The Christian News
5.32K subscribers
3.06K photos
27 videos
720 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
መካነየሱስ #ቤተክርስቲያን የሰላም #ጥሪ አቀረበች።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነየሱስ በአማራ ክልል በተፈጠረዉ ግጭት ማዘኗን ገልፃ ነገሮች በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ አቅርባለች።

ቤተክርስቲያኒቱ በዛሬው እለት በሰጠችዉ መግለጫ በአማራ ክልል የተከስተው ግጭት እና አለመረጋጋት የሕይወት ሕልፈት እና የንብረት ዉድመት ማስከተሉ ቤተክርስቲያን እጅግ አሳዝኗታል።

ይህ ግጭት ምክክር ተደርጎ አፋጣኝ መፍትሔ ካልተሰጠዉ ከፍተኛ አገራዊ ጉዳት እንደሚያስከትል በመግለፅ በሰላማዊ መንገድ እና በምክክር ይፈታ ዘንድ የሚመለከታቸዉ አካላት #ሁሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ስም የሰላም ጥሪ ታደርጋለች።
#live እየገባችሁ በልሳን የምትፀልዮ ሰዎች ስህተት ውስጥ ናችሁ። ዘማሪት ሶፊያ ሽባባዉ

#መጽሀፍ #ቅዱስ ድርጊታችሁን ስህተት ነው ስለሚል እኔም ስህተት ነው እላለሁ።

በየ ሚዲያውና በየ ቲቪ ቻናሎች በልሳን የሚጸለይበት አላማው ምንድነው? ይህን በማድረጋችሁ እምነቱን ከማሰደብና ማላገጫ ከማድረግ ውጭ አንዳች የምታመጡት ጥቅም የለምና እባካችሁ ስሜታዊነትን አስወግዱና ቃሉ እንደሚል እንሁን።

የሚመለከታቸው #ክርስቲያን #ሁሉ #አሜን እያለ ከማደፋፈር ይልቅ ልክ አለመሆናቸውን በማሳወቅ ማስተው ያስፈልጋል። ማንም ሰው ከቃሉ አይበልጥም።

አንዳንድ አገልጋዮች የማያምኑ ሰዎች በጉባኤው እንዳሉ እያወቁ እስኪ ሁላችሁ በልሳኖቻችሁ ጸልዩ ብለው ጭራሽ ትዛዝ ሲሰጡ ግራ ይገባኛል።ሰውም እነሱ ያሉትን ተከትሎ በሚያምንም በማያምንም ፊት በልሳን እየጮኸ ይጸልያል።

#የእግዚአብሔር #ቃል ነው መከበር ያለበት ወይስ የአገልጋዩ ትዕዛዝ? የሁልጊዜ ጥያቄዬ ነው።

1ቆሮንጦስ 14:23
እንግዲህ ማኅበር ሁሉ አብረው ቢሰበሰቡ ሁሉም በልሳኖች ቢናገሩና ያልተማሩ ወይም የማያምኑ ሰዎች ቢገቡ፡— አብደዋል አይሉምን?
#በአዲስ #አመት #ሌላ #በረከት
ከግማሽ #ሚልዮን በላይ .. በማዉጣት ለአቅመ ደካሞች ..

የፌይዝ ባይብል ኢንተርናሽናል ቸርች ሚራክል አጥቢያ ከጉድለቷ በመቆረስ ከ550,000 ብር በላይ ወጪ የተደረገበት ሶስት የአቅመ ደካሞች ቤት አስመረቁ።

በፕሮግራሙ ላይ የፌይዝ ባይብል #ኢንተርናሽናል ቸርች መሪ የሆነው ቢሾፕ ዳዊት ሞላልኝ እንዲሁም የልደታ ክፍለ ከተማ አፈ ጉባኤ አቶ ዘሪሁን እና የወረዳ 8 አፈጉባኤ እና ሌሎች አመራሮች በተገኙበት አስመርቀን አስረክበናል::

በዚህ በጎ ተግባር ላይ በገንዘባችሁ እና በሙያችሁ የተሳተፋችሁ የቤተክርስትያናችን አባሎች #ሁሉ #እግዚአብሔር ይባርካችሁ::

Fbi Church Miracle Chaple Mekanisa
#መልካም #እለተ ሰንበት ይሁንልን 🙏🙏🙏

ቴክኒካሊ ብልጥ ሆነን የማናልፍበት ዘመን መጥቷል።

ዘመኑን ለማለፍ መንፈሳዊ መሆን የግድ ነዉ። እሱም ከኢየሱስ ጋር #ብቻ መሆን #ነዉ የሚያዋጣዉ።

በመፅሐፍ #ቅዱስ #ብዙ ታሪክ የሰሩ ሰዎችን ብንመለከት #እንኳን አለም እነሱን አይታ ተሸናፊዎችነዉ ያለቻቸዉ። ማንም አይፈልጋቸዉም ነበር።

