The Christian News
5.15K subscribers
3.04K photos
25 videos
714 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#መጋቢ ጻዲቁ አብዶ እና መጋቢ እና #ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ

የዛሬ አመት ልክ በዚህ ሰዓት ቀጠና #ሁለት #ሙሉ #ወንጌልል #ቤተክርስቲያን በነበረው መረሃ ግብር #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት #ፕሬዝደንት መጋቢ ጻዲቁ አብዶ ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በተለይም ምዕመናንን ከስህተት ትምህርት በመጠበቅ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልዩ ተሸላሚ በማለት ከልጅነት እስካሁን ድረስ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ውስጥ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች እውነተኛውን ትምህርት በማስተማር ለአገልጋዮች በስደት ውስጥ እና በመከራ #ውስጥ ጸንተው በረሃብ በእጦት ሳይሸነፉ ምሳሌ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ እና የኖሩ በሚል #ልዩ ተሸላሚ አድርጋ እውቅና ሰጥታ ነበር።

በተመሳሳይ #ዘመን ተሻጋሪ ፤ ገሳጭ ፤ መካሪ ፤ አጽናኝ እና #ክርስቶስ ተኮር በሆኑ ሰማይ ተኮር #ህይወት ህይወት በሚሸቱ ዝማሬዎቻቸው የሚታወቁት መጋቢ እና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ እውቅና የዘጠችው ልክ በዚህ በያዝነው ሳምንት ነበር።

በሁሉም አብያተክርስቲያናት ዘንድ #እጅግ ተወዳጅ እንዲሁም ትውልድን እንደ ድልድይ በመሆን በማገናኘት በትሁትነታቸው የሚታወቁት መጋቢ እና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ የሙሉ ወንጌል ብቻ ሳይሆን የአብያተክርስቲያናት ሁሉ እንቁ ሃብት የሆኑ ሰው ናቸው።

#እግዚአብሔር ብሄር የሰጣቸው ዝማሬዎች ዘመን ተሻጋሪ እና ልብን እና ህይወትን አዳሾች ሲሆኑ በተጨማሪ በማስተማር እና በማሰልጠን ይታወቃሉ።

ይህ ከሆነ እነሆ አንድ አመት ሆነው። #እነዚህ #ሁለት መሪዎች ዛሬም ድረስ #ለኢትዮጵያ #ቤተክርስቲያን ስጦታዎቻችን ናቸው። ስለ እነርሱ እግዚአብሔርን ዘውትር እያመሰገንን #ይህ ትውልድ ዛሬም ብዙ ነገሮችን እነዚህን ከመሰሉ መሪዎች እንደሚማር እምነት አለን።

#ቀሪ #ዘመናቸው #የተባረከ #ይሁን
#አሳዛኝ #ዜና

በአሜሪካ አንዲት እናት #ክርስቶስ #ወደ ምድር በቶሎ ለፍርድ እንዲመጣ በሚል #ሁለት ልጆቿን ገደለች።

በዩናይትድ ስቴትስ የምትኖር አንዲት እናት በአፖካሊፕቲክ ሃይማኖታዊ እምነቷ መሰረት ሁለት ልጆቿን በመግደል እና የባሏን የቀድሞ ሚስት ለመግደል በማሴር የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባታል።

ሎሪ ቫሎው የተባለችዉ ይህችዉ #ሴት በግንቦት ወር የ16 ዓመቷን ሴት ልጇን ታይሊ ራያን እና የሰባት ዓመት በማደጎ የወሰደችዉን #ወንድ ልጇን ኢያሱ "ጄጄ" ቫሎውን በመግደል ጥፋተኛ ተብላለች፡፡

የእናታችን ኃጢአት (Sins of Our Mother) በሚል የዚህችዉ ሴት የህይወት #ታሪክ በኔትፍሊክስ እውነተኛ የወንጀል ዘጋቢ #ፊልም የቀረበ ሲሆን የኢየሱስ ክርስቶስን ዳግም ምጽዓት እንዲሆን ልጆቿን መግደሏ ከአምላክ የተሰጠ ራዕይ መሆኑን ትናገራለች፡፡

ዳኛ ስቲቨን ደብሊው ቦይስ በቫሎው የወንጀል ድርጊት ላይ ባሳለፉት የጥፋተኛነት ዉሳኔ በሶስት ተከታታይ የእድሜ ልክ እስራት በይነዋል፡፡ በወላጅ የተፈጸመውን የልጅ ግድያ “በእርግጥ መገመት ከምችለው በላይ አስደንጋጭ ነገር” ሲሉ ዳኛዉ ገልጸዋል።

