The Christian News
5.32K subscribers
3.06K photos
27 videos
720 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#ሱዳን #ጦርነት
#ቤተክርስቲያን ማቃጠል
#የክርስቲያኖች #ስደት

በሱዳን እየተካሄደ ያለው ጦርነት አብያተ ክርስቲያናትን ማፈራረሱን ቀጥሏል ተባለ።

ባለፈው ሳምንት #ብቻ #ሁለት የወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በጦርነቱ ምክኒያት ጋይተዋል። በሱዳን ሁለተኛ ጥንታዊ እና ትልቁ #ቤተክርስቲያን በኦምዱርማን ከተማ ከጥቅም ውጪ ሆኗል።

ጥቃቱ በቤተ ክርስቲያኗ ዙሪያ የሚገኝን የክርስቲያኖች ትምህርት ቤት ኢላማ ያደረገ ቢሆንም፣ የፕሪባይቴሪያን  ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ህንጻም ፈራርሷል። ውስጥ የሚገኙ መጽሃፍ ቅዱስ፣ የመዝሙር ደብተር እና ዶክመንቶች ከጥቅም ውጪ ሆነዋል።

በቤተ ክርስቲያኑ ዙሪያም ወላጅ አልባ ህጻናት ትምህርት ቤት፣ የጥቃቱ ሰለባ ነው። ምንም እንኳን ህንጻው ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ቢሆንም፣ ሰው ላይ ግን የደረሰ ጉዳት የለም።

በጦርነቱ ከጥቅም ውጪ ከሆኑ ቤተ ክርስቲያኖች መካከል አንዱ፣ 81 አመታትን መንፈሳዊና ማህበራዊ አገልግሎቶችን ይሰጥ የነበረ ነው። ባለፈው አርብ በደቡባዊ ካርቱም፣ የሚገኝ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የቦምብ ጥቃት ተፈጽሞበት፣ 5 መነኩሴዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በጦርነቱ ዋነኛ የጥቃት ሰለባ የሆኑት አብያተ ክርስቲያናት መሆናቸውም እየተዘገበ ይገኛል። ኦምዱርማንና ካርቱም ብቻ ፈጣን ድጋፍ ሰጪ የተባለው ጦር፣ ሁለት አብያተ ክርስቲያናትን ተቆጣጥሮ የጦር ማዘዣ አድርጓል። በካርቱም የምትገኝን አንዲት ቤ/ክ ንብረት የሆኑ ተሽከርካሪዎችንም ለጦርነት አላማ እያዋለ ይገናል።

ባለፈው ሚያዝያ ወር ጌሪፍ የተባለን የመጽሃፍ #ቅዱስ ትምህርት ቤት ከጥቅም ውጪ በማድረግ የተማሪዎችን ዶርም፣ መማሪያ ክፍሎችና የአምልኮ ስፍራም ጥቃት ተፈጽሞበት ከጥቅም ውጪ ሆኗል ነው የተባለው።

በሱዳን ጦርና ፈጣን ሃይል ሰጪ በሚባለው ጦር መካከል  እየተካሄደ በሚገኘው 2ኛ አመቱን በያዘው ጦርነት፣ እስካሁን 10ሺህ የሚሆኑ ንጹሃን #ህይወት ያለፈ ሲሆን፣ ወደ 5.6 ሚሊዮን የሚጠጉ #ሰዎች #ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተሰደዋል ሲል ተ.መ.ድ አስታውቋል።

የሱዳን ጦር መሪ ጀነራል አብደል ፈታህ አልቡርሃንና የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ሃይሉ መሪ ሞሃመድ ሃምዳን ደጋሎ በጋራ የሲቪሉን የሽግግር መንግስት ከስልጣን ካወረዱ በኋላ፣ በመካከላቸው የተፈጠረ ልዩነት ሱዳንን ዛሬ ላይ አድርሷታል።

#ምንም #እንኳን ለ30 አመታት ሱዳንን የመሩት ኦማር አልበሽር የስልጣን ዘመን የነበረው የክርስቲያኖች ስደት ይቀንሳል ተብሎ የነበረ ቢሆንም፣ በጦርነቱ ምክኒያት ግን እየተባባሰ ይገኛል ነው የተባለው።

ኦፕን ዶርስ በ2023ቱ ሪፖርት መሰረት፣ ሱዳን በ2021 ከነበረችበት የ13ኛ ደረጃ የክርስቲያኖች ስደት ተባብሶ ወደ 10ኛ ደረጃ ከፍ አድርጓታል።