በዘመናቸዉ #ሁሉ #ኢየሱስ ሲሉ ነበር ካለፉ በኋላ ግን ሁሉም ሰዉ ስለ ኢየሱስ ከ2ሺህ ዘመናት በላይ ይናገራል።

ኢየሱስ ካልክ የዚህ ድንቅ መፅሐፍ አካል ትሆናለህ። መፅሐፍ ቅዱስ የአንድ ታሪክ መፅሐፍ ነዉ። እነዚህ ሁሉ ሰዎች ስለ አንድ ታሪክ ሲናገሩ ነዉ የታሪክ አካል የሆኑት።

#ነብይ ጥሌ
#ኢየሱስን ተከተሉ

ዝነኛዉ የላቲን ሬጌቶን #አርቲስት ዳዲ_ያንኪ (ዘ ቢግ ቦስ) ለሚከተሉኝ #ሰዎች #ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስን ተከተሉ #እርሱ #መንገድ ፣ እውነትና #ሕይወት ነው” በማለት ዓለማዊ ሙዚቃን ትቶ ክርስቶስን እንደሚያገለግል አስታውቋል። ዳዲ_ያንኪ በተለይ ዴስፓሲቶ (Despacito) በሚለው ዘፈኑ ይታወቃል።
በርግጥ ወንጌላውያን #በዚህ ደረጃ ፍትሕ ተጓድሎባቸዋል ?

#ይህንን #ጥያቄ #ለምን በተደጋጋሚ ማንሳት አስፈለገ ?

ሁላችሁም መልሱን አዘጋጁ #እኛ #ግን የራሳችንን ሃሳብ እንሰነዝራለን።

በትላንትናዉ ዕለት #የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካዉንስል በወንጌላዊያን አማኞች እና አብያተክርስቲናት ላይ እየደረሰ ስላለዉ ፍትህ መጓደል ለሚዲያዎች ጋዜጣዊ #መግለጫ ሰጥቷል።

በካውንስሉ ጠቅላይ ጽሐፊ አማካኝነት በተሰጠዉ መግለጫ #ላይ በዋናነት ከ 6 በላይ .. የሆኑ (የደረሱ የፍትሕ መጓደል) የሚያሳዩ ነጥቦች ተጠቅሰዋል።

1. በደርግ #ዘመን የተወረሱ የቤተክርስቲያን ይዞታዎች በኢሕአዴግ ዘመን በከፊል ቢመለሱም እስካሁን ያልተመለሱ የኦሎምፒያ መሰረተ #ክርስቶስ ፣ የአዲስ ከተማ ገነት፣ የኢትዮጵያ ወንንጌላዊት #ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ብረት የሆነው የጉድ ሼፐርድ ማዕከል ፣ቄራ አካባቢ ያለው የብርሃነ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ፣እና ሌሎች እስካሁን ያልተመለሱ ይዞታዎች ሲሆኑ እነዚህ ይዞታዎች የቤተክርስቲያን ንብረት በመሆናቸዉ እንዲመለሱ ተጠይቋል።

2 የድሬዳዋ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን #በአንድ ወር #ጊዜ ዉስጥ ይዞታዋን ለቃ እንድትነሳ የከተማዉ አስተዳደር የወሰንኑ ቢሆንም የከተማዉ አስተዳደር እና የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች እንዲሁም የካውንስሉ አመራሮች ሰፊ ዉይይት አድርገዉ የከተማዉ አስተዳደር ጉዳዩን እየመከረበት ይገኛል። የከተማዉ አስተዳደር የደረሰበትን ደረጃ በአጭር ጊዜ ግልፅ እንዲያደርግ ተጠይቋል።

3 የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ይዞታ ነጥቆ የራሱ ጽህፈት #ቤት አድርጎት ይገኛል። እንዲሁም የቃለ #ህይወት ቤተክርስቲያን ይዞታ የሆነዉን የኩሪፍቱ የጸሎት ማዕከል በተመለከተም በማእከሉ #ምንም አይነት የልማት #ስራ ቤተ ክርስቲያን እንዳታከናወን በማገድ የቤተክርስቲያኑን ይዞታ ለመንጠቅ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝኝ ተገልጾ የቢሾፍቱ #ከተማ አስተዳደር ከዚህ ህገወጥ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እና የወሰደዉን የቤተክርስቲያን ንብረት እንዲመልስ ተጠይቋል።

