አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ
183K subscribers
4.94K photos
156 videos
14 files
750 links
ስሜት፣ እምነት፣ ወኔ፣ ፍቅር፣ አልሸነፍ ባይነት የሚንፀባረቅበት የታላቁ ክለብ ኢትዮጵያ ቡና ቻናል ነው። ይህ ቻናል ሰለ ውዱ ክለባችን ኢትዮጵያ ቡና 24 ሰዐት መረጃዎችን በፍጥነት ወደእናንተ ያደርሳል።

ለማንኛውም አስተያየት እና መረጃ
@UTD14
@Bunnacoffee12

መወያያ ግሩፕ ➲ @BunnaFC
Download Telegram
አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ
👆👆👆 @coffeefc 👆👆👆

✔️ #ቅድመ_ጨዋታ_ዳሰሳ |

☕️ #ኢትዮጵያ_ቡና#ባህርዳር_ከተማ 🎽

በ21ኛው ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች መካከል በአዲስ አበባ ስታድየም የሚደረገውን #የኢትዮጵያ_ቡናን እና #ባህር_ዳር_ከተማን ጨዋታ በቅድመ ዳሰሳችን ተመልክተነዋል።

➡️ ባለፈው ሳምንት መቐለን ድል በማድረግ የፕሪምየር ሊግ ጉዟቸውን እያስተካከሉ ያሉት ባህር ዳሮች ዛሬ ደግሞ ሌላኛውን የአዲስ አበባ ክለብ ኢትዮጵያ ቡናን ከሜዳቸው ውጭ ያስተናግዳሉ።

📜 ዘንድሮ ወደ ሊጉ ከመጡ ሌሎቹ ክለቦች በተሻለ ሁኔታም ሰባተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። ሳምንት ከወላይታ ዲቻ ጋ ተጫውተው አቻ የነበሩት ቡናዎች የዲቻው ሄኖክ ባስቆጠራቸው ሁለት ጎሎች በመሸነፋቸው ኢትዮጵያ ቡናዎች ወደ መሪዎቹ የሚጠጉበትን ዕድል መቀጠል ይችሉ የነበሩበትን ዕድል አበላሽተዋል ።

📄 #በመሆኑም እስካሁን ሁለቱ ክለቦች በሚገናኙበት ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ሙሉ ነጥብ በማግኘት ከተጋጣሚው ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለመስተካከል ባህርዳር ደግሞ ሦስት ነጥብ ይዞ በመመለስ የሳምንቱን ውጤት ለመድገም እንደሚፋለሙ ይጠበቃል።

📈 #በሌላ_በኩል ጉዳት ላይ ከነበሩት የኢትዮጵያ ቡና ተጫዋቾች መካከል ግዙፉ አጥቂ #ሱለይማን_ሉኮዋ ፣ ተከላካዩ #ተመስገን_ካስትሮ#ሚኪያስ_መኮንን#ንታምቢ እንዲሁም በረኛው #ዋቴንጋ አሁንም ጉዳት ላይ የሚገኙ በመሆኑ ከዛሬው ጨዋታ ውጪ ሆነዋል።

💧 💧#ባህር_ዳር_ከተማ ከሜዳውም ውጪ በማጥቃት ላይ የተመሰረተ አጨዋወትን የሚተገብር ከመሆኑ አንፃር ሲታይ የዛሬው ጨዋታ ፈጠን ያለ እና በሙከራዎች የታጀበ እንደሚሆን ይገመታል።

💧 #ባህር_ዳሮች ከኋላ ተመስረተው የሚመጡ ኳሶችን በዋነኝነት #በዳንኤል_ኃይሉ እና #ኤልያስ_አህመድ የአማካይ ክፍል ጥምረት ለሦስትዮሹ የፊት መስመር ጥምረታቸው ግብዓት የሚያደርጉ ይሆናል።

🦋 ይህም ሁለቱ የማጥቃት አማካዮች #ከሄኖክ እና #አማኑኤል_ዮሃንስ ጋር የሚገናኙባቸውን ቅፅበቶች እንድንጠብቅ ያደርገናል።

▪️ ከዚህ በተጨማሪም በማጥቃት ላይ አብዝተው የሚሳተፉት የኢትዮጵያ ቡና የመስመር ተከላካዮችም ከባህር ዳር የመስመር አጥቂዎች ከነ #ግርማ_ዲሳሳ ጋር ከባድ ፍልሚያ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