ክርስቲያኒቲ ቱደይ እንዳስነበበው በሱዳን ከአጠቃላይ 43 ሚሊዮን ህዝቧ መካከል፣ 4.3 በመቶው ወይም ወደ 2 ሚሊዮን የሚሆነው #ሕዝብ #ክርስቲያን ነው።
#ሰው ሸሽቶ #ቤተክርስቲያን ሲገባ #እንዴት ይገደላል? አገዳደሉ አሳቃቂ ነው። ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ

የመካነ ኢየሱስ ፕሬዝደንት በዚህ ወረ በመካነኢየሱስ ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ #መጽሐፍ #ቅዱስ ግምባራቸው #ላይ ነበር የተገደሉት ምዕመናን ከአንድ #ቀን በኋላ ነው የተገኙት ብለዋል።

ፕሬዝደንቱ አክለው #እንደ ቤተክርስቲያን መረጃው እስኪጣራ ነው ይፋ ያላደረግነው ያሉ ሲሆን በቤተክርስቲያን አካሄድ የቻልነውን ያህል ሄደናል ያሉ ሲሆን #መንግስት የሕዝብ የድህንነት #ጉዳይ በእጁ ነውና አሁንም #ተስፋ የምናደርገው መንግስት ገዳዮችን ለፍርድ እንደሚያቀርብ እናምናለን ሲሉም ተናግረዋል።

#ይህ ጥቃት በማን ነው የተፈጸመው ?

ከአደጋው የተረፉት ትክክለኛው ገዳዮች #ምን እንዳደረጉ እነማን እንደሆኑ ያውቃሉ። #ነገር #ግን ለደህንነታቸው ስለሚሰጉ ለመናገር ፍላጎት የላቸውም። መንግስት ግን ተከታትሎ ለፍርድ እንዲያቀርብልን እንጠይቃለን።
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።
የመጽሃፍ ቅዱስ ሳምንት ሊያካሂድ ነው።

#በኢትዮጵያ የመጽሃፍ ቅዱስ ማህበር አዘጋጅነት የሚካሄደዉ የመፅሐፍ ቅዱስ ሳምንት እና የቅዱሳት መጻህፍት አውደ ርዕይ ከመጋቢት 16-21 የሚቆይ ሲሆን በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል ነው የሚካሄደው።

ማህበሩ በእነዚህ ቀናት ያለፉትን 98 ዓመታት የሰራቸውን ስራዎች ለታዳሚያን እንደሚያቀርብና ራሱን የሚያስተዋውቅበት መድረክ እንደሚሆን ይጠበቃል።

#ዛሬ ስካይላይት ሆቴል የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ የማህበሩ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ተስፋጽዮን ደለለኝ፣ የማህበሩ ዋና ጸሃፊ አቶ ይልማ ጌታሁን እና መጋቢ አሸብር ከተማ በጋራ ሰጥተዋል።

መጽሃፍ #ቅዱስ ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ፣ ክርስቲያኑን ስለ መጽሃፍ ቅዱስ ንባብ ማነቃቃት፣ በመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ የሚሰሩ አብያተ ክርስቲያናትን በተዛማጅ ስራዎች ላይ ማስተባበር፣ የወንጌል ስብከትን ማበረታት፣ ለአሁኑ ትውልድ የመጽሃፍ ቅዱስን አደራና ሃላፊነት ማስተላለፍ እና መጽሃፍ ቅዱስን ከአደጋዎች መጠበቅ በሳምንቱ ከሚኖሩ ክንውኖች መካከል ናቸው።

ሌላው ማህበሩ ከመጋቢት 16-21 ድረስ የቅዱሳት መጻህፍት አውደ ርዕይ ያከናውናል። በእነዚሁ ቀናቶች የውይይት መድረኮች፣ ሴሚናሮች እና ልዩ ዝግጅቶች ይካሄዳሉ።

ትውልዱን ስለ ቅዱሳት መጻህፍት እንዲያውቅ ማድረግ፣ የህትመት ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ ማድረስ እና ማህበሩን ከህዝብ ጋር ማስተዋወቅ በአውደ ርዕይው የሚከናወኑ ዋና ዋና ስራዎች ናቸው።

የኢትዮጵያም ይሁን የአለም አቀፉ መጽሃፍ ቅዱስ ማህበር እስከ ቅርብ ጊዜ የመጽሃፍ ቅዱስ ተደራሽነት ላይ ብቻ ሲሰራ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ግን ተጽኖ ፈጣሪነቱም ላይ መስራት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል።
#ደረሰ ደረሰ ደረሰ ...