4. በአዲስ አበባ ዙሪያ ባለችው የሸገር ከተማም የፈረሱ የወንጌላዊያን የእምነት ተቋማት ይዞታቸዉ እንዲመለስ እንዲሁም በከተማዋ ለ23 አብያተክርስቲያናት ከካቢኔ #ቦታ ተወስኖላቸዉ ቦታቸዉን መረከብ ላልቻሉ በአፋጣኝ ካቢኔ የወሰነዉ ዉሳኔ ተግባራዊ እንዲሆን ተጠይቋል።

5 የመቃብር ስፍራን ጥሶ በመግባት እየተደረገ የሚገኘዉ አግባብ ያልሆነ ተግባር በአስቸኳይ እንዲቆም

6 በምዕራብ ኢትዮጵያ በቄለም ወለጋ ዞን በጊዳሜ ወረዳ ዘጠኝ ምእመናንን የአምልኮ ስነስርአት እየፈፀሙ ካሉበት ሌሊት ላይ ተወስደዉ መረሸናችው #እጅግ #አሳዛኝ እንደሆነና ለነዚህ ንፁሃን ፍትህ እንዲሰጥ ተጠይቋል።

በአጠቃላይ #ይህ #ሁሉ እየሆነ ያለዉ የታችኛዉ የመንግስት አካል የመንግስትን ስልጣን በመጠቀም ጥቂት ግለሰቦች የግል አጀንዳ ይዘዉ የሚፈፅሙት ተግባር ነዉ።

የፌደራል መንግስት ጣልቃ በመግባት ፍትህ ሊያሰፍን ይገባል ሲል የኢትዮዽያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት #ካዉንስል በመግለጫዉ አስታዉቋል።

#ታዲያ ይህ ሁሉ የፍትህ ጥያቄ አለ #ማለት መጀመሪያላይ ለጠየኩት ጥያቄ ትክክለኛ ምላሽ በርግጥም ወንጌላውያን በግልፅ በአደባባይ #ፍትሕ ተነፍገዋል የሚል ነዉ።

ይሄንን ጥያቄ በዚህ ሰዓት ለምን ማንሳት አስፈለገ ከተባለ ደግሞ ከዚህ በፊት ለበርካታ አመታት ምላሽ ያላገኙ እና ፍትህ ያልተሰጣቸው ጥያቄዎች ባለበት ዛሬም ሌላ በደል እየደረሰ ስለሆነ ማንሳት አስፈላጊ ነዉ።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና የወንጌላውያን ድምፅ በመሆን ለበርካታ ጊዜያት ሲያገለግል ቆይቷል። አሁንም ገና ለቤተክርስቲያን ፍትህ ካልተሰጠ በስተቀር ጥያቄያችንን ማስተጋባታችን ይቀጥላል።

ፍትሕ ለወንጌላዉያን ቤተክርስቲያን
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።
#ወደ #ጌታ #ሄደ
ወንድዬ ዓሊ

ገጣሚ፣ ደራሲ፣ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና የግለታሪኮች ጸሐፊ፣ የድንቅ መዝሙራት ደራሲና ዘማሪ፣ የብዙዎች የሙያ አባት፣ … ወንድዬ ዓሊ በስተመጨረሻ ለሞት እጅ ሰጠ።

በክርስቶስ #ኢየሱስ አምኖ በመዳኑ መዳረሻውን ስለሚያውቅ ከባድ ህመም ቢያደቀውም በጽናት እና ያለ ሀዘን ነፍሱን ሰጠ።

የዘለአለም #ሕይወት ወራሽ ያደረገው የሞተለት #ጌታ ኢየሱስ በወንድዬ ሕይወት አልፎ ለቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ ለአገራችን ስነጽሑፍ ወዳጆች እና ለመላው የወንጌል አማኝ ስለሠራው #ሁሉ ስሙ ብሩክ ይሁን።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለመላው ወዳጆቹ #እግዚአብሔር መፅናናትን እንዲሰጥ ይመኛል።
#አስደሳች #ዜና ለወንጌል አማኞች #በሙሉ

#በመስቀል #አደባባይ የንስሐ፣ የምልጃና የምስጋና ፕሮግራም መዘጋጀቱ ተገለጸ።

በዛሬው እለት #የኢትዮጵያ #ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል መሪዎች በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ የንስሐ፣ የምልጃና የምስጋና ፕሮግራም መዘጋጀቱን ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል።

በተሰበረ #ልብ፣ በንስሐ መቅረብ የመጀመሪያ ተግባራችን መሆን እንዳለበት የጠቀሱት መሪዎቹ “#ወደ ደጆቹ በመገዛት ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፣ አመስግኑት፣ ስሙንም ባርኩ” (መዝ 100)፤4 በሚለው ቃለ #እግዚአብሔር መሠረት መጋቢት 8 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ #በአዲስ አበባ #መስቀል አደባባይ የንስሐ፣ የምልጃና የምስጋና በዓል ለማካሄድ አስፈላጊው ዝግጅት #ሁሉ ተጠናቋል ብለዋል።

