The Christian News
5.38K subscribers
3.07K photos
27 videos
724 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
“ካሁን በኋላ #ሴት #ነኝ የሚሉ ወንዶችን አናስተምርም” ኖተርዳም ስነ መለኮት ኮሌጅ

በአሜሪካ የሚገኘው እውቁ የኖተርዳም ስነ መለኮት ኮሌጅ ከዚህ ቀደም ያስተላለፈውን ውሳኔ ቀለበሰ። በአሜሪካ ኢንድያና ግዛት የሚገኘው የቅድስት #ማርያም ኖተርዳም የሴቶች ስነ መለኮት ኮሌጅ #ነው #ወደ ቀድሞው አቋሜ ተመልሻለው ያለው።

የኮሌጁ ፕሬዝዳንት #እና የቦርድ ሰብሳቢ በጋራ በመሆን “ወደ ካቶሊካዊት እሴታችን ተመልሰናል” ሲሉ መግለጫ አውጥተዋል።

ከወር በፊት ሴት ሆነው ተፈጥረው #ወንድ ነኝ ብለው የሚያምኑ ሰዎችን ኮሌጁ እቀበላለው ብሎ ነበረ። ኮሌጁ በውሳኔው ምክኒያት ትችቶች ተዘንዝረውበታል።

የኮሌጁ ቦርድ እና መሪዎች #ምንም #እንኳን በተለዋዋጭ አለም #ውስጥ ብንኖርም፣ የቤተ ክርስቲያንን አቋም ሳንቀያይር እናስቀጥላለን ሲሉ ተደምጠዋል።

ውሳኔው #ግን በኮሌጁ ተማሪዎች እና መምህራን ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም። ይሄንን አይነት ምላሽ ከኮሌጃችን ማህበረሰብ ባንጠብቅም፣ ካቶሊካዊ ማንነታችንን ግን አስጠብቀን መሄድ አለብን ሲሉ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።

ባለፈው #ወር በወሰንነው ውሳኔ በኮሌጃችን ህብረትን የሚያመጣ መስሎን ነበረ፣ #ነገር ግን ልዩነትን ፈጥረናል፣ ለዚህም #ይቅርታ እንጠይቃለን ብለዋል።
#ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየትኛዉም መልክ የተመሳሳይ #ጾታ ጋብቻን አትፈቅድም።

#የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት #ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ጠቅላይ ጽ/ቤት ከሰሞኑ ርዕሳነ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች የፈቀዱት ቡራኬ ላይ ማብራሪያ ሰጠ።

ከሰሞኑ የሮማዉ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ቤተክርስቲያኗ ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ቡራኬ እንዲሰጡ ፈቃድ መስጠታቸዉን የተለያዩ #መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

ይህንኑ ተከትሎም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ #ጠቅላይ ጽ/ቤት በጉዳዩ #ላይ #መግለጫ አዉጥቷል። ጠቅላይ ጽ/ቤቱ ከካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ስርዓተ አምልኮ ጋር የሚጻረር ወይንም ዉዥንብርን ሊፈጥር የሚችል ስርዓተ አምልኮን ያወግዛል ብሏል።

ሆኖም የጳጳሱ መልዕክት በተቃራኒው ተወስዷል የሚል ሃሳብ ያለዉን መግለጫ ያወጣ ሲሆን ለተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ጋብቻን #ግን ጳጳሱ ፈቃድ አልሰጡም ብሏል።

አክሎም የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅስን በማስቀመጥ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በየትኛዉም መልክ የተመሳሳይ ጾታ ጋብቻን አትፈቅድም ፤ አታጸድቅምም ማለቱን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከመግለጫው ተመልክቷል።

ቤተክርስቲያኒቱ ሀጢያትን አትባርክም ታወግዛለች #እንጂ ያለዉ መግለጫዉ የተመሳሳይ ጾታ #ጋብቻ የኢትዮጵያ ባህል #እና እሴትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት እንደማይኖረዉም በመግለጫው አስታዉቋል።

በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል
አሜሪካዊው #ፓስተር ለጋዛ #ክርስቲያኖች #ገንዘብ በማሰባሰብ #ላይ ይገኛሉ ተባለ።