ቫሎው ልጆቿን ከገደለች በኃላ #እንኳን እንደጠፉ ገልጻ ባታዉቅም በፖሊስ አስክሬናቸዉ ተገኝቷል፡፡

#ዳጉ_ጆርናል
#ስላማችሁን #ጠብቁ መጋቢ ደሳለኝ አበበ

#Ethiopiaየመሠረተ #ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን የወጣቶች አገልግሎት ክፍል ከፖይሜን ሚኒስትሪ #ጋር በመተባበር #ሠላም_ለወጣቶች_ወጣቶች_ለሠላም በሚል መሪ ሀሳብ ከሁሉም የሐገርቷ #ክፍል ከተውጣጡ የአሰልጣኞች ሥልጠና ለ41 #ወጣቶች #በኢትዮጵያ የሠላም ግንባታ ዙሪያ ሥልጠና እና ውይይት በቢሾፍቱ #ከተማ እያካሄዱ ይገኛል።

በመድረኩ የቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት መጋቢ ደሣለኝ አበበ #ሠላማችሁን ጠብቁ በማለት ወጣቶቹን አበረታተዋል።

#ሠላም_ነጣቂ_እንጂ_ጠባቅ_አጥታላች ያሉት ፕሬዝዳንቱ የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በበኩሏ በኢትዮጵያ እየተከሰተ ካለው የልዩነት ዘመቻ በተቃራኒ በመቆም ሁሉም ከጥላቻ ፣ ከወቃሽነትና ነቃሽነት ተራ ወጥቶ የሠላም ሰባኪ እንዲሆን በአጽንኦት ተናግሯል።

ውይይቱ #ነገ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።
በርግጥ ወንጌላውያን #በዚህ ደረጃ ፍትሕ ተጓድሎባቸዋል ?

#ይህንን #ጥያቄ #ለምን በተደጋጋሚ ማንሳት አስፈለገ ?

ሁላችሁም መልሱን አዘጋጁ #እኛ #ግን የራሳችንን ሃሳብ እንሰነዝራለን።

በትላንትናዉ ዕለት #የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል በወንጌላዊያን አማኞች እና አብያተክርስቲናት ላይ እየደረሰ ስላለዉ ፍትህ መጓደል ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ #መግለጫ ሰጥቷል።

በካውንስሉ ጠቅላይ ጽሐፊ አማካኝነት በተሰጠዉ መግለጫ #ላይ በዋናነት ከ 6 በላይ .. የሆኑ (የደረሱ የፍትሕ መጓደል) የሚያሳዩ ነጥቦች ተጠቅሰዋል።

1. በደርግ #ዘመን የተወረሱ የቤተክርስቲያን ይዞታዎች በኢሕአዴግ ዘመን በከፊል ቢመለሱም እስካሁን ያልተመለሱ የኦሎምፒያ መሰረተ #ክርስቶስ ፣ የአዲስ ከተማ ገነት፣ የኢትዮጵያ ወንንጌላዊት #ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ብረት የሆነው የጉድ ሼፐርድ ማዕከል ፣ቄራ አካባቢ ያለው የብርሃነ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ፣እና ሌሎች እስካሁን ያልተመለሱ ይዞታዎች ሲሆኑ እነዚህ ይዞታዎች የቤተክርስቲያን ንብረት በመሆናቸዉ እንዲመለሱ ተጠይቋል።

2 የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን #በአንድ ወር #ጊዜ ዉስጥ ይዞታዋን ለቃ እንድትነሳ የከተማዉ አስተዳደር የወሰንኑ ቢሆንም የከተማዉ አስተዳደር እና የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እንዲሁም የካውንስሉ አመራሮች ሰፊ ዉይይት አድርገዉ የከተማዉ አስተዳደር ጉዳዩን እየመከረበት ይገኛል። የከተማዉ አስተዳደር የደረሰበትን ደረጃ በአጭር ጊዜ ግልፅ እንዲያደርግ ተጠይቋል።

3 የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ይዞታ ነጥቆ የራሱ ጽህፈት #ቤት አድርጎት ይገኛል። እንዲሁም የቃለ #ህይወት ቤተክርስቲያን ይዞታ የሆነዉን የኩሪፍቱ የጸሎት ማዕከል በተመለከተም በማእከሉ #ምንም አይነት የልማት #ስራ ቤተ ክርስቲያን እንዳታከናወን በማገድ የቤተክርስቲያኑን ይዞታ ለመንጠቅ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝኝ ተገልጾ የቢሾፍቱ #ከተማ አስተዳደር ከዚህ ህገወጥ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እና የወሰደዉን የቤተክርስቲያን ንብረት እንዲመልስ ተጠይቋል።

4. በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው የሸገር ከተማም የፈረሱ የወንጌላዊያን የእምነት ተቋማት ይዞታቸዉ እንዲመለስ እንዲሁም በከተማዋ ለ23 አብያተክርስቲያናት ከካቢኔ #ቦታ ተወስኖላቸዉ ቦታቸዉን መረከብ ላልቻሉ በአፋጣኝ ካቢኔ የወሰነዉ ዉሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ተጠይቋል።

5 የመቃብር ስፍራን ጥሶ በመግባት እየተደረገ የሚገኘዉ አግባብ ያልሆነ ተግባር በአስቸኳይ እንዲቆም

6 በምዕራብ ኢትዮጵያ በቄለም ወለጋ ዞን በጊዳሜ ወረዳ ዘጠኝ ምእመናንን የአምልኮ ስነስርአት እየፈፀሙ ካሉበት ሌሊት ላይ ተወስደዉ መረሸናችው #እጅግ #አሳዛኝ እንደሆነና ለነዚህ ንፁሃን ፍትህ እንዲሰጥ ተጠይቋል።

በአጠቃላይ #ይህ #ሁሉ እየሆነ ያለዉ የታችኛዉ የመንግስት አካል የመንግስትን ስልጣን በመጠቀም ጥቂት ግለሰቦች የግል አጀንዳ ይዘዉ የሚፈፅሙት ተግባር ነዉ።

የፌደራል መንግስት ጣልቃ በመግባት ፍትህ ሊያሰፍን ይገባል ሲል የኢትዮዽያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት #ካዉንስል በመግለጫዉ አስታዉቋል።

#ታዲያ ይህ ሁሉ የፍትህ ጥያቄ አለ #ማለት መጀመሪያላይ ለጠየኩት ጥያቄ ትክክለኛ ምላሽ በርግጥም ወንጌላውያን በግልፅ በአደባባይ #ፍትሕ ተነፍገዋል የሚል ነዉ።

ይሄንን ጥያቄ በዚህ ሰዓት ለምን ማንሳት አስፈለገ ከተባለ ደግሞ ከዚህ በፊት ለበርካታ አመታት ምላሽ ያላገኙ እና ፍትህ ያልተሰጣቸው ጥያቄዎች ባለበት ዛሬም ሌላ በደል እየደረሰ ስለሆነ ማንሳት አስፈላጊ ነዉ።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና የወንጌላውያን ድምፅ በመሆን ለበርካታ ጊዜያት ሲያገለግል ቆይቷል። አሁንም ገና ለቤተክርስቲያን ፍትህ ካልተሰጠ በስተቀር ጥያቄያችንን ማስተጋባታችን ይቀጥላል።

ፍትሕ ለወንጌላዉያን ቤተክርስቲያን
#መሰረተ #ክርስቶስ #ታላቅ የሕብረት #ጊዜ ላይ ናቸዉ

በአዲስ አበባ እና አከባቢው የሚገኙ የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪዎች እና ምዕመናን #ሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን በመዝጋት በጋራ በምስራቅ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን እያመለኩ ይገኛል።

መረሃ ግብሩ "በሕይወት ታድሶ በህብረት ፀንቶ ወደ ፍፃሜዉ መገስገስ" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ ይገኛል።

በመሰናዶዉ በአዲስ አበባ በ11ዱም ክፍለ ከተማ የሚገኙ ሙሉ ምዕመናን እየተካፈሉ ይገኛል።
... “ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።” ...

— ማቴዎስ 25፥43

የመሠረተ #ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት የኤጄሬ ማረሚያ ቤትን ጎበኙ።

በቤተክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት መጋቢ ደሣለኝ አበበ የተመራ የልዑካን ቡድን #ዛሬ ጠዋት በምዕራብ ሸዋ የኤጄሬ ወረዳ ማረሚያ ቤትን ተጎብኝቷል ።

የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የሕግ ታራሚዎች አገልግሎት መምሪያ ላለፉት 14 ዓመታት የእንጨት መሰንጠቂያ መሣሪያ ፣የብሎኬት ማምረቻ ማሽን እንዲሁም ለመስኖ ሥራ የሚሆን የውሃ ፓምፕ ማሽኖችን በመግዛት እና በማሰልጠን የሕግ ታራሚዎች የሞያ ባለቤት እንዲሆኑ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ይገኛል ።

ከሁለት ዓመት ወዲህ #ደግሞ #የሰላም ግንባታ እና የእርቅ አገልግሎት ሥልጠና በመስጠት ሰዎች በሠላም አብሮ እንዲኖሩ ታራሚዎች ከባላኔጣዎቻቸው ጋር ጠባቸውን በእርቅ እንዲጨርሱ ከፍተኛ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።

የዛሬው ጉብኝት እስከ ዛሬ እየተሰሩ ያሉትን ማህበራዊና መንፈሳዊ ሥራዎችን በማየት ለቀጣይነት ለማበረታታት የተሰበ ቢሆንም እግረመንገዳቸውን 250 ለሚሆኑ ታራሚዎች መጽሐፍ ቅዱሳትን በነጻ አከፋፍለዋል።

በተጨማሪም የማረሚያ ጊዜያቸውን ጨርሰው በወጡ የቀድሞ የሕግ ታራሚዎች አማካኝነት የተተከለችውን የሆራ ቆታ የወንጌል ሥርጭት ጣቢያ ተጎብኝቷል ።
152 #ሰዎች ተጠመቁ!!!