አሁንም የእርስ በርስ መጠፋፋቱ አልቆመም ያሉት መሪዎቹ መደማመጥና መከባበር በመካከላችን እንዲኖርና ለይቅርታና ለፍቅር ልባችን የቀና እንዲሆንና ፀጋውንም እንዲያበዛልን #እግዚአብሔርን የምንማጸንበት #ጊዜ ይኖራል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በፕሮግራሙ የሚካፈለው የሕዝብ #ብዛት እጅግ ብዙ ስለሆነ ስብሰባው የሚካሄደው በመስቀል አደባባይ ነው፡፡

በመሆኑም መላው የወንጌል አማኝ በነቂስ ወጥቶ #በእግዚአብሔር ፊት የንስሐ፣ የምልጃና የምስጋና ፕሮግራሙ ተካፋይ እንዲሆን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዝርዝሩን አሰናዳንላችሁ።

#photo Christian tube - ክርስቲያን ቲዩብ

ዝርዝር መረጃ ምሽት ላይ በቪዲዮ ይዘንላችሁ የምንመለስ ይሆናል።
https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A?sub_confirmation=1
እግሮች #ሁሉ #ወደ #መስቀል አደባባይ ያመራሉ፥ እጆች ሁሉ ወደ አምላካቸው ይነሳሉ፣ ለአገራችን ይጸልያሉ አምላካቸውን ያመልካሉ!

በመጋቢት 8 ከ 7:0ዐ ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ልንገናኝ ቀጠሮ አለንና ከወዲሁ ሁላችንም እንዘጋጅ!!
#ዜና
«ዲልቢ ገለታ የሱሲፍ" የተሰኘ የመዝሙር ድግስ በሚሊኒየም #አዳራሽ ሊካሄድ ነዉ።

ኤልሀዳር ኢንጂነሪንግ ከዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ ጋር በመተባበር «ዲልቢ ገለታ የሱሲፍ» የተሰኘውን የመዝሙር ድግስ በሚኒሊየም አዳራሽ ሰኔ 2/2016 ዓ.ም ቀን ከ7፡00 ጀምሮ ማዘጋጀቱን #ዛሬ ግንቦት 27/2016 ዓ.ም በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል ።

#ዘማሪ ጳውሎስ ተገኝ ሶስት አልበሞችን እና የተለያዩ ዝማሬዎችን ከተለያዩ ዘማሪዎች ጋር በመስራት ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ያበረከተ ሲሆን «ሙጫ ካዮ» ከተሰኘ የህፃናት ህብረት ጋር በመሆን ሁለት ቪሲዲዎችን በመስራት ለአማኞች አድርሷል።

በእለቱ ስለታማ ነገሮች ምግብ እና መጠጥ ይዞ መግባት እንደማይቻል የተገለፀ ሲሆን በሚሊኒየም አዳራሽ መጠጥ እና ምግብ በሽያጭ እንደተዘጋጀ ተነግሯል።

በዚህ ፕሮግራም ለመሳተፍ የመግቢያ ዋጋው በነፃ ስለሆነ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከጠዋቱ 4 ሰአት ጀምሮ እንዲገኙ ጥሪ አስተላልፈዋል።

ፎቶ 📸 @ጥላሁን ደሳለኝ

#ወንጌል #ለዓለም #ሁሉ
ፍትህ #ግን ይወጣል ከሰማይ ...😭😭😭
አበጥሮ ሁሉን ከሚያይ ...
የጊዜ ጉዳይ እንጂ #ሁሉ ነገር
ከፍርድ የለም ሚቀር
ከፈጣሪ ወንበር ከሰማዩ መንበር
ስታይ ከዙፋን የለም አንድም ሚቀር
#ፍትህ ይወጣል ከሰማይ

#ልጆች #የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው። እናቶች የምድር በረከቶች ናቸው። እናቶች ብዙ ጊዜ ከመጽናናት ከሚከብዳቸው ነገሮች መካከል አንዱ የልጆችን ሃዘን መቋቋም ይከብዳቸዋል።

መጽሃፍ ቅዱስም “ #እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። የዋይታና የመራራ ልቅሶ ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤ የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናትን ፈጽሞ እንቢ አለች።” ይላል።

የእናትየዋን መሪር ሃዘን ሳይ ጥፋተኞቹ ከጥፋታቸው በላይ #አሁን በድጋሜ ለሌላ ጥፋት እየተሰናዱ መሆናቸው የበለጠ እንዳሳመማት ያሳያል።

የመጽናናት አምላክ የሆነ #እግዚአብሔር ለእናትዬው መጽናናት ይስጥ። ፍትህ ግን ተጓድላ አትቀርም።