን።
#አስደሳች #ዜና

በአሁኑ ወቅት #ብቻ በኢንዶኔዥያ ከ35 በሚበልጡ ቋንቋዎች መጽሃፍ #ቅዱስ ትርጉም እየተካሄደ ይገኛል።

ኢንዶኔዥያን ለየት የሚያደርጋት ነገር፣ በአለማችን #ላይ ብዙ የእስልምና #እምነት ተከታዮች ያሉባት ሃገር መሆኗ ነው። ዋይክሊፍ አሶሴሽን የትርጉም ስራዎቹን የሚያከናውነው፣፣ በአካባቢው ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትና #አዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ነው።

#አዲሱ የትርጉም ቴክኖሎጂ፣ በየአካባቢው የሚገኙ ክርስቲያኖች የትርጉም ስራውን ከፊት ሆነው ይመሩ ዘንድ ይረዳል ነው የተባለው። ይሄም መጽሃፍ ቅዱስ ባለቤትነታቸውን ይበልጥ ያረጋግጥላቸዋል። ግምገማ፣ ስልጠና፣ ህትመትና ስርጭቱንም ቢሆን እራሳቸው የየአካባቢው #ሰዎች እንዲሳተፉበት ይረዳቸዋል ነው የተባለው።

በአሁኑ ወቅት ብቻ ከዋይክሊፍ ተጨማሪ ሌሎች የመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ድርጅቶች #አንድ ላይ በመሆን ከ60 በማያንሱ የኢንዶኔዥያ ሃገር ቋንቋዎች እየተተረጎሙ ይገኛሉ።

በኢንዶኔዥያ ብቻ ለሚሰራው የመጽሃፍ ቅዱስ ስራ፣ ከ400 እስከ 500 ሺህ ዶላር በጀት ተይዞለታል። #ይሄ ወጪ ከበጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበ ሲሆን ሌሎችም በጸሎት የዚህ #ታላቅ ስራ አካል ይሁኑ ሲል ዋይክሊፍ ጥሪ አቅርቧል።

ኢንዶኔዥያ ውስጥ ከ700 በላይ ቋንቋዎች ይገኛሉ። ይሄም ሃገሪቱን በአለም ላይ ካሉ ቋንቋዎች 10 በመቶ በሃገሪቱ ብቻ መኖሩን ያሳያል።
#ዛሬ ይጠናቀቃል

“መጽሀፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በሕዝባችን #ሕይወት እናስርጽ!” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየዉ የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ይጠናቀቃል።

በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እና የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት መሪዎች በተገኙበት በመካሄድ #ላይ ይገኛል።

#የኢትዮጵያ መጽሐፍ #ቅዱስ ማሕበር አዘጋጅነት የመጽሀፍ ቅዱስ ሳምንት በዓል #እና የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ከሰኞ የጀመረ ሲሆን በዛሬዉ እለት የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ክርስቲያኑን #ስለ መጽሃፍ ቅዱስ ንባብ ማነቃቃት፣ በመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ የሚሰሩ አብያተ ክርስቲያናትን በተዛማጅ ስራዎች ላይ ማስተባበር፣ የወንጌል ስብከትን ማበረታት፣ ለአሁኑ ትውልድ የመጽሃፍ ቅዱስን አደራና ሃላፊነት ማስተላለፍ እና መጽሃፍ ቅዱስን ከአደጋዎች መጠበቅ በሳምንቱ ዉስጥ ሲሰራ የነበረ #ስራ ነዉ።

በሳምንቱ ዉስጥ ትውልዱን ስለ ቅዱሳት መጻህፍት እንዲያውቅ የማድረግ ስራ ፣ የህትመት ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ ማድረስ እና ማህበሩን ከህዝብ ጋር ማስተዋወቅ በአውደ ርዕይው ሲከናወን ቆይቷል።

የኢትዮጵያ መፅሐፍ ቅዱስ ማሕበር ሁሉንም ሁሉንም አብያተ ክርስቲያናት እና ምዕመናንን ባለፋት 98 ዓመታት አገልግሏል።

ፎቶ 📷 Hossana production Hossana
#ክርስቶስ እንኳን #ወደ ምድር ቢወርድ #አንድ አዳራሽ መስሪያ ቦታ አይሰጣችሁም