ዊሊያም ዴቭሊን የተባለው #ይህ ፓስተር ከ2010 ጀመሮ #ወደ ጋዛ ከ30 ጊዜ በላይ ለሚሽን #ስራ ተመላልሰዋል። በእነዚህ ጉዞአቸውም በጋዛ የሚገኙትን የመጨረሻዎቹን 3 አብያተ ክርስቲያናት ሲያገለግሉ ነው የቆዩት።

በጋዛ ከሚገኙ 2.2 ሚሊዮን ዜጎች መካከል ወደ 1ሺህ የሚጠጉ ብቻ ናቸው ክርስቲያኖች።

በጋዛ በአንዲት የግሪክ ኦሮቶዶክስ #ቤተክርስቲያን ከ500 በላይ ክርስቲያን #እና ሙስሊሞች ተጠልለው የነበረ ቢሆንም በእስራኤል የአየር ጥቃት ቤተ ክርስቲያኗም ፈራርሳ የተጠለሉትም ተሰደዋል።

ሪዲም የተሰኘ የባልቴቶች እና ወላጅ አልባ ሚኒስትሪ በጋዛ የሚያካሂዱት እኚህ ፓስተር ካለፈው የፈረንጆቹ ዲሴምበር #ወር ጀመረው #ወደ 50ሺህ ዶላር መሰብሰብ መቻላቸውን ለክርስቲያን ፖስት ገልጸዋል።

#ምንም #እንኳን ገንዘቡ የተሰበሰበ ቢሆንም ወደ ጋዛ ለመላክ መጀመሪያ ወደ ዌስት ባንክ ከዚያ በጋዛ ላሉ ክርስቲያኖች እንደሚደርስ ነው የተናገሩት።

በጦርነቱ በጋዛ #ብቻ እስካሁን ከ22 ሺህ በላይ ሰዎች ሲገደሉ ወደ 58 ሺህ የሚጠጉ ደግሞ ቆስለዋል። በአንጻሩ በእስራኤል 1200 ሰዎች ህይወት አልፏል። አሁን ለጋዛ ዜጎች የሚያስፍልገው ጸሎት እና ጸሎት ብቻ ነው ብለዋል።

ፓስተር ዊሊያም ዴቭሊን በግብጽ፣ ጋዛ፣ ፓኪስታን፣ አፍጋኒስታን እና ጆርዳን የሚገኙ አናሳ ቁጥር ያላቸውን ክርስቲያኖች የሚያገለግል ሚኒስትሪ ይመራሉ።

ክርስቲያን መሪዎች ወደ ጋዛ ምድር ሄደው ለምን አይረዱም በሚል ጥያቄያቸውም ይታወቃሉ። ለአሁኑ ግጭትም ቢሆን የእስራኤልን ጦር እንዲሁም የሃማስ ጦር ይወቅሳሉ። በቬትናም ጦርነት ተዋጊ ነበርኩ የሚሉት እኚህ #ሰው በጦርነት ዋናዎቹ ተጎጂዎች ንጹሃን ናቸው ብለዋል።
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Please 🙏WATCH me
& #Register

#እግዚአብሔር የለም" በሚልበት በዚህች ዓለም ልጆችን

#እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደግሞም በሰውም ፊት የላቁ አድርጎ ማሳደግ እንዴት ይቻላል?

#ሁሉም ሊሰሙት #እና ሊማሩበት የሚገባ ...

የቀረን ጥቂት #ቦታ ነው #ብቻ በመሆኑ አሁኑኑ ይመዝገቡ

#ማሳሰቢያ ያለምዝገባ መግባት አይቻልም!!!

ልጆቻችንን የሚጠብቅልን የለም ብላችሁ አትስጉ #ልጆች እየተጫዉቱ የሚጠበቁበት #እኛ በቂ ቦታ አዘጋጅተናል።

#Register #Register #ይመዝገቡ #ይመዝገቡ #ይመዝገቡ

ለመመዝገብ ሊንኩን ይጫኑ /ይደውሉ
https://docs.google.com/forms/d/1XBwJuLL8hCAO1SA3E8aTmmg2y32G9jwY1PnG-BS8XXQ/edit?usp=drivesdk
0911136520/0988353423
#ደረሰ ደረሰ ደረሰ ...