📌 #የእርስ_በርስ_ግንኙነት_እና_እውነታዎች

📍 ክለቦቹ በፕሪምየር ሊጉ ታሪክ የሚገናኙበት ሁለተኛው ጨዋታ ይሆናል።

🌼 በአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ፍጻሜ ጥቅምት ወር ላይ ተገናኝተው ኢትዮጵያ ቡና አሸንፎ ዋንጫ ማንሳቱ የሚታወስ ነው፡፡ ነገር ግን በ ፕሪምየር ሊጉ በመጀመርያው ዙር ባህር ዳር ከተማ ኢትዮጵያ ቡናን ማሸነፉ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው ።

💧 #ባህርዳር_ከተማ ካደረጋቸው 20 ጨዋታዎች ባለፈው ሳምንት ውጤት በማስመዝገቡ በ 32 ነጥብ 5ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ በአንፃሩ #ኢትዮጵያ_ቡና በ 20 ጨዋታ ባለፈው ሳምንት በዲቻ በመሸነፉ በ 29 ነጥብ 9ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል ።

🔻 #ግምታዊ_አሰላለፍ 🔻

☕️☕️ #ኢትዮጵያ_ቡና (4-3-3)

#ወንደሰን

👤 #አህመድ_ረሺድ
👤 #ቶማስ_ስምረቱ
👤 #እያሱ_ታምሩ
👤 #ተካልኝ_ደጀኔ

👤 #ሄኖክ_ካሳሁን
👤 #አማኑኤል_ዮሐንስ
👤 #ካሉሻ_አልሀሰን

👤 #ሁሴን_ሻባኒ
👤 #አቡበከር_ነስሩ
👤 #አስራት_ቱንጆ

#ሁሌም_እንደምንለው_መልካም_ዕድል_የሀገሩን_ስም_ከፊት_ላስቀደመው_ኢትዮጵያ_ቡና

አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ
👆👆👆 @coffeefc 👆👆👆


#ቡንዬ_የኔ የሚለው መዝሙር ተመረቀ

#ሁለተኝ ዙር ከቡና ሰማይ ስር አመታዊ የተጫዋቾች ሽልማት ምክንያት በማድረግ መዝሙር ተለቋል

#ግጥም_ሲሳይ (ሲስኮ ጥላ ፎቅ)
እና #ሄኖክ_ተገኝ
#ዜማ_ሲሳይ (ሲስኮ ጥላ ፎቅ )
እና #ቤባ(እዬብ)
ድምጽ #ትግስቱ (ማርኮናል)
#መቅደስ
#ቤባ(እዬብ)
#ህፃን #ሶፈንያስ_ጌትነት
#ሙዚቃ ቅንብር #ታምሩ_አማረ (ቶሚ)
#ፕሮዲውሰር ከቡና ሰማይ ስር ፔጅ

#ልዩ_ምስጋና ከ ቤባ
በጣም ለምወደው እና ለማከብረው ሙዚቃ አቀናባሪ ለ #ታምሩ_አማረ ለ ድምጻዊ #ትግስቱ( ማርኮናል) እንዲሁም በቅርቡ እዲስ ነጠላ ስራዋን ለምትለቀው ድምጻዊት #መቅደስ በመጨረሻም #ለጋደኞቼ እና ይህ ስራ ከመነሻው ተስርቶ እስኪያልቅ በሀሳብም በአቅምም ላገዙ ላበረታቱን በሙሉ

ኢትዮጰያ_ቡና ለዘላለም ይኑር


👆አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ 👆
👉👉 @coffeefc 👈👈
👉👉 @bunnafc 👈👈
ቅድመ ዳሰሳ | ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ኢትዮጵያ ቡና

የስድስተኛ ሳምንት መክፈቻ የሆነውን የሸገር ደርቢ የተመለከተው ዳሰሳችንን እነሆ።

የመዲናይቱ ሁለት ክለቦች ከድል መልስ የሚገናኙበት ተጠባቂ ጨዋታ ነገ ረፋድ ላይ ይከናወናል።

በእርግጥ ባለፉት ዓመታት የሸገር ደርቢ በሜዳ ላይ የታሰበውን ያህል ፉክክር ሳያሳየን የጎል ድርቅም እየመታው ሲጠናቀቅ ቆይቷል።

ይህ መሆኑ ተጠባቂነቱን ባይቀንሰውም ጓጉቶ ለሚጠብቀው የስፖርት ቤተሰብ የሚጠበቀውን ያህል አዝናኝ አለመሆኑ ቅሬታን የሚፈጥር ነው።

