The Christian News
5.38K subscribers
3.07K photos
27 videos
724 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
#Hanna_Tekle #እንደ_ሰው

በዚህ ዘመን በብዙ መልኩ ልብ በሚያወርዱ ጉዳዮች እናልፋለን በየቀኑ ብዙ እንሰማለን እናያለን.. እንደግል እንደቤተሰብ እንደሀገር ወይ እንደቤተክርስቲያን በብዙ ልብ የሚያሳዝኑ ጉዳዬች ብናልፍም አለምን ባሸነፈው በጌታችን ኢየሱስና በእርሱ ላይ ባለን እምነት ተስፋ አንቆርጥም! በዘላለሙ ተስፋችን ሁሌም በፀጋው እንበረታለን!

ደግሞ ከኀጢያት በቀር እንደኛ በነገር ሁሉ የተፈተነ ነውና ምናልፍበትም ጊዜያዊ ፈተናም ቢሆን ይገባዋል እርሱ እንደፈቃዱ በወደደው መንገድ ሁሉን ለበጎ ያደርጋል!

በዚህ ዝማሬ በየትኛውም ከባድ ሁኔታ ለምታልፉ ሁሉ መፅናናት እንዲሆንላቹ ፀሎቴ ነው!

እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን።
ሮሜ 8:28

https://www.youtube.com/watch?v=xawbM4JycJI
በመዲናችን #አዲስ አበባ እጅግ ብዙ #ወንጌል የተሰራ ብዙዎች በወንጌል የተደረሱ ይመስላችኋል?

የአዲስ አበባ ጎዳናዎች በተለይም #መገናኛ#ሜክሲኮ#ፒያሳ#ጀሞ#አያት እና ሌሎች አከባቢዎችን ስንመለከት ከተማዋ በወንጌል የተጥለቀለቀች ይመስላል።

#ነገር #ግን ይመስላል #ነው #እንጂ እውነታው #እጅግ ከዚህ የራቀ እንደሆነ በቅርብ #ጊዜ በአንድ መድረክ አስደንጋጭ ሪፖርት ወጥቷል።

#ከተማ ተኮር የወንጌል አገልግሎት በሚል በቀጠና #ሙሉ ወንጌል አጥቢያ #ቤተክርስቲያን ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ነበር።

ታዲያ #ይህ ጥናት ሲቀርብ ከ700 በላይ የሆኑ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች መጋቢዎች #እና አገልግዮች በቦታው ተገኝተው ነበር።

ጥናቱ #ኢትዮጵያ #ውስጥ የሚገኙ ተለቅ ተለቅ ያሉ 11 ከተሞችን የሚዳስስ የነበረ ቢሆንም እኛ ግን ለጊዜዉ የመዲናችንን አዲስ አበባ #ብቻ የተወሰነ እንበል።

ይህም ጥናት አዲስ አበባ ላይ በወንጌል የተደረሰው ሕዝብ 6 በመቶ ብቻ እንደሆነ ያሳያል።

ይህም በወንጌል ካልተደረሱ የአለማችን ከተሞች መካከል አንዷ አዲስ አበባ እንድትሆን አድርጓታል።

#እንደ ጥናቱ ከሆነ የአዲስ አበባ ከተማ እድገት እጅግ ፈጣን እና ከሌሎች የአለም ከተሞች ጋር ተወዳዳሪነት ባለው መልኩ በፈጣን እድገት ውስጥ የምትገኝ ከተማ እንደሆነች ተጠቅሷል ነገር ግን ይህቺን ከተማ መድረስ በሚችል መልኩ አገልጋዮቻችን ግን ለዚህ ዝግጁ እንዳልሆኑ ጠቁመዋል።

ይህንን ለመድረስ እጅግ ቅንጅት የሚፈልግ ቢሆንም በከተማችን የሚገኙ አገልጋዮች ግን ወደዚህ መስመር ለመግባት ገና ብዙ ስራ እንደሚጠይቅ ተጠቁሟል።