የመጽሃፍ #ቅዱስ ሳምንት

#በኢትዮጵያ የመጽሃፍ ቅዱስ ማህበር አዘጋጅነት የሚካሄደዉ የመፅሐፍ ቅዱስ ሳምንት #እና የቅዱሳት መጻህፍት አውደ ርዕይ ከመጋቢት 16-21 በኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል።

ክርስቲያኑን #ስለ መጽሃፍ ቅዱስ ንባብ ማነቃቃት፣ በመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ የሚሰሩ አብያተ ክርስቲያናትን በተዛማጅ ስራዎች ላይ ማስተባበር፣ የወንጌል ስብከትን ማበረታት፣ ለአሁኑ ትውልድ የመጽሃፍ ቅዱስን አደራና ሃላፊነት ማስተላለፍ እና መጽሃፍ ቅዱስን ከአደጋዎች መጠበቅ በሳምንቱ ከሚኖሩ ክንውኖች መካከል ናቸው።

ትውልዱን ስለ ቅዱሳት መጻህፍት እንዲያውቅ ማድረግ፣ የህትመት ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ ማድረስ እና ማህበሩን ከህዝብ ጋር ማስተዋወቅ በአውደ ርዕይው የሚከናወኑ ዋና ዋና ስራዎች ናቸው።

#ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።

መግቢያ #በነፃ ...
#ሩስያ ወሰነች... የግብረ ሰዶም እንቅስቃሴ የሽብር ድርጊት ነዉ።

ሩሲያ የግብረ ሰዶም እንቅስቃሴን የአክራሪነት #እና የሽብር ድርጊት ዝርዝር #ውስጥ አካተተች

የሩሲያ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት ተቆጣጣሪው ሮስፊንሞኒቶሪንግ አለምአቀፍ የግብረሰዶም እንቅስቃሴን በአሸባሪነት እና በአክራሪነት ዝርዝር ውስጥ ማካተቱን የሩሲያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ውሳኔው የተደረሰው ሩሲያ ከሞስኮ የፍትህ ሚኒስቴር የቀረበለትን አቤቱታ ተከትሎ የግብረሰዶም ተከራካሪዎች አክራሪ ተብለው እንዲጠሩ በህዳር ወር ላይ የሩሲያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከወሰነ በኋላ ነው ተብሏል።

የሩሲያ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት አክራሪ ወይም አሸባሪ ተብለው የተፈረጁና በዝርዝሩ የሚካተቱ የግብረሰዶም አቀንቃኞችን ወይም ቡድኖችን የባንክ ሂሳቦች የማገድ ስልጣን ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።

#tikvahethmagazine
“ክርስቲያናዊ ኢትዮጵኝነት” በሚል ርዕስ በወንድም ዘላለም መንግስቱ ተዘጋጅቶ በሐዋሳ ሐይቅ ዳር ቃለ ሕይወት #ቤተክርስቲያን አሳታሚነት #እና አከፋፋይነት ለቅዱሳን በረከት ሊሆን ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡

ሚያዚያ 6/2016 በሐዋሳ ሐይቅ ዳር ቃለ #ሕይወት ቤተክርስቲያን ተገኝተው መጽሐፉን በእጆዎ በማስገባት ከቀዳሚ አንባቢያን መካከል ይሁኑ፡፡

መጽሐፉን ወንድማችን ዘላለም መንግስቱ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ያበረከተው ሲሆን ከመጽሐፉ ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ የወንጌሉን አገልግሎት ለመደገፍ ይውላል፡፡

ወንድማችን ዘላለም መንግስቱ ከአስር ያላነሱ የታተሙ መጽሐፍትን እና ከአስር ያላነሱ ያልታተሙ #ግን በsoft copy መጽሐፍትን ለቅዱሳን አገልግሎት እንዲውል ያበረከተ እና እያበረከተ ያለ ወንድም ነው፡፡

በእቅበተ ዕምነት አገልግሎት ግንባር ቀደም አገልግሎትን በተለያዩ መንገዶች እያገለገለ ያለ እና ከ25 ዓመታት በላይ #ጊዜ የወሰደውን የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አዘጋጅቶ #ወደ ማተሚያ #ቤት በመላክ በቅርብ ወራት ለቅዱሳን አገልግሎት እንዲውል ለማድረግ እየተጋ ያለ ትጉህ ወንድማችን ነው፡፡
#ዛሬ ይጠናቀቃል

