The Christian News
5.32K subscribers
3.06K photos
27 videos
720 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
ውድ የክርስቲያን ዜና አድማጭ ተመልካቾቻችን እንደምን አላችሁልን!!! ዛሬ በማለዳ ኢየሱስ ነን ብለው የተነሱ ሀሰተኞችን በተመለከተ ያልተሰማ መረጃ ይዘንላቹ መጥተናል። መረጃውን ከተመለከታችሁ በኋላ ሀሳብ አስተያየታችሁን ኮመንት ላይ አስፍሩልን። ሙሉ መረጃዎቹን ለመመልከት ሊንኩን ይጫኑ!!! https://youtu.be/9at6AC1kRoM
#ሁሉም #ሊያነበው #የሚገባ #አስቸኳይ #መልዕክት
#እንዴት #ድንቅ #አምላክ #ነው #እኛ #የምናመልከው..

ለ5 #ሰከንድ #ኦክሲጅን ከአለም ላይ ቢጠፋ ምን ይፈጠራል?

ግራቪቲ (የመሬት ስበት) ለ5ሰከንድ ከመሬት ላይ ቢጠፋስ ምን የሚፈጠር ይመስላችኋል? እኛ ሰዎች ምንድነው የምንሆነው?

ምናልባት ደግሞ #አሁን ያለውን የመሬት ስበት እጥፍ ቢሆን ምን ይፈጠራል?

ሌላኛው ለሰው ልጆች #ሁሉ ጠቃሚ የሆነችው ጸሃይ ድንገት ብትጠፋ ... ቀጥሎ የምድራችን እና #የሰው #ልጆች እጣ ፈንታ ምንድነው? በነገራችን ላይ ይህን #ሁሉ ለ5 ሰከንድ #ብቻ ነው።

እነዚህን ጥያቄዎች የሞኝ ጥያቄዎች ይመስላሉ?

#እኔም ለመጀመሪያ #ጊዜ ስሰማቸው እንደዛ ነው ያሰብኩት ነገር ግን #እጅግ መሰረታዊ እንደሆነ የተመለከትኩበትን አንድ ነገር ላካፍላችሁ።

ከጥቂት ቀናት በፊት TechTalk With Solomon በተሰኘ ፕሮግራም #EBS #ቴሌቪዥን ላይ ማለት ነው። ሰለሞን እነዚህ ጥያቄዎች እየጠየቀ ነበር።

ከጥያቄዎች በሻገር ምን ሊፈጠር ይችላል የሚለውን ምናባዊ ምልከታ በሳይንስ አስደግፎ በ2 ተከታታይ ክፍሎች ለተመልካች አቅርቦታል። ለማንኛውም እኔ ያንን ፕሮግራም ስሰማው እጅግ እየዘገነነኝ እና እየተሳቀኩኝ ነበር።

በኋላ #ላይ #ግን ቆም ብዬ ሳስበው እንደዚህ አይነት ፕሮግርሞች ሊበረታቱ የሚገቡ እንደሆነ ገባኝ።

ምክንያቱም እሱ የሚዘረዝራቸው በሙሉ ለ5 ሰከንድ ቢፈጠሩ ምድራችን ላይ የሚፈጠሩት እጅግ ዘግናኝ እልቂቶች እና ነገሮችን ለማስቀረት የሚያስችል አንዳችም ቴክኖሎጂ እስካሁን #በሰው #ልጆች አልተፈጠሩም።

ይህንን ሳስብ እኛ የምናመልከት አምላክ እንዴት #ድንቅ እንደሆነ እና ምድርን #በቃሉ አጽንቶ እና እያንዳንዱ እንቅስቃሴ ያለ አንዳች መፋለስ #ሁሉም ነገር ስረዓታቸው ይዘው እንደሚሄዱ ሳሰብ ደነቀኝ።

ምድር ትንሽ ከሚባሉት ፕላኔቶች መካከል አንዷ ነች። ጸሃይ ደግሞ የምድርን 6ሚሊዮን አከባቢ እጥፍ የሆነች ከግዙፎቹ #መካከል ነች። ታዲያ የጸሃይ ብረሃን እንኳን በልካችን ተመጥኖ የሚደርሰን ለማሰብ የሚከብድ ምን አይነት ጥበብ ነው?

የሰው ልጅ ምናልባትም እየተማረ እና ብዙ እውቀቶችን እየሰበሰብ ሲሄድ ይበልጥ ወደ #አምላኩ እንደሚቀርብ አምናለሁ።

ለማንኛውም እኔ ከምጽፍላችሁ ይልቅ ፕሮግራሙን ገብታችሁ እንድትመለከቱት ሊንኩን አስቀምጬላችኋለሁ። https://www.youtube.com/watch?v=cqZU3b8NDB8&t=89s

#እንዴት #ድንቅ #አምላክ #ነው #እኛ #የምናመልከው..
#ከዚህ ቀደም የተወረሱ ቦታዎች እንዲመለሱ ተደርጓል። መጋቢ ታምራት አበጋዝ

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታማራት አበጋዝ ከWBN ጋር በነበራቸው ቆይታ የስረዓተ አምልኮ ቦታዎችን #እና የስረዓተ መቃብር ቦታዎችን ፍተሃዊ በሆነ #መንገድ እንዲያገኙ ተሰርቷል ብለዋል።

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከዚህ ቀደም የነበረው ተግዳሮት እንዲፈታ እና #ሁሉም በፍትሃዉነት እንዲስተናገዱ ሰርቷል።