የመጽሃፍ #ቅዱስ ሳምንት

#በኢትዮጵያ የመጽሃፍ ቅዱስ ማህበር አዘጋጅነት የሚካሄደዉ የመፅሐፍ ቅዱስ ሳምንት #እና የቅዱሳት መጻህፍት አውደ ርዕይ ከመጋቢት 16-21 በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል።

ክርስቲያኑን #ስለ መጽሃፍ ቅዱስ ንባብ ማነቃቃት፣ በመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ የሚሰሩ አብያተ ክርስቲያናትን በተዛማጅ ስራዎች ላይ ማስተባበር፣ የወንጌል ስብከትን ማበረታት፣ ለአሁኑ ትውልድ የመጽሃፍ ቅዱስን አደራና ሃላፊነት ማስተላለፍ እና መጽሃፍ ቅዱስን ከአደጋዎች መጠበቅ በሳምንቱ ከሚኖሩ ክንውኖች መካከል ናቸው።

ትውልዱን ስለ ቅዱሳት መጻህፍት እንዲያውቅ ማድረግ፣ የህትመት ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ ማድረስ እና ማህበሩን ከህዝብ ጋር ማስተዋወቅ በአውደ ርዕይው የሚከናወኑ ዋና ዋና ስራዎች ናቸው።

#ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

መግቢያ #በነፃ ...
#መጽሐፍ #ቅዱስ የማያነብ #ክርስቲያን የተበደለ ነው”

ይህንን ያሉት የኢትዮጵያ የመጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ተስፋጽዮን ደለለው ናቸው።

“መጽሀፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በሕዝባችን ሕይወት እናስርጽ!” በሚል መሪ ቃል የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ማስጀመሪያ መረሃ ግብር እየተካሄደ ነው።

በመድረኩ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የማህበሩ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ተስፋጽዮን ደለለው “መጽሐፍ ቅዱስ ያነበቡት ሁሉ ሕይወታቸው ተለውጧል ስለዚህ አሁን ያለው ትውልድ እንዲነብ ልናበረታታው ይገባል ብለዋል።” ብለዋል።

አክለውም መጽሐፍ ቅዱስን የማያነብ እና የማይገልጥ ክርስቲያን የተበደለ ነው። ማህበሩ ከማሳተም እና ከማሰራጨት ውጪ ብቻውን ምንም ማድረግ አይችልም በመሆኑም ህዝበ ምዕመኑ መጽሐፍ ቅዱስን አጠንክሮ እንዲያነብ ስለሚያስፈልግ ይህንን መድረክ አዘጋጅተናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማሕበር አዘጋጅነት የመጽሀፍ ቅዱስ ሳምንት በዓል እና የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ መክፈቻ መረሃ ግብር በስካይ ላይት ሆቴል የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች በተገኙበት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

መረሃ ግብሩ የቀጠለ ሲሆን The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው የምንገኝ ሲሆን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎች ይዘን የምንመለስ ይሆናል።
#አስደሳች #ዜና

በአሁኑ ወቅት #ብቻ በኢንዶኔዥያ ከ35 በሚበልጡ ቋንቋዎች መጽሃፍ #ቅዱስ ትርጉም እየተካሄደ ይገኛል።

ኢንዶኔዥያን ለየት የሚያደርጋት ነገር፣ በአለማችን #ላይ ብዙ የእስልምና #እምነት ተከታዮች ያሉባት ሃገር መሆኗ ነው። ዋይክሊፍ አሶሴሽን የትርጉም ስራዎቹን የሚያከናውነው፣፣ በአካባቢው ከሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትና #አዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ነው።

#አዲሱ የትርጉም ቴክኖሎጂ፣ በየአካባቢው የሚገኙ ክርስቲያኖች የትርጉም ስራውን ከፊት ሆነው ይመሩ ዘንድ ይረዳል ነው የተባለው። ይሄም መጽሃፍ ቅዱስ ባለቤትነታቸውን ይበልጥ ያረጋግጥላቸዋል። ግምገማ፣ ስልጠና፣ ህትመትና ስርጭቱንም ቢሆን እራሳቸው የየአካባቢው #ሰዎች እንዲሳተፉበት ይረዳቸዋል ነው የተባለው።

በአሁኑ ወቅት ብቻ ከዋይክሊፍ ተጨማሪ ሌሎች የመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ድርጅቶች #አንድ ላይ በመሆን ከ60 በማያንሱ የኢንዶኔዥያ ሃገር ቋንቋዎች እየተተረጎሙ ይገኛሉ።