“መጽሀፍ ቅዱሳዊ እሴቶችን በሕዝባችን #ሕይወት እናስርጽ!” በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየዉ የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ዛሬ ይጠናቀቃል።

በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን እና የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት መሪዎች በተገኙበት በመካሄድ #ላይ ይገኛል።

#የኢትዮጵያ መጽሐፍ #ቅዱስ ማሕበር አዘጋጅነት የመጽሀፍ ቅዱስ ሳምንት በዓል #እና የቅዱሳት መጻሕፍት ዐውደ ርዕይ ከሰኞ የጀመረ ሲሆን በዛሬዉ እለት የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ክርስቲያኑን #ስለ መጽሃፍ ቅዱስ ንባብ ማነቃቃት፣ በመጽሃፍ ቅዱስ ትርጉም ላይ የሚሰሩ አብያተ ክርስቲያናትን በተዛማጅ ስራዎች ላይ ማስተባበር፣ የወንጌል ስብከትን ማበረታት፣ ለአሁኑ ትውልድ የመጽሃፍ ቅዱስን አደራና ሃላፊነት ማስተላለፍ እና መጽሃፍ ቅዱስን ከአደጋዎች መጠበቅ በሳምንቱ ዉስጥ ሲሰራ የነበረ #ስራ ነዉ።

በሳምንቱ ዉስጥ ትውልዱን ስለ ቅዱሳት መጻህፍት እንዲያውቅ የማድረግ ስራ ፣ የህትመት ውጤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህዝብ ማድረስ እና ማህበሩን ከህዝብ ጋር ማስተዋወቅ በአውደ ርዕይው ሲከናወን ቆይቷል።

የኢትዮጵያ መፅሐፍ ቅዱስ ማሕበር ሁሉንም ሁሉንም አብያተ ክርስቲያናት እና ምዕመናንን ባለፋት 98 ዓመታት አገልግሏል።

ፎቶ 📷 Hossana production Hossana
#ክርስቶስ እንኳን #ወደ ምድር ቢወርድ #አንድ አዳራሽ መስሪያ ቦታ አይሰጣችሁም

#ክርስቲያኖች ላይ ስደት በዝቷል።

በደቡብ ምስራቅ አውሮፓ በምትገኘው ኮሶቮ፣ ክርስቲያኖች #ላይ ስደት በርትቷል ተባለ።

በሃገሪቱ ክርስቲያኖች #ምንም አይነት የመሰብሰብ መብት እንደሌላቸው #እና ፈቃድ ለማግኘትም ሁኔታዎች እንደሚወሳሰቡባቸው ገልጸዋል።

የአርሜ #ቋንቋ ተናጋሪዎች የሚበዙባት ኮሶቮ፣ 93 በመቶ ዜጎቿ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው።

ምንም #እንኳን የሃገሪቱ ህገ መንግስት የሃይማኖት ነጻነትን የሚፈቅድ ቢሆንም፣ ክርስቲያኖች ላይ ግን መድሎና አመጽ ይበረታባቸዋል።

#ይህ ስደት በግል ደረጃም፣ የቀብር ስፍራ መከልከል፣ ንብረት የማፍራት መብት አለማግኘትና ሌሎችም በደሎች እየደረሱባቸው እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በተለይ #ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች፣ የባንክ ሂሳብ መክፈት፣ ንብረት ማፍራት እና ሰራተኞችን ቀጥሮ የመንቀሳቀስ ዴሞክራሲያዊ መብቶች የላቸውም።

በቅርቡ የወጣ #አንድ ህግ ደግሞ የሰርቢያ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊኮችን እና ሌሎችንም ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናትን ኢላማ ያደረገ ነው ይባልለታል።

በሃገሪቱ ያለፉትን 25 ዓመታት ያገለገሉ አንድ ቄስ ሲናገሩ፣ ያለው ስቃይ በግልጽ ስላልሆነ ይበልጥ ከባድ ያደርገዋል ብለዋል።

ለቀብር እንኳን በሙስሊሞች የቀብር ስፍራ፣ በኢማሞች የተመራ ቀብር ስነ ስርዓት እያደርግን ነው የምንገኘው ብለዋል። ምንም ቢሆን #ግን ለሃገራችን የወንጌል ተስፋ አለን ሲሉም እኚሁ ቄስ ይናገራሉ።

