The Christian News
5.15K subscribers
3.04K photos
25 videos
715 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#መጋቢ ጻዲቁ አብዶ እና መጋቢ እና #ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ

የዛሬ አመት ልክ በዚህ ሰዓት ቀጠና #ሁለት #ሙሉ #ወንጌልል #ቤተክርስቲያን በነበረው መረሃ ግብር #የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት #ፕሬዝደንት መጋቢ ጻዲቁ አብዶ ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በተለይም ምዕመናንን ከስህተት ትምህርት በመጠበቅ ላበረከቱት አስተዋጽኦ ልዩ ተሸላሚ በማለት ከልጅነት እስካሁን ድረስ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ውስጥ በተለያዩ የሃገራችን ክፍሎች እውነተኛውን ትምህርት በማስተማር ለአገልጋዮች በስደት ውስጥ እና በመከራ #ውስጥ ጸንተው በረሃብ በእጦት ሳይሸነፉ ምሳሌ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ እና የኖሩ በሚል #ልዩ ተሸላሚ አድርጋ እውቅና ሰጥታ ነበር።

በተመሳሳይ #ዘመን ተሻጋሪ ፤ ገሳጭ ፤ መካሪ ፤ አጽናኝ እና #ክርስቶስ ተኮር በሆኑ ሰማይ ተኮር #ህይወት ህይወት በሚሸቱ ዝማሬዎቻቸው የሚታወቁት መጋቢ እና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ እውቅና የዘጠችው ልክ በዚህ በያዝነው ሳምንት ነበር።

በሁሉም አብያተክርስቲያናት ዘንድ #እጅግ ተወዳጅ እንዲሁም ትውልድን እንደ ድልድይ በመሆን በማገናኘት በትሁትነታቸው የሚታወቁት መጋቢ እና ዘማሪ ተስፋዬ ጋቢሶ የሙሉ ወንጌል ብቻ ሳይሆን የአብያተክርስቲያናት ሁሉ እንቁ ሃብት የሆኑ ሰው ናቸው።

#እግዚአብሔር ብሄር የሰጣቸው ዝማሬዎች ዘመን ተሻጋሪ እና ልብን እና ህይወትን አዳሾች ሲሆኑ በተጨማሪ በማስተማር እና በማሰልጠን ይታወቃሉ።

ይህ ከሆነ እነሆ አንድ አመት ሆነው። #እነዚህ #ሁለት መሪዎች ዛሬም ድረስ #ለኢትዮጵያ #ቤተክርስቲያን ስጦታዎቻችን ናቸው። ስለ እነርሱ እግዚአብሔርን ዘውትር እያመሰገንን #ይህ ትውልድ ዛሬም ብዙ ነገሮችን እነዚህን ከመሰሉ መሪዎች እንደሚማር እምነት አለን።

#ቀሪ #ዘመናቸው #የተባረከ #ይሁን