ምናልባት ይህንን ለመቅረፍ የቤት ስራ ተወስዶ በየአመቱ ለመሰብሰብ እና ለመነጋገር ቀጠሮ ቢያዝም ውጤቱን ግን ለወደፊት የምናየው ይሆናል።
#አንድ #ሰው በጌታ ያልሆነ ወዳጁ፣ ወደ ቤተ ክርስቲያናቹ ይዘኸኝ ሂድ ብሎ ይጠይቀዋል።

ይሄ ሰው የራሱን ማህበር እዳይወስደው፣ የምስባኩን ድራማ ፈራ! አሰብ አደረገና ይሻላል ብሎ ወዳሰበበት #ወደ ሌላ ህብረት ይዞት ሄደ። እዚያ የነበረው መድረክና ምስባክም ሰውየውን ከሰቀቀን አላዳነውም። ከዚያ ይሄ ወዳጁ ምን አለው፣ እዚህ #ቦታ አይደለም #እኔ፣ አንተስ ምን ታደርጋለህ አለው?

#እንደ #ክርስቲያን #አንድ አማኝ ያልሆነ #ሰው፣ ወደምትሄድበት ቤ/ክ ውሰደኝ ቢለን የት ይዘነው እንሄዳለን?

ፕሮፌሰር አታላይ አለም
#መንግሥት በአብያተ ክርስቲያናት ላይ የሚያደርገውን ግፍ ቀጥሏል።

የአልጄሪያ መንግስት በአብያተ ክርስቲያናት #ላይ እየወሰደ ያለውን ስልታዊ እርምጃ ቀጥሏል።

አልጄሪያ 42 ሚሊዮን #ህዝብ እንዳላት የሚነገር ሲሆን 1% ህዝብ በካቶሊኮች እና ፕሮቴስታንቶች የተወከለው የክርስቲያን ማህበረሰብን ናቸዉ።

#እንደ #ክርስቲያን ኮንሰርን ዘገባ ከሆነ በእስራኤል እና በሃማስ እየተካሄደ ያለው ጦርነት በሰሜን አፍሪቃዊቷ ሀገር ላሉ ክርስቲያኖች ህይወትን አስቸጋሪ አድርጎታል።

"የአልጄሪያ መንግስት በግጭቱ #ውስጥ እስራኤልን እንደሚደግፉ እና የውጭ እና የምዕራባውያን ተፅዕኖዎች የአገሪቱን ብሄራዊ አንድነት እንደሚያበላሹ ይገነዘባሉ" ሲል ICC በሪፖርቱ ገልጿል።

ባለፈው #አመት በአጠቃላይ 16 አብያተ ክርስቲያናት መዘጋታቸውን ተከትሎ የአልጄሪያ መንግስት የክርስቲያን አገልግሎቶች እስከ 10 #ሰዎች #ብቻ እንዲስተናገዱ መወሰኑን ዘገባዉ አክሏል።

በተጨማሪም፣ ICC እንዳለው፣ ባለፉት ሳምንታት በርካታ የአልጄሪያ ፓስተሮች በእምነታቸው ምክንያት ታስረዋል።

ICC (አይሲሲ) በሪፖርቱ "አብዛኞቹ የአልጄሪያ ክርስቲያኖች ከካቢሌ ጎሳ የመጡ በመሆናቸው የክርስቲያኖች ሁኔታ በአልጄሪያ ያለው ሁኔታ የበለጠ የተወሳሰበ ነው" ሲል ገልጿል።

"በአልጄሪያ ውስጥ ያለው ክርስትና ረጅም #ታሪክ ያለው ነው እና በአልጄሪያ መንግስት በአልጄሪያ ክርስቲያኖች እምነት እና በአካባቢው የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች መካከል ያለውን ልዩነት በአልጄሪያ መንግስት መለየት አለበት" ሲል አይሲሲ ተናግሯል.