#ክርስቲያኖች ላይ ስደት በዝቷል።

በደቡብ ምስራቅ አውሮፓ በምትገኘው ኮሶቮ፣ ክርስቲያኖች #ላይ ስደት በርትቷል ተባለ።

በሃገሪቱ ክርስቲያኖች #ምንም አይነት የመሰብሰብ መብት እንደሌላቸው #እና ፈቃድ ለማግኘትም ሁኔታዎች እንደሚወሳሰቡባቸው ገልጸዋል።

የአርሜ #ቋንቋ ተናጋሪዎች የሚበዙባት ኮሶቮ፣ 93 በመቶ ዜጎቿ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው።

ምንም #እንኳን የሃገሪቱ ህገ መንግስት የሃይማኖት ነጻነትን የሚፈቅድ ቢሆንም፣ ክርስቲያኖች ላይ ግን መድሎና አመጽ ይበረታባቸዋል።

#ይህ ስደት በግል ደረጃም፣ የቀብር ስፍራ መከልከል፣ ንብረት የማፍራት መብት አለማግኘትና ሌሎችም በደሎች እየደረሱባቸው እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በተለይ #ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች፣ የባንክ ሂሳብ መክፈት፣ ንብረት ማፍራት እና ሰራተኞችን ቀጥሮ የመንቀሳቀስ ዴሞክራሲያዊ መብቶች የላቸውም።

በቅርቡ የወጣ #አንድ ህግ ደግሞ የሰርቢያ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊኮችን እና ሌሎችንም ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናትን ኢላማ ያደረገ ነው ይባልለታል።

በሃገሪቱ ያለፉትን 25 ዓመታት ያገለገሉ አንድ ቄስ ሲናገሩ፣ ያለው ስቃይ በግልጽ ስላልሆነ ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ብለዋል።

ለቀብር እንኳን በሙስሊሞች የቀብር ስፍራ፣ በኢማሞች የተመራ ቀብር ስነ ስርዓት እያደርግን ነው የምንገኘው ብለዋል። ምንም ቢሆን #ግን ለሃገራችን የወንጌል ተስፋ አለን ሲሉም እኚሁ ቄስ ይናገራሉ።

በኮሶቮ በ1980ዎቹ ወንጌላዊያን፣ ክርስቶስ እንኳን ወደ ምድር ቢወርድ አንድ አዳራሽ መስሪያ ቦታ አይሰጣችሁም የሚል ተደጋጋሚ ዛቻ ከወቅቱ ኮሚኒስት መንግስት ሲደርስባቸው እንደ ነበረ ዘገባዉ አስታዉሷል።
#የኢየሱስ ወታደር ነኝ ... #ወደ አምላኩ ሄደ 😭
ከ40ዓመት በላይ በጌታ ቤት ቆይቷል...

#ሄደ #ወደ አምላኩ ሄደ ...
ኢየሱስን ብሎ አለምን የካደ ሄደ ..😭

ከ1945 - 2016 ...

ሙሉቀን በ1960ና 70ዎቹ ብዙዎች በኢትዮጵያ ወርቃማ በሚባለው የሙዚቃ ዘመን፣ ቁንጮ ከነበሩት መካከል ነዉ ይሉታል። ኋላ ላይም ወደ ጌታ #ኢየሱስ መጥቷል።

ሙሉቀን በ1945 ዓ.ም በጎጃም ክፍለ ሃገር ተወለደ። በልዩ ተሰጦው ምክንያት በ12 አመቱ ሙዚቃን የጀመረው ሙሉቀን፣ በለጋ እድሜው ነበረ በመሸታ ቤቶች ውስጥ “እናቴ ስትወልደኝ መች አማከረችኝ” በሚለው ሙዚቃ የጀመረው።

ሙሉቀን የዘፈኑ አለም በቃኝ ብሎ ወደ ጌታ ከመጣበት 1970ዎቹ ማገባደጃ አካባቢ ጀምሮ በዝማሬ ማገልገሉን ቀጥሏል። በየጊዜው የቀድሞ የዘፈን ወዳጆቹ የእንዝፈን ግብዣ ቢቀርብለትም፣ አሻፈረኝ ብሎ ቀጥሎበታል።

ህመሙ በጠናበት ጊዜም እነ ታማኝ በየነ ልህክምና ወጪ የዘፈን ድግስ እናዘጋጅ ሲሉትም በኔ ስም አይዘፈንም ብሎ በቅድስና የኖረ ጀግና ክርስቲያን ነው።