በኢንዶኔዥያ ብቻ ለሚሰራው የመጽሃፍ ቅዱስ ስራ፣ ከ400 እስከ 500 ሺህ ዶላር በጀት ተይዞለታል። #ይሄ ወጪ ከበጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበ ሲሆን ሌሎችም በጸሎት የዚህ #ታላቅ ስራ አካል ይሁኑ ሲል ዋይክሊፍ ጥሪ አቅርቧል።

ኢንዶኔዥያ ውስጥ ከ700 በላይ ቋንቋዎች ይገኛሉ። ይሄም ሃገሪቱን በአለም ላይ ካሉ ቋንቋዎች 10 በመቶ በሃገሪቱ ብቻ መኖሩን ያሳያል።
" 2 አገልጋዮች ከነ #ሙሉ ቤተሰቦቻቸው በጥይት ተደብድበው ተገድለዋል " - የአካባቢው ምዕመናን

የደብረ ቅዱሳን #ቅዱስ ገ/ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን #ሁለት አገልጋዮች #ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው መገደላቸውን የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለጸ።

በምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በዶዶላ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን 2 አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው ጋር ለጊዜው " ማንነታቸው አልታወቀም " በተባሉ አካላት መገደላቸው ተነግሯል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው ፤ ግድያው የተፈፀመው ትናንት መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ገደማ መሆኑን የአካባቢው ምዕመናን እንደነገሩት ገልጿል።

በተፈጸመው በዚህ ግድያ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ #ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት አንድ መሪጌታና ዲያቆንን ጨምሮ 5 የቤተሰብ አባሎቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸው ተገልጿል።

የቴሌቪዥን ጣቢያው ፥ በዶዶላ ከተማ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም በርካታ ኦርቶዶክሳውያን መገደላቸውን አስታውሷል። ሲል ቲክቫህ #ኢትዮጵያ አስነብቧል።
የቀድሞው የ #አሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መጽሃፍ #ቅዱስ መሸጥ ጀመሩ።

ትራምፕ በራሳቸው ማህበራዊ ትስስር ገጽ (ትሩዝ ሶሻል) ደጋፊዎቻቸው “ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ” የሚል ስያሜ ያለውን መጽሃፍ ቅዱስ እንዲገዙ ጥሪ አቅርበዋል።

#ወደ ፋሲካ በዓል እየተቃረብን ነው፤ ‘ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ’ መጽሃፍ ቅዱስን በመግዛት አሜሪካ ዳግም እንድትጸልይ እናድርጋት” ሲሉም ነው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት።

#ሁሉም አሜሪካውያን በቤታቸው መጽሃፍ ቅዱስ ሊኖራቸው እንደሚገባም ነው ያነሱት።

ትራምፕ ዝርዝር #ውስጥ መግባት ባልፈልግም መጽሃፍ ቅዱስ በህይወቴ ውስጥ ልዩ ቦታ አለው ብለዋል።

“ፈጣሪ አሜሪካን ይባርክ” መጽሃፍ ቅዱስ God Bless The USA Bible.com በተሰኘ ድረገጽ በ59.9 ዶላር ለገበያ ቀርቧል ተብሏል።

ድረገጹ መጽሃፍ ቅዱስ በትራምፕ መተዋወቁ “ምንም አይነት ፖለቲካዊም ሆነ የምርጫ ቅስቀሳ” አላማ የለውም ማለቱንም አሶሼትድ ፕረስ ዘግቧል።

#አዲሱ የመጽሃፍ ቅዱስ ግዙ ቅስቀሳም በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ትራምፕ በቀጣዩ ምርጫ ክርስቲያን ደጋፊዎቻቸውን ለማብዛት ሊጠቀሙበት እንደሚችሉ ተገልጿል።
#ዛሬ ይጠናቀቃል

“መጽሀፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በሕዝባችን #ሕይወት እናስርጽ!” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየዉ የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ይጠናቀቃል።

በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እና የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት መሪዎች በተገኙበት በመካሄድ #ላይ ይገኛል።

#የኢትዮጵያ መጽሐፍ #ቅዱስ ማሕበር አዘጋጅነት የመጽሀፍ ቅዱስ ሳምንት በዓል #እና የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ከሰኞ የጀመረ ሲሆን በዛሬዉ እለት የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ክርስቲያኑን #ስለ መጽሃፍ ቅዱስ ንባብ ማነቃቃት፣ በመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ የሚሰሩ አብያተ ክርስቲያናትን በተዛማጅ ስራዎች ላይ ማስተባበር፣ የወንጌል ስብከትን ማበረታት፣ ለአሁኑ ትውልድ የመጽሃፍ ቅዱስን አደራና ሃላፊነት ማስተላለፍ እና መጽሃፍ ቅዱስን ከአደጋዎች መጠበቅ በሳምንቱ ዉስጥ ሲሰራ የነበረ #ስራ ነዉ።