አልጄሪያ በኦፕን ዶርስ የአለም ለክርስትና አስቸጋሪ ከሆኑ ሀገራት የ2023 ዝርዝር መሰረት ክርስትያኖች ከሚሰደዱባቸው 50 ሀገራት 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
የውክልና #ውጊያ‼️መጋቢ ፃዲቁ አብዶ
#ድንቅ #መልዕክት

ጦርነቱ የውክልና ጦርነት ነው የእውነተኛ አምላክና የአማልእክት ጦርነት ...

    መነሻ ቃል 1ሳሙ 17

👉 ቁጥር 4 በዚህ ስፍራ #ስለ ጎሊያድ ማንነት ይዘረዝራል ስለ ቁመቱ የጌት #ሰው መሆኑን ጀግንነቱን ትጥቁን ይናገራል::

👉 እስራኤልና ፍልስጤም ሁሌም ይዋጋሉ:: #በአንድ ወቅት #ግን  ጎሊያድ ያልተለመደና #እስራኤል ያልተዘጋጁበት የጦር ስልት ይዞ ቀረበ!! #እኔ የፍልስጤማውያንን ወገን ወክዬ አለሁ እናንተም የሚወክላቹ ጀግና ሰው ካላቹ አምጡና እንዋጋ ካሸነፈኝ ህዝቤ #እንደ ተሸነፈ ይቆጠር የሚል::

✝️ ቁጥ 8 " እናንተ የሳኦል ባሪያዎች" ሲል ከእስራኤል ወገን የሆኑትን ወታደሮች ሞራል በሚያወርድ ንግግር ተናገራቸው ከመሪያቸው እንዲሸሹ:: የሰዎቹን #ልብ ለመምታት። #ዛሬም  አንዳንድ #ሰዎች #እግዚአብሔር ከሰጣቹ መሪዎች ለመለየት ሲፈልጉ #እንዲህ አይነት ፕሮፓጋንዳ ይዘራሉ ።

✝️ ሰውዬው ከልጅነቱ ጦርነት የለመደ ተክለ ሰውነቱና ትጥቁ አስፈሪ ነበርና ለአርባ ቀንና ሌሊት ጠዋትና ማታ በተናገራቸው ቁጥር ሳዖልም እስራኤልም እጅግ ይደነግጡ ነበር::

👉ይሄኔ በንጉሡ በሳዖል በኩል ጎሊያድን የሚገድል እንዲህ ይደረግለታል የሚል አዋጅ ቢወጣም አንድም ሰው ግን አልተገኘም ነበር::

ጦርነቱ የውክልና ጦርነት ነው የእውነተኛ አምላክና የአማልእክት ጦርነት ነው:: #ስለዚህ ጎሊያድ ዳዊትን በአማልክቶቹ ስም ነው የረገመው #ነገር ግን ይሄንን እውነተኛ #አምላክ የሚወክል ጀግና ሰው አልተገኘም

👉ቀጥሎ ባሉት ቁጥሮች የእሴይ ስምንተኛና የመጨረሻ ስለሆነው ልጅ ስለ ዳዊት ማስተዋወቅ ይጀምራል::

✝️ እግዚአብሔር በስውር ያዘጋጀው ማንም የማያውቀው ከእግዚአብሔር ጋር ግን የሚተዋወቅ ቤተሰቡ የረሳው ጌታ ድል ያለማመደው:: ዳዊትን ወንድሙ እብሪተኛ አለው ቢያሳድገውም ቀዳሚው ቢሆንም አልተረዳውምና::

✝️ ዳዊት ስለ ጎሊያድ ጥያቄን ሲጠይቃቸው ንጉሱ ሳዖልን ጨምሮ ከራሳቸው በላይ ስለ ጎሊያድ አስፈሪነት እንደሰው አወሩት አትችለውም አሉት የአምላክን ጣልቃ ገብነት እረስተዋል::