ሙሉቀን ወደ ክርስቲያኖች ካደረሳቸው መዝሙሮች መካከል “ስለ ውለታህ”፣ አድራሻ ቢስ ሆኜ በዓለም ውስጥ ስጨነቅ”፣ “ሃሌሉያ”፣ “አቤኔዜር” እና ሌሎችንም መዝሙሮችን ከሃሌሉያ አልበሙ አስመቶናል።

በአንድ ወቅት ጋዜጠኛ መታሰቢያ በEBS Tv ላይ "ከኢትዮጵያ ከወጣህ 38 ዓመት ሆኖሃል አትናፍቅህም?" የሚል ጥያቄ ብትሰነዝርለትም ሙሉቀን መለሠ ግን አትናፍቀኝም! ... ኢየሱስን ማየት ነው የናፈቀኝ ማለቱ የቅርብ ዓመች ትዝታ ነዉ።

#ዘማሪ #ሙሉ #ቀን ኑሮውን በአሜሪካን ሃገር ዋሽንግተን ዲሲ ከባለቤቱ ጋር አድርጎ በኖረበት በ71 ዓመቱ ወደ ሚወደውና ወዳገለገለው #ጌታ ሄዷል።

በነገራችን #ላይ ሙሉቀን መለሰ በዓለም የሙዚቃ ስራ ዉስጥ ለ14ዓመት ብቻ ከ13 ዓመቱ እስከ 27ዓመቱ ብቻ ነዉ የቆየው ዘፈን አቁሞ ወደ ጌታ ከመጣ ደግሞ 43 አመታትን አስቆጥሯል።

ከበርካታ ዝማሬዎቹ መካከል
አለም ተስፋ ቁረጭ አልተገናኘንም
አምላክ ከእኔ ጋር ነው አታሸንፊኝም

እንዲሁም
ከኢየሱስ ጋራ ሲሄዱ
ከጌታ ጋራ ሲሄዱ
እንዴት ያምራል ጎዳናዉ
እንዴት ያምራል መንገዱ

በብዙዎች ዘንድ የሚታወቀዉ
የኢየሱስ ወታደር ነኝ
የኢየሱስ ወታደር ነኝ
እዋጋለሁኝ አልሽነፍም
ለጠላት እጅን አልስጥም

የሚሉት ተጠቃሽ ናቸዉ ...

ለሙሉቀን መለሰ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶች The Christian News - የክርስቲያን ዜና በድጋሜ መጽናናትን ይመኛል።
#አፍሪካ

አፍሪካ ባለፉት 150 አመታት በርካታ ክርስቲያናት ያሉባት አህጉር ሆናለች።

በ1900 #ላይ በአለም ካለው #ክርስቲያን 82 በመቶው፣ በሰሜን የአለም ክፍል፣ አውሮፓ እና #አሜሪካ ይገኝ ነበረ። በተቃራኒው ደቡባዊ የአለም ክፍል አፍሪካ፣ እስያና ላቲን አሜሪካ ደግሞ 18 በመቶ ብቻ ነበረ።

#አንድ #መቶ አመታትን #ወደ ፊት፣ ሰሜኑ አለም 33 በመቶው #ብቻ ክርስቲያን ሲሆን፣ ደቡቡ የአለም ክፍል ደግሞ 67 በመቶ ክርስቲያን ነው።

በጋና አክራ፣ በተካሄደ አለም አቀፍ የክርስቲያኖች ፎረም፣ በአለም ላይ የክርስትና ህዝብ ነክ ቁጥር ትልቅ ለውጥ ማሳየቱ ተነስቷል። ከኤፕሪል 16-20 በነበረው በዚህ ፎረም ከ60 የተለያዩ ሃገራት የተወጣጡ ከ240 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

በዚህ ለውጥ ውስጥ ሴቶች ያላቸው ሚና እጅግ ታላቅ ነው ተብሏል። ወደፊት በተቀመጠ ትንበያ መሰረት ደግሞ በ2050፣ 77 በመቶ ክርስቲያኖች በደቡቡ የአለም ክፍል የሚኖሩ ይሆናል።

እነዚህ የአሃዝ ለውጦችና ትንበያዎች ወደፊት የክርስትና ማዕከል የትኛው የአለም ክፍል እንደሚሆን ያሳያል ተብሏል።

ለአብነት በአውሮፓና አሜሪካ የክርስትና ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ ሲሆን፣ በተቃራኒው በአፍሪካና እስያ ደግሞ በፍጥነት እያደገ
የትንሳዔ በዓልን የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በድሬዳዋ ዓለም ዓቀፍ ስታዲየም በተለያየ የአምልኮ ስርዓት አከበሩ።