በሳምንቱ ዉስጥ ትውልዱን ስለ ቅዱሳት መጻህፍት እንዲያውቅ የማድረግ ስራ ፣ የህትመት ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ ማድረስ እና ማህበሩን ከህዝብ ጋር ማስተዋወቅ በአውደ ርዕይው ሲከናወን ቆይቷል።

የኢትዮጵያ መፅሐፍ ቅዱስ ማሕበር ሁሉንም ሁሉንም አብያተ ክርስቲያናት እና ምዕመናንን ባለፋት 98 ዓመታት አገልግሏል።

ፎቶ 📷 Hossana production Hossana
#አዲስ መጽሐፍ #በቅርብ #ቀን...

ከ1,300 ገጾች በላይ ተዋቅሮ ከ4,800 በላይ ቃላት ያካተተ #ድንቅ የአማርኛ መጽሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት በዘላለም መንግስቱ ተዘጋጅቶ በቅርብ ቀን ወደ አንባቢያን ይደርሳል።

23 ዓመታት የፈጀው #ይህ #ድንቅ መጽሀፍ በቅርብ ቀን በአዲስ አበባ ሰኔ 15 2016 በኢቫንጀሊካል ቴዎሎጂካል ኮሌጅ (ETC) የምስጋና ጊዜ ከጠዋቱ 4 እስከ 6 ሰዓት በድምቀት ይመረቃል።
#ብዙ ዋጋ የተከፈለበት #በኢትዮጵያ ትልቁ የመፅሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት ተመረቀ።

በዘላለም #መንግስቱ ተጽፎ ከ1,300 ገጾች በላይ ተዋቅሮ ከ4,800 በላይ ቃላት ያካተተው ይህ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የጸሀፊው ወዳጆች በተገኙበት በCETC) ኢትዮጵያን ቴዎሌጂካል ኮሌጅ በድምቀት ተመርቆ ለአንባብያን ተሰራጭቷል።

በመድረኩ መጽሀፉን #ሙሉ በሙሉ ጽፎ ለማጠናቀቅ 23 ዓመታት እደፈጀ እና በዚህ ስራ #ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት ምስጋናውን አቅርቧል።

ዘላለም መንግስቱ በንግግሩ ይህ መፅሐፍ ማለት እንደ "ማንኪያ" ነው። ዋናው ምግቡ ግን "መፅሐፍ ቅዱስ" ነው። ያለ ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስን የበለጠ ለመረዳት የሚያግዝ መጽሐፍ እንደሆነ ተናግሯል።

አክሎም ምንም እንኳን እጨርሰዋለሁ ብዬ ባልጀምረውም ለብዙዎች የሚያግዝ በመሆኑ በእግዚአብሄር እርዳታ ተጠናቋል። ይህ መጽሐፍ በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ የተጻፈ እንደመሆኑ መጠን ይህ መጽሀፍ መጽሀፍ ብቻ ሳይሆን አደራም ጭምር ነው ሲል ተናግሯል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉ መሪዎች እረጅም አመታትን በትዕግት በመጻፍ ይህንን መጽሀፍ በዚህ ወቅት ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በማበርከቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ ዘመን ያለን አገልጋዮች ይህንን መጽሀፍ ባንጠቀምበት ፤ እና ባንሰራበት ለእኛ እዳ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ዘላለም መንግስቱ ከዚህ ቀደም መንፈስ ቅዱስ እና ካሪዝማዊ ቀውሶች ፤ እንዘምር ወይስ እንዝፈን ፤ ክርስቲያናዊ ኢትዮጵኝነት ፤ የሐሰተኞች እሳተ ጎመራ ፤ ትንቢተ ዕምባቆም ፤ የይሁዳ መልዕክትን ጨምሮ ወደ 20 የሚደርሱ መጽሀፍትን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አበርክቷል።

#የኢትዮጵያ ቃለ #ሕይወት #ቤተክርስቲያን #ዋና ጸሐፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት #እና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች በጽሎት መጽሀፉን መርቀው ለንባብ እንዲበቃ በይፋ መርቀውታል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ሙሉ ዘገባውን አሰናዳንላችሁ። በቻናላችን ስም ለወንድም Zelalem Mengistu የተሰማንን እጅግ ትልቅ ደስታ እየገለጽን ሁላችሁም ትጠቀሙበት ዘንድ እናበረታታለን።