✝️ ጎሊያድ ላቀረበው እስራኤል ግን ለማያውቀው አዲስ የጦር ስልት የሚገጥም ጀግና በታጣበት ጊዜ እግዚአብሔር በድብቅ ያዘጋጀውን ሰው አመጣ:: ዳዊትም ይህ ያልተገረዘ ማን ነው? አለ‼️

#ይህም ንግግሩ ለሳዖል ደረሰ ሳዖልም ዳዊትን አስጠራው የራሱን ልብስ አለበሰው ። #ይህ የሚያሳየን #ዳዊት በሚያመጣው ድል ተቀባይነትንና ስምን ለራሱ ለመውሰድ በመፈለግ ነበር ። አንዳንድ ሰዎች አሉ በሰው ድካም ድሉን የነሱ አድርገው የሚወስዱ ። ዳዊት ግን በዚህ መንገድ አልለመድኩም አለ::

እግዚአብሔር ባለማመደው ስልት ገባ በአምላኩ በእግዚአብሔር ስም ሊዋጋው #ወደ ጦር ሜዳው ገባ ገደለው በራሱ ሰይፍ አንገቱን ቆረጠው ።

      👉👉 መልእክቴ ይህ ነው ‼️

✝️ ዛሬም በህይወት ጉዞአችን ውስጥ ያልለመድነው ፣ ያላወቅነው፣ ያልጠበቅነው ፣ ያልተዘጋጀንበት #እኛ በፍጹም የማንችለው #ፈተና  ቢገጥመንም ነገር ግን #ጌታ ከእኛ ጋር አለና ጌታ ባለማመደን መንገድ #ድል ይሰጠናል ያድነናል ይታደገንማል::

✝️ ካፈጠጠብኝ  በአለም ካለው
     እጅግ ይበልጣል በእኔ ያለው
     የፍጥረት ገዢ ተቆጣጣሪው
     ጌታ ኢየሱስ ከእኔ ጋራ ነው‼️

#መጋቢ ጻድቁ አብዶ
#ሰው ሸሽቶ #ቤተክርስቲያን ሲገባ #እንዴት ይገደላል? አገዳደሉ አሳቃቂ ነው። ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ

የመካነ ኢየሱስ ፕሬዝደንት በዚህ ወረ በመካነኢየሱስ ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን ግድያ አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ #መጽሐፍ #ቅዱስ ግምባራቸው #ላይ ነበር የተገደሉት ምዕመናን ከአንድ #ቀን በኋላ ነው የተገኙት ብለዋል።

ፕሬዝደንቱ አክለው #እንደ ቤተክርስቲያን መረጃው እስኪጣራ ነው ይፋ ያላደረግነው ያሉ ሲሆን በቤተክርስቲያን አካሄድ የቻልነውን ያህል ሄደናል ያሉ ሲሆን #መንግስት የሕዝብ የድህንነት #ጉዳይ በእጁ ነውና አሁንም #ተስፋ የምናደርገው መንግስት ገዳዮችን ለፍርድ እንደሚያቀርብ እናምናለን ሲሉም ተናግረዋል።

#ይህ ጥቃት በማን ነው የተፈጸመው ?

ከአደጋው የተረፉት ትክክለኛው ገዳዮች #ምን እንዳደረጉ እነማን እንደሆኑ ያውቃሉ። #ነገር #ግን ለደህንነታቸው ስለሚሰጉ ለመናገር ፍላጎት የላቸውም። መንግስት ግን ተከታትሎ ለፍርድ እንዲያቀርብልን እንጠይቃለን።
#አስቸኳይ...