በዛሬው የትንሳዔ በአል በድሬዳዋ ዓለም ዓቀፍ ስታዲየም ሲከበር የድሬዳዋ አስተዳደር #ከንቲባ ክቡር ከዲር ጁሀርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ በርካታ የወንጌላዉያን ዕምነት ተከታዮችና የሀይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።

በድሬዳዋ ዓለም አቀፍ ስታዲየም የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት በተዘጋጀው የትንሳኤ በዓል አከባበር ላይ የክብር እንግዳ የነበሩት የአስተዳደሩ ከንቲባ ክቡር ከድር ጁሀር በዓሉን ስናከብር ትላንት የነበሩ ዛሬ ያልነበሩ ወገኖቻችን ቤተ ዘመዶችን ከጎናቸው በመቆምና የተቸገሩትን ደግሞ በመደገፍ መሆን እንዳለበት አስገንዝበው ለመላው ክርስትና ዕምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በፕሮግራሙ #ላይ የድሬዳዋ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ዋና ሰብሳቢ መጋቢ ሚኪያስ ታዬ የዛሬው የትንሳዔ በዓል አከባበር ዝግጅት መሳካት የድሬዳዋ አስተዳደር ላደገላቸዉ ትብብር ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቀርበዋል።

የድሬዳዋ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ ምክትል ሰብሳቢ ሊቀ ብርሀናት ቀለመ ወርቅ ቢምረው በዛሬው የትንሳኤ በዓል ዲያቢሎስ የታሠረበት፣ ሀጢያት የተሻረበት እንዲሁም ብዙዎች ነጻ የወጡበት በመሆኑ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

የዛሬው #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የትንሣኤ በዓል ዝግጅት ለስኬት እንዲበቃ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም የዕውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቷል።

ጁሌት ተድላ ለድሬ ቲቪ እንደዘገበዉ
ካሜራ:- ምንተስኖት ደረጀ

https://youtu.be/tOWD7qwfcDo
#ጅማ ክርስቲያን

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖ ካምፓስ የቀድሞ የ#ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረት (ኪቶ ፋሚሉ) አባል የነበሩ ተማሪዎች መልካም ግንኙነት ሊያስቀጥል የሚችል ክርስቲያን ኔትወርኪንግ ኢቨንት ተካሄደ።

#ይህ ለሁለተኛ #ጊዜ የተዘጋጀው ፕሮግራም በዋናነት ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ወጥተው በተለያዩ የግል የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ተማሪዎችን ግንኙነት ማስቀጠል #እና የተሰማሩበትን የቢዝነስ ዘርፍ አስተዋውቀው #መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም አቤኔዜር ማቴዎስ ለክርስቲያን ዜና ተናግሯል።

አቤኒዘር አክሎ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ አብዛኛውን ጊዜ ግንኙነቱ ሲቀጥል አይታይም ይህን ክፍተት ለመቀነስ ያሰበ መልካም ግንኙነት እንደሆነ ተናግሯል።

ይህ ሕብረት በቀጣይ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ውጪ የሚገኙ ሕብረትን ለማሳደግ እንደሚሰሩ ወጣት አቤኔዜር አክሎ ለክርስቲያን ዜና ተናግሯል።

ክርስቲያን #ዜና ያናገራቸው በፕሮግራሙ #ላይ የሚሰሩትን የተለያዩ ስራዎችን ይዘው የቀረቡ የቀድሞ ተማሪዎች ይህ የህብረት ፕሮግራም ከሌሎች ጋር የመተዋወቅን እና የቢዝነስ ስራ በጋራ ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ነግረውናል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዘገባውን አዘጋጀን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በክርስቲያን ዜና የዮቲዩብ ቻናል ይዘን እንመለሳለን።
በመቱ የሙሉ #ወንጌል አማኞች #ላይ ደረሰ የተባለው ድብደባ እንዲጣራ የአብያተ ክርስቲያናት ኅብረቱ ጠየቀ።

#እሁድ ግንቦት 25 በመቱ ከተማ ለወንጌል ስርጭት በወጡ ክርስቲያኖች ላይ በፖሊስ እና ሚሊሻዎች ድብደባ ተፈጽሟል። ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው ወገኖች መካከል አስተያቷን ለአሜሪካ ድምጽ ራድዮ የሰጠችው ኤደን ግርማ እንዲህ ብላለች።

