The Christian News
5.15K subscribers
3.04K photos
25 videos
714 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
ኦቲዝም ጥላ ስር የሚኖሩ ልጆች ያሏቸው ወላጆች ከቤታቸው ሳይወጡ እስከ ሁለት እና ሶስት አመታት ይቆያሉ። እነዚህ ልጆች ግን አስፈላጊውን ክትትልና እንክብካቤ ከተደረገላቸው እንደማንኛውም ልጅ ትክክለኛ እድገት ማደግ እና ምርታማ ዜጋ መሆን እንደሚችሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ይናገራሉ።

ቻምፒየንስ አካዳሚ የኦቲዝም ግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም አካሄደ። ትምህርት ቤቱ ለልዩ ፍላጎት ልጆች ልዩ የትምህርት ክፍሎችን በማዘጋጀት፣ በአዲሰ አበባ ከተማ አገልግሎትን እየሰጥ ይገኛል።

አካዳሚው ይሄንን የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃግብር ሲያዘጋጅ ይህ ለዘጠነኛ ጊዜ ነው።
በግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብሩ፣ ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች መዝሙሮች፣ እንቆቅልሽ፣ ድራማ እና ሌሎችም የመድረክ ላይ ዝግጅቶች አቅርበዋል። ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች ወላጆችና በኦቲዝም ጥላ ስር የሚኖሩ አዋቂዎችም ልምድ አካፍለዋል።

የመርሃ ግብሩ አዘጋጅ መዓዛ መንክር፣ በክርስቲያኖች ዘንድ ኦቲዝም ጥላ ስር ያሉ ልጆች እንደ መንፈስ እና እርግማን የመቁጠር የተሳሳተ ግንዛቤ አለ፣ ይሄንንም ወደ ባለሙያ በመምጣትና በማማከር የልጆችን ጊዜ መቆጠብና ቀድመው ክትትል በማድረግ ችግሩን መቅረፍ ይቻላል ብለዋል።

ለክርስቲያን ዜና ሃሳባቸውን የሰጡ ወላጆች፣ ምንም እንኳን በኦቲዝም ጥላ ስር ያለ ልጅ ማሳደግ ከባድ ቢሆንም፣ በቂ ክትትል እና እንክብካቤ ሲደረግላቸው ልጆቻችንን ይበልጥ እንድንወዳቸው እና ሁኔታቸውን የሚመስል እንክብካቤ እያደረጉ ሁኔታውን ማሸነፍ መቻላቸውን ገልጸዋል።

መዓዛ መንክር “ሁሉም በአንድ” የሚል ስለ ኦቲዝም እና ሁኔታው የሚያስረዳ መጽሃፍ ጽፋለች።

በአለማችን ላይ ድከሚወለዱ 100 ህጻናት አንዱ በኦቲዝም ጥላ ስር የሚኖር መሆኑን WHO መረጃ ያሳያል።
ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት ተፈፀመባቸው

በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚዘዋወር ስብከታቸው የሚታወቁት ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ተገለጸ !

በአሦርያውያን ቤተ ክርስቲያን የአውስትራሊያ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በእንግሊዝኛ እና ዐረብኛ ቋንቋዎች በሚያስተላልፉት ስብከት የሚታወቁ ሲሆን በሲድኒ በሚገኝ አንድ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ሳሉ በአንድ ግለሰብ አማካይነት በስለት መወጋታቸው ተገልጿል።

የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስም ጥቃቱን የፈፀመውን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል። የኒው ሳውዝ ዌልስ የአምቡላንስ አገልግሎት በዕለቱ ጥቃቱ በደረሰበት ወቅት አራት ሰዎች ቆስለዋል ብሏል።

ሊቀ ጳጳሱ የሕክምና እርዳታ ተደርጎላቸው በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተዘግቧል።

በዕለቱ በሠላሳዎቹ ውስጥ ከሚገኝ ወጣት በተጨማሪ በከባድ ሁኔታ ወደ ሆስፒታል የተወሰደው በሀምሳዎቹ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሰው መኖሩንና በርካታ ቦታዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰበት ለመገንዘብ ተችሏል።

ጥቃቱን የሚያሳየው ቪዲዬ >>>>> https://vm.tiktok.com/ZMMCA7PVT/
#የወንጌል ዘመቻ ሊካሄድ ነዉ።

ጋፕስ አለም አቀፍ አገልግሎት
አንጾኪያ የወንጌል እንቅስቃሴ

ጋፕስ ያለፉትን 14 ዓመታት የአገልጋዮችን የኑሮ ክፍተት መሙላት፡ የመንፈሳዊ ክፍተት መሙላት (ማጎልበት፡ ማስተማር) ላይ ሲሰራ ቆይቷል።