በኮሶቮ በ1980ዎቹ ወንጌላዊያን፣ ክርስቶስ እንኳን ወደ ምድር ቢወርድ አንድ አዳራሽ መስሪያ ቦታ አይሰጣችሁም የሚል ተደጋጋሚ ዛቻ ከወቅቱ ኮሚኒስት መንግስት ሲደርስባቸው እንደ ነበረ ዘገባዉ አስታዉሷል።
#ቤተክርስቲያን እዉቅና ሰጠች።

ወንጌላዊ ጋሽ ቦጋለ ለማ ለረጅም አመታት በቀጠና #ሁለት #ሙሉ #ወንጌል ያገለገሉ #እና አጋሽ ቦጋለ ለማ ለረጅም አመታት በቀጠና ሁለት ሙሉወንጌል ያገለገሉ እና አሁን ደግሞ በአዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ውስጥ እያገለገሉ ይገኛሉ ይህንንም በማስመልከት ቤተክርስቲያን እውቅና ሰጥታለች።

ቤተክርስቲያን እንደዚህ ላሉ አገልጋዮች እውቅናና ክብር መስጠቷ እጅግ የሚያበረታታ እና ሊቀጥል የሚገባ ተግባር ነው።

Christian ዜማ Tube ገፅ የተወሰደ...
#ጅማ ክርስቲያን

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖ ካምፓስ የቀድሞ የ#ክርስቲያን ተማሪዎች ሕብረት (ኪቶ ፋሚሉ) አባል የነበሩ ተማሪዎች መልካም ግንኙነት ሊያስቀጥል የሚችል ክርስቲያን ኔትወርኪንግ ኢቨንት ተካሄደ።

#ይህ ለሁለተኛ #ጊዜ የተዘጋጀው ፕሮግራም በዋናነት ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ወጥተው በተለያዩ የግል የስራ ዘርፎች የተሰማሩ ተማሪዎችን ግንኙነት ማስቀጠል #እና የተሰማሩበትን የቢዝነስ ዘርፍ አስተዋውቀው #መልካም ግንኙነት እንዲፈጠር ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወንድም አቤኔዜር ማቴዎስ ለክርስቲያን ዜና ተናግሯል።

አቤኒዘር አክሎ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ አብዛኛውን ጊዜ ግንኙነቱ ሲቀጥል አይታይም ይህን ክፍተት ለመቀነስ ያሰበ መልካም ግንኙነት እንደሆነ ተናግሯል።

ይህ ሕብረት በቀጣይ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ውጪ የሚገኙ ሕብረትን ለማሳደግ እንደሚሰሩ ወጣት አቤኔዜር አክሎ ለክርስቲያን ዜና ተናግሯል።

ክርስቲያን #ዜና ያናገራቸው በፕሮግራሙ #ላይ የሚሰሩትን የተለያዩ ስራዎችን ይዘው የቀረቡ የቀድሞ ተማሪዎች ይህ የህብረት ፕሮግራም ከሌሎች ጋር የመተዋወቅን እና የቢዝነስ ስራ በጋራ ለማሳደግ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ነግረውናል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዘገባውን አዘጋጀን ተጨማሪ ዝርዝር መረጃ በክርስቲያን ዜና የዮቲዩብ ቻናል ይዘን እንመለሳለን።
#ብዙ ዋጋ የተከፈለበት #በኢትዮጵያ ትልቁ የመፅሐፍ #ቅዱስ መዝገበ ቃላት ተመረቀ።

በዘላለም #መንግስቱ ተጽፎ ከ1,300 ገጾች በላይ ተዋቅሮ ከ4,800 በላይ ቃላት ያካተተው ይህ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የጸሀፊው ወዳጆች በተገኙበት በCETC) ኢትዮጵያን ቴዎሌጂካል ኮሌጅ በድምቀት ተመርቆ ለአንባብያን ተሰራጭቷል።

በመድረኩ መጽሀፉን #ሙሉ በሙሉ ጽፎ ለማጠናቀቅ 23 ዓመታት እደፈጀ እና በዚህ ስራ #ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት ምስጋናውን አቅርቧል።