ኤደን ግርማ፣ ጥቃት የደረሰባት “የእሁድ አምልኮ ጨርሰን ለወንጌል ስርጭት ሶሪ ዳቦ የሚባልበት አካባቢ ስንደርስ ፖሊሶችና ሚልሻዎች በመኪና መጡ። መሬት ላይ ተቀመጡ ካሉ በኋላ፣ የተወሰኑ ወጣቶች ወደ ፖሊስ ጣብያ ወሰዱን።

አመሻሽ ላይ ከአንዱ አመራር ጋር ፖሊስ ጣብያው አካባቢ መሬት ተቀመጡ ብሎ እያወራን፣ ፖሊሶችና ሚሊሻዎች ድብደባ ጀመሩ። እኔ ጭንቅላቴን ተመቼ ስደማ፣ ሌሎችም በጣም ተጎድተው ወደ ሆስፒታል ለህክምና ተወስደናል።” ስትል ተናግራለች።

#ቄስ ደበላ ያደታ፣ የኢሉባቦር ዞን ወንጌላዊያን አብያተ ክርስትያናት ህብረት ሰብሳቢ በበኩላቸው “እኛ ህገ መንግስቱ በሚሰጠን መብት መሰረት እምነታችንን የማካሄድ መብት አለን። ከመንግስት ጋርም በሚያስፈልጉ ነገሮች ዙርያ በትብብር ስንሰራ ቆይተናል። መንግስት እንደዚህ ያደርጋል የሚል እምነት ባይኖረንም፣ የመንግስት መዋቅር ውስጥ ያሉ ሰዎች ግን ይሄንን እንዳደረሱ በትክክል እናውቃለን። ስለዚህ ሁኔታው በትክክል እንዲታራ እንጠይቃለን።” ብለዋል።

አቶ ተሻለ ኤጄርሶ፣ የመቱ ከተማ ከንቲባ በበኩላቸው “ከሳምንት በፊት ለነበረው ስብከተ ወንጌል ፍቃድ የተሰጠ ቢሆንም፣ እሁድ ግንቦት 18 ሲደረግ ለነበረው የወንጌል ስርጭት የተሰጠ ፍቃድ የለም። አላስፈላጊ ድብደባና ግጭት ከፖሊስ ዘንድ መድረሱን ተመልክተናል። ከጸጥታ አካላት ጋርም ይሄንኑ ጉዳይ በተመለከተ ምርመራ እየተካሄደ ነው።”

VOA Amharic
#የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ #ኢየሱስ #ቤተክርስቲያን የማዕከላዊ #ደቡብ #ኢትዮጵያ ሲኖዶስ የልማት ኮሚሽን ፤ ኖሮዌ #ቤተክርስቲያን ተራዕዶ እና UN #women በጋር የሚተገብሩት Creating safe #city #and safe #public #space #project ጾታን መስረት ያደረገን ጥቃት ለመከላከል የሚስችል የግንዛቤ ማሳጨበጫ ፕሮግራም በሀዋሳ #ከተማ አካሄድ፡፡

በፕሮግራሙ #ላይ ከካቶሊክ ፤ ከወንጌል አማኞች #እና ከግሮት ኮሚሽን የተወጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

ጾታዊ ጥቃት/በሴቶችና ልጃገረዶች የሚደርሰውን ጥቃት የሚፅየፍ ትወልድ መፍጠር የሚል አላማ የነበረው ፕሮግራም እንደሆነ ተገልጿል።

በፕሮግራሙ ከአቶቴ #እስከ ታቦር መካነ #ኢየሱስ ቤ/ክ ድረስ የእግር ጉዞ የተደረገ ሲሆን በጉዞ ወቅት ተሳታፊዎች የተለያዩ የጹሁፍና የድምፅ መልዕክቶችን በማሰማት በሴቶችንና ልጃገረዶች #ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አውግዘዋል፡፡

በተጨማሪም በግሬት ኮሚሽንና በሪፍራል መካነየሱስ ወንድ ወጣቶች #መካከል የእግር ኩዋስ #ውድድር የተካሄድ ሲሆን የውድድሩ አላማ ወንዶች ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ነው።

ይህም ጥቃት የሚያደርስ ወንድ #ብቻ ሳይሆን የሚቃውም መሆኑን በማሳየት ተሳትፎቸውን ለመጨመር ነው፡፡