አንጾኪያ የወንጌል እንቅስቃሴ የ10 ቀናት የወንጌል ዘመቻ በነገው እለት ጀምሮ ከሚያዝያ 9-19 ድረስ ይካሄዳል።

ዘመቻው፡ የቡና #ሻይ ሰዓትን ለወንጌል፡ ሙስሊም ኢቫንጀሊዝም፡ የደም ልገሳ፡ የጎዳና ወንጌል፡ #አንድ #ሰው ለኢየሱስ፡ ማህበራዊ ሚድያን ከወንጌል፡ አርትን ለወንጌል፡ በመርዳት ወንጌል መስበክ፡ ሙዚቃን ለወንጌል፡ የርህራሄ አገልግሎት በዘመቻው በየእለቱ የሚሰሩ ስራዎች ናቸው።

የጋፕስ ሚኒስትሪ መስራችና መሪ መጋቢ ዳንኤል ዋለልኝ ሁሉም ሰው የተልዕኮ ሰራተኛ መሆኑን ማወቅ ይኖርበታል፡ በእነዚህ 10 ቀናት ሁሉም #ክርስቲያን አንጾኪያ በሚያደርገው የወንጌል ዘመቻ እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

የክርስቲያን መገናኛ ብዙሃንም በዚህ የወንጌል ዘመቻ በትልቅ ተሳትፎ እንዲሰራ፡ የክርስቲያን ጋዜጠኞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዘሪሁን ግርማ ጥሪ አቅርበዋል።

አንጾኪያ ሙቭመንት #አዲስ የወንጌል ተኮር አገልግሎት ነው። አላማው በሐዋ ስራ 11 እንደተገለጸው፡ የአንጾኪያ ቤ/ክ የወንጌል አካሄድ መድገም ነው።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና መግለጫውን በስፍራዉ በመገኘት አሰናዳንላችሁ።
#አስደሳች #ዜና ካህን #የክርስቲያን ባዛር ሊደረግ ነው።

በመልህቅ ፕሮዳክሽን እና ኢቨንት አዘጋጅነት "ካህን" የተሰኘ እና ጀማሪ እና መካከለኛ የንግድ ስራ ላይ የተሰማሩ #ክርስቲያን ነጋዴዎች የሚሳተፉበት የክርስቲያን ባዛር ሊካሄድ ነው።

ሚያዝያ 12/2016ዓ.ም ቅዳሜ በሚደረገው ፕሮግራም ላይ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች፤ ታዋቂ የኪነ ጥበብ ሰዎች ፤ ወጣት እና አንጋፋ ዘማሪዎች በክብር እንግድነት ተገኝተው በድምቀት እንደሚከፍቱት አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

በመረሃ ግብሩ የክርስቲያን ባዛር የአምልኮ #ጊዜ የተለያዩ ጨዋታዎች የሚዲያ ሽፋን እንዲሁም ለክርስቲያን ቲክቶከሮች ማበረታቻ የሚሰጥበት ጊዜ እንደሚኖር ታውቋል።

#ቦታ ብሔራዊ ትያትርን ተሻግሮ በከተማና ልማት አዳራሽ ከማለዳው 2:30 ጀምሮ እስከ ምሽት 2:00ሰዓት ይከወናል።

ሁላችሁም ተጋብዛችኋል። ይጎብኙ ፤ ይሸምቱ ፤ አብረውን ያምልኩ።
ሕብረቱ በአድዋ ሙዝየም ፕሮግራም ሊያካሂድ ነዉ።

ፓስተር ጻድቁ አብዶ አድዋ 00 ስለሚካሄደው ስብሰባ መግለጫ ሰጡ!

የኢትዮጵያ ወንጌላዉያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ለ5300 የቤ/ክ መሪዎች ከሚያዝያ15-17 በአድዋ 00 ሙዚየም አዳራሽ ውስጥ ነው ስልጠናው የሚሰጠው።

ስልጠናው "የወንጌል ተልዕኮና የእርቅ መንገድ ለኢትዮጵያ ቤ/ክ" በሚል መሪ ቃል ይካሄዳል።

ሮሜ 14ን መሰረት አድርጎ፡ ሰላምና እርቅ፡ ወንጌል ተልዕኮ፡ መንፈሳዊ ስምረት እና ጽኑ አመራርነት ላይ ትኩረት ያደርጋል ብለዋል የህብረቱ ስነ መለኮት መምሪያ ሃላፊ ፓስተር ደረጀ።

የስልጠናው ወጪ ከአባል ቤተ እምነት እና ሚኒስትሪዎች በተገኘ ድጋፍ ነው የተሸፈነው። በስፍራው ምዝገባ ያደረጉ ሰዎች ብቻ መገኘት የሚችሉ መሆኑ በመግለጫ ተነስቷል።