ዘላለም መንግስቱ በንግግሩ ይህ መፅሐፍ ማለት እንደ "ማንኪያ" ነው። ዋናው ምግቡ ግን "መፅሐፍ ቅዱስ" ነው። ያለ ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስን የበለጠ ለመረዳት የሚያግዝ መጽሐፍ እንደሆነ ተናግሯል።

አክሎም ምንም እንኳን እጨርሰዋለሁ ብዬ ባልጀምረውም ለብዙዎች የሚያግዝ በመሆኑ በእግዚአብሄር እርዳታ ተጠናቋል። ይህ መጽሐፍ በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ የተጻፈ እንደመሆኑ መጠን ይህ መጽሀፍ መጽሀፍ ብቻ ሳይሆን አደራም ጭምር ነው ሲል ተናግሯል።

በመድረኩ ንግግር ያደረጉ መሪዎች እረጅም አመታትን በትዕግት በመጻፍ ይህንን መጽሀፍ በዚህ ወቅት ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በማበርከቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ ዘመን ያለን አገልጋዮች ይህንን መጽሀፍ ባንጠቀምበት ፤ እና ባንሰራበት ለእኛ እዳ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ዘላለም መንግስቱ ከዚህ ቀደም መንፈስ ቅዱስ እና ካሪዝማዊ ቀውሶች ፤ እንዘምር ወይስ እንዝፈን ፤ ክርስቲያናዊ ኢትዮጵኝነት ፤ የሐሰተኞች እሳተ ጎመራ ፤ ትንቢተ ዕምባቆም ፤ የይሁዳ መልዕክትን ጨምሮ ወደ 20 የሚደርሱ መጽሀፍትን ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አበርክቷል።

#የኢትዮጵያ ቃለ #ሕይወት #ቤተክርስቲያን #ዋና ጸሐፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት #እና የአብያተክርስቲያናት መሪዎች በጽሎት መጽሀፉን መርቀው ለንባብ እንዲበቃ በይፋ መርቀውታል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ሙሉ ዘገባውን አሰናዳንላችሁ። በቻናላችን ስም ለወንድም Zelalem Mengistu የተሰማንን እጅግ ትልቅ ደስታ እየገለጽን ሁላችሁም ትጠቀሙበት ዘንድ እናበረታታለን።
#ሰው ተመኑ ስንት ነው?

በጋሽ ሽፈራው ወ/ሚካኤል የተጻፉ #ሁለት መጽሃፍት ተመረቁ።

መጻህፍቱ “የሰው ተመኑ ስንት ነው?” እና “የግለሰብ ሚና (እኔም ቁምነገር ነኝ)” ይሰኛሉ። መጻህፍቱን ያሳተመው አቢጊያ የሰላም ኢኒሼቲቭ ነው።

አቢጊያ የሰላም ኢንሺዬቲቭ፣ በጋሽ ሽፈራው ወ/ሚካኤል ሃሳብ አመንጪነት ከ35 ወንድሞች ጋር በመሆን ስለ ሃገር ሰላም ለመስራት ከጥቂት አመታት በፊት የተቋቋመ ነው። ፥ሁሉ በሰላም፣ ሁሉ ለሰላም በሚል መሪ ቃል የተቋቋመው ኢኒሽዬቲቩ ከወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እውቅና ተቀብሎ እየሰራ ይገኛል።

ኢኒሽዬቲቩ ተቋማት ስለ ሰላም በሰላም የሚለውን መርህ እንዲከተሉ፣ ስለ ሰላም ከሚሰሩ ጋር አብሮ መስራትና ስለ ሰላም በሰላም ለቆሙ እውቅና መስጠት የሚሰራባቸው ስልቶቹ እንደሆኑ አስታውቋል። ስራውንም በወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና የወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት መካከል የነበረውን ልዩነት ለማርገብ በመስራት ጀምሯል።