ከቅርብ አመታት ወዲህ የሃይማኖት ተቋማት #ህጋዊ ሰውነት እንዲያገኙ ተስርቷል ያሉት መጋቢ ታማራት አበጋዝ የስረዓተ አምልኮ ቦታ እንዲያገኙ ተደርጓል።

በሌላ በኩል በአግባቡ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ እንዲስተናገዱ እና #ከዚህ ቀደም የተወረሱ ቦታዎች እንዲመለሱ ተደርጓል አሁንም ቀሪዎቹ እንዲመለሱ እና እንዲስተካከል እየተሰራበት ነው ብለዋል።

#ሙሉ ቃለ መጠይቁን የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሚል የፌስ ቡክ ገጽ ላይ ይመልከቱ።

የክርስቲያን ዜና በከፊል ዝርዝሩን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።
#ታላቅ ክሩሴድ በወታደሮች

የዩጋንዳ ጦር አባላት በሰሜናዊ ዩጋንዳ የ5 ቀናት ታላቅ ክሩሴድ ማድረጋቸው ተሰማ።

የወታደሮች #ክርስቲያን ፌሎሺፕ የሚል ህብረት ያላቸው የሃገሪቱ ጦር አባላት “ወታደራዊ ሃዋርያ” በሚል ቅጽል ስምም ይታወቃሉ።

ክሩሴዱን ኔቢ በምትባለው ሰሜን ዩጋንዳ በምትገኘው ላይፍ ላይን ሚኒስትሪ ጋር በመሆን ነው ያዘጋጁት።

ወንጌልን #ሁሉም መስማት አለበት በሚል የተጀመረው ይሄ ክሩሴድ የጦር አዛዥ የሆኑ ሜጀር ጀነራል ዴቪድ ዋካሎ የተባሉ ከፍተኛ መኮንንም ተገኝተዉበታል።
#መሰረተ #ክርስቶስ #ታላቅ የሕብረት #ጊዜ ላይ ናቸዉ

በአዲስ አበባ እና አከባቢው የሚገኙ የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሪዎች እና ምዕመናን #ሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናትን በመዝጋት በጋራ በምስራቅ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን እያመለኩ ይገኛል።

መረሃ ግብሩ "በሕይወት ታድሶ በህብረት ፀንቶ ወደ ፍፃሜዉ መገስገስ" በሚል መሪ ቃል እየተከናወነ ይገኛል።

በመሰናዶዉ በአዲስ አበባ በ11ዱም ክፍለ ከተማ የሚገኙ ሙሉ ምዕመናን እየተካፈሉ ይገኛል።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Please 🙏WATCH me
& #Register

#እግዚአብሔር የለም" በሚልበት በዚህች ዓለም ልጆችን

#እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደግሞም በሰውም ፊት የላቁ አድርጎ ማሳደግ እንዴት ይቻላል?

#ሁሉም ሊሰሙት #እና ሊማሩበት የሚገባ ...

የቀረን ጥቂት #ቦታ ነው #ብቻ በመሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ

#ማሳሰቢያ ያለምዝገባ መግባት አይቻልም!!!

ልጆቻችንን የሚጠብቅልን የለም ብላችሁ አትስጉ #ልጆች እየተጫዉቱ የሚጠበቁበት #እኛ በቂ ቦታ አዘጋጅተናል።

#Register #Register #ይመዝገቡ #ይመዝገቡ #ይመዝገቡ

ለመመዝገብ ሊንኩን ይጫኑ /ይደውሉ
https://docs.google.com/forms/d/1XBwJuLL8hCAO1SA3E8aTmmg2y32G9jwY1PnG-BS8XXQ/edit?usp=drivesdk
0911136520/0988353423
የቀድሞው የ #አሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መጽሃፍ #ቅዱስ መሸጥ ጀመሩ።

ትራምፕ በራሳቸው ማህበራዊ ትስስር ገጽ (ትሩዝ ሶሻል) ደጋፊዎቻቸው “ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ” የሚል ስያሜ ያለውን መጽሃፍ ቅዱስ እንዲገዙ ጥሪ አቅርበዋል።

#ወደ ፋሲካ በዓል እየተቃረብን ነው፤ ‘ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ’ መጽሃፍ ቅዱስን በመግዛት አሜሪካ ዳግም እንድትጸልይ እናድርጋት” ሲሉም ነው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት።

#ሁሉም አሜሪካውያን በቤታቸው መጽሃፍ ቅዱስ ሊኖራቸው እንደሚገባም ነው ያነሱት።

ትራምፕ ዝርዝር #ውስጥ መግባት ባልፈልግም መጽሃፍ ቅዱስ በህይወቴ ውስጥ ልዩ ቦታ አለው ብለዋል።

“ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ” መጽሃፍ ቅዱስ God Bless The USA Bible.com በተሰኘ ድረገጽ በ59.9 ዶላር ለገበያ ቀርቧል ተብሏል።

ድረገጹ መጽሃፍ ቅዱስ በትራምፕ መተዋወቁ “ምንም አይነት ፖለቲካዊም ሆነ የምርጫ ቅስቀሳ” አላማ የለውም ማለቱንም አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል።

#አዲሱ የመጽሃፍ ቅዱስ ግዙ ቅስቀሳም በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ትራምፕ በቀጣዩ ምርጫ ክርስቲያን ደጋፊዎቻቸውን ለማብዛት ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ተገልጿል።