ህብረቱ በቀጣይ 10 ዓመታት መንፈሳዊ ተሃድሶ፡ መንፈሳዊ መነቃቃትና እርቅና ተሃድሶ የትኩረት አቅጣጫዎቹ ናቸው።

ከዚህ ቀደም ህብረቱ መሰል ስልጠና በኤልያና ሆቴልና ሚሊኒየም አዳራሽ መሰጠቱ ይታወሳል።
#አፍሪካ

አፍሪካ ባለፉት 150 አመታት በርካታ ክርስቲያናት ያሉባት አህጉር ሆናለች።

በ1900 #ላይ በአለም ካለው #ክርስቲያን 82 በመቶው፣ በሰሜን የአለም ክፍል፣ አውሮፓ እና #አሜሪካ ይገኝ ነበረ። በተቃራኒው ደቡባዊ የአለም ክፍል አፍሪካ፣ እስያና ላቲን አሜሪካ ደግሞ 18 በመቶ ብቻ ነበረ።

#አንድ #መቶ አመታትን #ወደ ፊት፣ ሰሜኑ አለም 33 በመቶው #ብቻ ክርስቲያን ሲሆን፣ ደቡቡ የአለም ክፍል ደግሞ 67 በመቶ ክርስቲያን ነው።

በጋና አክራ፣ በተካሄደ አለም አቀፍ የክርስቲያኖች ፎረም፣ በአለም ላይ የክርስትና ህዝብ ነክ ቁጥር ትልቅ ለውጥ ማሳየቱ ተነስቷል። ከኤፕሪል 16-20 በነበረው በዚህ ፎረም ከ60 የተለያዩ ሃገራት የተወጣጡ ከ240 በላይ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።

በዚህ ለውጥ ውስጥ ሴቶች ያላቸው ሚና እጅግ ታላቅ ነው ተብሏል። ወደፊት በተቀመጠ ትንበያ መሰረት ደግሞ በ2050፣ 77 በመቶ ክርስቲያኖች በደቡቡ የአለም ክፍል የሚኖሩ ይሆናል።

እነዚህ የአሃዝ ለውጦችና ትንበያዎች ወደፊት የክርስትና ማዕከል የትኛው የአለም ክፍል እንደሚሆን ያሳያል ተብሏል።

ለአብነት በአውሮፓና አሜሪካ የክርስትና ቁጥር በፍጥነት እየቀነሰ ሲሆን፣ በተቃራኒው በአፍሪካና እስያ ደግሞ በፍጥነት እያደገ
#ሬማ በድምቀት #ተመረቀ

ለዝማሬ አገልግሎት ከፍተኛ አሶተዋፅኦ የሚሰጥ ሬማ ሪከርዲንግ ስቱዲዮ ሚያዚያ 12 ቀን 2016ዓ/ም ተመርቆ ለአገልግሎት በቃ።

የስቱዲዮዉ ባለቤት ሙዚቀኛ ዳዊት ወርቁ በቤተክርስቲያን ዉስጥ ለረዥም አመታት ያገለገለ #ወጣት አገልጋይ ሲሆን ሬማ ሪከርዲንግ ስቱዲዮ ለትርፍ ያልተቋቋመ እና በዋነኝነት ተማሪዎችን እና የዝማሬ ፀጋ ያላቸዉን ለማገልገል የተዘጋጀ መሆኑን ገልፃል።

በምረቃ ስነስረአቱ ላይ ስቱዲዮዉን በፀሎት የመረቁት አፖስትል ብስራት ብዙአየን(ጃፒ) “አሁንም ቤተክርስቲያን ለሙዚቀኞች ትኩረት ልትሰጥ ይገባል የቤተክርስቲያን ሙዚቃ የአለምን ሙዚቃ መዋጥ አለበት” ሲሉ ተናግረዋል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለወንድማችን ሙዚቀኛ ዳዊት የተሰማን ደስታ እንገልፃለን።
በ18 አመቴ ሀኪም ትሞታለህ እንጅ አትተርፍም ከሆስፒታል ውጣ አለኝ።

#እኔ ደግሞ #ዛሬ በ78 ዓመቴ ኢየሱስ ያድናል እላለሁ!

ዶ/ር ቤተ መንግስቱ

ስንመለከታቸዉ እረጋ ያሉ በአገልግሎት ከኬኒያ እስከ አሜሪካ ከአሜሪካ እስከ ኢትዮጵያ የጉባኤ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያን ምስረታ ቀዳሚ የነበሩ።

ዶ / ር ቤተ መንግስቱ በአሁኑ ሰዓት በተልይ "አፍሪካ ተነሺ" በሚል አለም አቀፋዊ ጉባኤ የምትታወቀዉን የቤዛ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን እየመሩ ይገኛሉ።
♦️ በቅርብ ቀን♦️

"የአማኝ ህይወት" በሚል ርእሰ የተፃፈ ድንቅ መፅሐፍ ወጣት አገልጋይ ካሌብ ይዞልን እየመጣ ሲሆን

በቅርብ #ቀን በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።
The Christian News pinned «ተለቀቀ !!! #እኔ አገልጋይ ነኝ እያየሽ ግቢበት ነው ያልኳት ያልተሰሙ #አስገራሚ እና #አዝናኝ የተወዳጁ አገልጋይ #ዘማሪ እንዳለ ወ/ጊዮርጊስ እና ቤተሰቡ የበዓል ቆይታ https://youtu.be/tOWD7qwfcDo»