ኢኒሽዬቲቩ በረጅም ጊዜ እቅዱ፣ ስለ ስላም የሰውኣን የአዕምሮ ውቅር ለመለወጥ በትዕግስት መስራት ላይ አተኩሮ ይሰራል።

#አድዋ ሙዚየም አዳራሽ በተካሄደው ምረቃ መርሃግብር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱአለም፣ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጣሰው ገብሬ #እና የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝን ጨምሮ ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎችና የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ተመርቋል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በስፍራው ተገኝተን ዘገባውን አሰናዳንላችሁ።
#የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ #ኢየሱስ #ቤተክርስቲያን የማዕከላዊ #ደቡብ #ኢትዮጵያ ሲኖዶስ የልማት ኮሚሽን ፤ ኖሮዌ #ቤተክርስቲያን ተራዕዶ እና UN #women በጋር የሚተገብሩት Creating safe #city #and safe #public #space #project ጾታን መስረት ያደረገን ጥቃት ለመከላከል የሚስችል የግንዛቤ ማሳጨበጫ ፕሮግራም በሀዋሳ #ከተማ አካሄድ፡፡

በፕሮግራሙ #ላይ ከካቶሊክ ፤ ከወንጌል አማኞች #እና ከግሮት ኮሚሽን የተወጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

ጾታዊ ጥቃት/በሴቶችና ልጃገረዶች የሚደርሰውን ጥቃት የሚፅየፍ ትወልድ መፍጠር የሚል አላማ የነበረው ፕሮግራም እንደሆነ ተገልጿል።

በፕሮግራሙ ከአቶቴ #እስከ ታቦር መካነ #ኢየሱስ ቤ/ክ ድረስ የእግር ጉዞ የተደረገ ሲሆን በጉዞ ወቅት ተሳታፊዎች የተለያዩ የጹሁፍና የድምፅ መልዕክቶችን በማሰማት በሴቶችንና ልጃገረዶች #ላይ የሚደርሰውን ጥቃት አውግዘዋል፡፡

በተጨማሪም በግሬት ኮሚሽንና በሪፍራል መካነየሱስ ወንድ ወጣቶች #መካከል የእግር ኩዋስ #ውድድር የተካሄድ ሲሆን የውድድሩ አላማ ወንዶች ጾታዊ ጥቃትን ለመከላከል ያላቸውን ቁርጠኝነት ለማሳየት ነው።

ይህም ጥቃት የሚያደርስ ወንድ #ብቻ ሳይሆን የሚቃውም መሆኑን በማሳየት ተሳትፎቸውን ለመጨመር ነው፡፡
#የትግራይ የሀይማኖት አባቶች ፖለቲከኞች ልዩነቶችን ከማባባስ እንዲቆጠቡ አሳሰቡ።

አባቶቹ አክለዉ አለመግባባቶችን ለመፍታት #ውይይት እንዲደረግ ጠይቀዋል።

የትግራይ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ #ቤተክርስቲያን የሀይማኖት አባቶች የህዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (#ህወሓት) አመራሮች #እና የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ልዩነታቸውን ሊያባብሱ ከሚችሉ መግለጫዎች እንዲቆጠቡ ጠይቀዋል።

በትላንትናዉ #እለት በሰጡት መግለጫ፣ በተለይም በክልሉ ወቅታዊ ፈተናዎች #ውስጥ የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት መፍታት አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል ሲል #አዲስ እስታንዳርድ አስነብበዋል።

"አባቶቹ ጥሪውን ያቀረቡት የአሜሪካው አምባሳደር ሁለቱንም ቡድኖች በመቀሌ ካነጋገሩ በኋላ ነው"

#Ethiopia #addisababa #news #NewsUpdate #BREAKING #BreakingNews
በአገራችን #ታሪክ በህክምና ቁሳቁስ አቅርቦት፣ ጥገና እና አገልግሎት አሰጣጥ መስክ በቁጥር #አንድ ደረጃ በግንባር ቀደምነት አስተዋጽዖ ያበረከቱት (ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ)
በዘርፉ የተለያዩ ኩባንያዎች ያቋቋሙት

በደርግ ዘመን ለቀበሌም ለቤተክርስቲያንም በረከት በመሆን የተሸለሙ #እና ቤተክርስቲያን እንዳትዘጋ መሣሪያ የሆኑ

በኑሮአቸው በቃላቸው እና በሃብታቸው ጌታቸውን በማገልገል ከቤተሰባቸው ጋር እውነተኛ የደቀመዝሙርነት ሕይወትን በብዙ ትጋት ያሳዩት የመርጋ ሰርቤሳ ታሪክ መጽሐፍ ዝግጅት ተጠናቆ እነሆ መስከረም 4 ቀን በአቃቂ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ይመረቃል።

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።