#በመሠረተ #ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን 152 ሰዎች የውሃ ጥምቀት ወስደው #ወደ ቤተክርስቲያን ተቀላቀሉ ።

ቦሰት አካባቢ 62 ሰዎች እና በመካከለኛው ሥምጥ ሸለቆ ዝዋይ አጥቢያ አማካኝነት ደግሞ 90 ሰዎች በአጠቃላይ 152 ወገኖች በዛሬው ዕለት የውሃ ጥምቀት ወስደው ወደ ቤተክርስቲያን ተቀላቅለዋል ።

በተጨማሪም #ነገ ዕለት በደቡብ አዳማ ክልል ሌሎች 40 ሰዎች የውሃ ጥምቀት እንደሚወስዱ ይጠበቃል።

በአጠቃላይ በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን "#አጀንዳ28 19" ወይም "#አጀንዳችን_ወንጌል" የሚለውን እንደ መራህ በመከተል በዓመት እያንዳንዱ አጥቢያ በቁጥር 10% እድገት እንዲያሳዩ በተቀመጠው አቅጣጫ አካል መሆኑ ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የኮሚኒኬሽን ቢሮ አሳውቋል።

#ወንጌል ካልሰራን #ምንም አልሰራንም።
#ክርስቶስ እንኳን #ወደ ምድር ቢወርድ #አንድ አዳራሽ መስሪያ ቦታ አይሰጣችሁም

#ክርስቲያኖች ላይ ስደት በዝቷል።

በደቡብ ምስራቅ አውሮፓ በምትገኘው ኮሶቮ፣ ክርስቲያኖች #ላይ ስደት በርትቷል ተባለ።

በሃገሪቱ ክርስቲያኖች #ምንም አይነት የመሰብሰብ መብት እንደሌላቸው #እና ፈቃድ ለማግኘትም ሁኔታዎች እንደሚወሳሰቡባቸው ገልጸዋል።

የአርሜ #ቋንቋ ተናጋሪዎች የሚበዙባት ኮሶቮ፣ 93 በመቶ ዜጎቿ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው።

ምንም #እንኳን የሃገሪቱ ህገ መንግስት የሃይማኖት ነጻነትን የሚፈቅድ ቢሆንም፣ ክርስቲያኖች ላይ ግን መድሎና አመጽ ይበረታባቸዋል።

#ይህ ስደት በግል ደረጃም፣ የቀብር ስፍራ መከልከል፣ ንብረት የማፍራት መብት አለማግኘትና ሌሎችም በደሎች እየደረሱባቸው እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በተለይ #ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች፣ የባንክ ሂሳብ መክፈት፣ ንብረት ማፍራት እና ሰራተኞችን ቀጥሮ የመንቀሳቀስ ዴሞክራሲያዊ መብቶች የላቸውም።

በቅርቡ የወጣ #አንድ ህግ ደግሞ የሰርቢያ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊኮችን እና ሌሎችንም ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናትን ኢላማ ያደረገ ነው ይባልለታል።

በሃገሪቱ ያለፉትን 25 ዓመታት ያገለገሉ አንድ ቄስ ሲናገሩ፣ ያለው ስቃይ በግልጽ ስላልሆነ ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ብለዋል።

ለቀብር እንኳን በሙስሊሞች የቀብር ስፍራ፣ በኢማሞች የተመራ ቀብር ስነ ስርዓት እያደርግን ነው የምንገኘው ብለዋል። ምንም ቢሆን #ግን ለሃገራችን የወንጌል ተስፋ አለን ሲሉም እኚሁ ቄስ ይናገራሉ።

በኮሶቮ በ1980ዎቹ ወንጌላዊያን፣ ክርስቶስ እንኳን ወደ ምድር ቢወርድ አንድ አዳራሽ መስሪያ ቦታ አይሰጣችሁም የሚል ተደጋጋሚ ዛቻ ከወቅቱ ኮሚኒስት መንግስት ሲደርስባቸው እንደ ነበረ ዘገባዉ አስታዉሷል።