ሞትን ለማምለጥ የሚደረግ የሞኞች እሩጫ 🏃‍♂️🏃‍♀️🏃‍♂️🏃‍♂️

ከሰሞኑ #አንድ ዘገባ አነብብኩኝ ዝገባው #ቃል በቃል "የፌስቡክ መስራቹ ማርክ ዙከርበርግ ራሳቸውን ከዓለም ፍጻሜ ለመጠበቅ በሚል መጠለያ እየገነቡ መሆኑ ተገለጸ" ይላል #እንደ ርዕሱ ቢሆን ሁላችንም ፈገግ ብለን ብናልፈው መልካም #ነበር #ግን አይሆንም።

#ሁሉም #ሰው እንደሚሞት እንዲሁም የአለም ፍጻሜ እንዳለ እርግጠኛ ነው። ግን የሚመጣውን ጥፋትም #ይሁን የሚጠብቀውን የዘላለም #ሞት #እንዴት ማምለጥ እንዳለበት የተረዳ አይመስለኝም።

ለዚህም ይመስለኛል ባለጸጋው በአንድ ደሴት #ውስጥ ባለ #መሬት ውስጥ በ100 ሚሊዮን ዶላር መጠለያ በመገንባት #ላይ መሆናቸው የተሰማው።

አንዳንዴ ግን አጠቃቀሙን ካላወቅነው ሃብታም መሆን ከባድ ይመስለኛል።

ከ120 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተጣራ ሀብት እንዳላቸው የሚነገረው ቱጃሩ የፌስቡክ መስራች ዙከርበርግ የደሴቲቱን ስፍራ በ170 ሚሊዮን ዶላር ከዓመታት በፊት የገዙት ሲሆን አሁን #ደግሞ #በዚህ ስፍራ ላይ ቅንጡ የክፉ #ጊዜ መኖሪያ #ቤት እየገነቡ ነው፡፡

#ይህ ስፍራ ለኑሮ አስፈላጊ የሚባሉ ምግቦችን ማምረት፣ የኤሌክትሪክ ሀይል፣ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ማድረጊያ ሜዳ፣ ውሃ ዋና #እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ አገልግሎቶችን #ሙሉ ለሙሉ ከዚሁ ስፍራ ማግኘት በሚያስችል መልኩ በመገንባት ላይ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

#ክፉ ጊዜ ግን መቼ #ነው? ይህ ክፉ ጊዜ ሲመጣ እንዴት በደሴቶች ተሸሽገን ማለፍ እንችል ይሁን?

#መጽሐፍ #ቅዱስ የጌታ ምጽዓት እና የአለም ፍጻሜ በቀረበ ጊዜ በመጨረሻው ዘመን ጦርነት እና የጦር ወሬ ፤ የተፈጥሮ አደጋ መብዛት እንዳለ ይነግረናል በራዕይ መጽሀፍ ደግሞ ደሴቶችም #ሁሉ ሸሹ ተራራዎችም አልተገኙም ይላል።

ታዲያ ቱጃሩ ወዳጃችን ደሴትም ፈልፍሎ ለክፉ #ቀን የሚሆን ማምለጫ የሚያዘጋጀው ከማን ለመሸሽ ነው?

#ኢየሱስ ለደቀመዛሙርቱ #እውነት እውነት እላችኋለሁ ባለጠጋ #ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል ያለው ቃል ግልጽ ይመስላል።

ስለ ስሙ ያላቸውን ሁሉ ትተው የተከተሉት ግን የዘላለምን ሕይወት ይወርሳሉናል።

ለማንኛውም ወዳጄ ማርክን እና ሌሎች ባለጠጎች ከክፉ ቀን ማንም ሸሽቶ አያመልጥም እና መሸሸጊያ ዋሻ ወደ ሆነዉ ኢየሱስ ተሰብስበኝ በተሰጠን ጊዜ ተጠቅመን መጽሀፍ "እነሆ በደመና ይመጣል አይንም ሁሉ ያየዋል" እንደሚል ያንን ለማየት እንናፍቅ "ማራናታ" #አሜን መልዕክታችን ነው።