ለዚህ እንደአንድ ምክንያትነት የሚነሳው የሜዳ ላይ ጡዘቱ ወደ ደጋፊዎች ግጭት እንዳያመራ የመሰጋቱ ነገር ዘንድሮ በኮቪድ 19 ምክንያት ጨዋታዎች በዝግ በመካሄዳቸው የማይኖር በመሆኑ ጨዋታው ከፍ ያለ ፉክክር እንዲኖረው በር ሊከፍት እንደሚችል ይገመታል።

የቡድኖቹ ተጨዋቾችም ቀለል ባለ ጫና ውስጥ ሆነው ሲገናኙ የተሻለ ብቃታቸውን አውጥተው ለመጨወት ዕድል እንደሚያገኙም ይታሰባል።

ከሰባት ቀናት በኋላ ወደ ጨዋታ የሚመለሰው ቅዱስ ጊዮርጊስ ሦስት ተከታታይ ድሎችን በማሳካት መልካም አቋም ላይ ይገኛል።

ከማሸነፍ በዘለለ በየጨዋታዎቹ ያስቆጠራቸው ግቦች ቁጥር ከፍ ማለትም ከእንደነገው ዓይነት ጨዋታ በፊት የቡድኑን በራስ መተማመን ከፍ ለማድረግ የሚረዳ ሌላው በጎ ነጥብ ነው።

ወደ ቀደመ የቀጥተኛነት አጨዋወቱ የማዘንበል ባህሪ እየታየበት ያለው ጊዮርጊስ ከተከላካይ ጀርባ የሚገኙ ክፍተቶችን በአግባቡ በመጠቀም ጥንካሬውን ማሳየት ችሏል።

ነባሮቹም ሆኑ አዳዲሶቹ ፈራሚዎች ግብ በማስቆጠር እና ጨዋታ ለዋጭ ተፅዕኖዎችን በመፍጠር እያሳዩ ያሉት ብቃት ቡድኑ አማራጮች እንዲሰፉለት ጨዋታው ቢከብደው እንኳን በተጫዋቾች የግል ብቃት የሚገኙ ግቦችን ለማስቆጠር የሚረዳው ጉዳይ ነው።

በተለይ ኢትዮጵያ ቡና ከኃላ መስመር ላይ ከሚሰራው ተደጋጋሚ ስህተት አንፃር የፈረሰኞቹ ቀጥተኝነት እና ፊት ላይ ያሉ ተሰላፊዎቻቸው ፍጥነት ተጠቃሚ ሊያደርጋቸው እንደሚችል ይገመታል።

ቡድኑ መሀል ሜዳ ላይ ኳስን የማቆየት ሀሳብ ካለው ግን የተሻለ ውህደት ባለው ተጋጣሚው መፈተኑ የሚቀር አይመስልም።
ኢትዮጵያ ቡና እንደተጋጣሚው ረዘም ያለ የማገገሚያ ጊዜ ባይኖረውም ከኋላ ተነስቶ ያሸነፈበት የሰበታው ጨዋታ ትዝታ ትኩስ መሆኑ የቡድኑ ጉልበት ላይ የሚጨምርለት አዕምሯዊ ጥንካሬ ይኖራል።

የኳስ ቁጥጥር የበላይነትን አብዝተው የሚፈልጉት ቡናማዎቹ እንደ ሰበታው ጨዋታ ታታሪነት የታከለበት እና የፊት መስመር ተሰላፊዎች እገዛ ያልተለየው እንቅስቃሴ የመሀል ሜዳውን ጦርነት ለማሸነፍ ትልቅ እገዛ ያደርግላቸዋል።

እንደ #ዊሊያም_ሰለሞን እና #ሬድዋን_ናስር ዓይነት ወጣት ተጫዋቾቻቸው ጭምር ቡድኑ ለሚፈልገው አካሄድ በጨዋታ ጭምር ተፈትነው ለደርቢው መድረሳቸውም ለቡድኑ ተጨማሪ ኃይል ይሆነዋል።
ምንም እንኳን ከተጋጣሚው በራሱ ሜዳ ከፍ ያለ ጫና ሊደርስበት እንደሚችል ቢገመትም ያንን የሚያልፍበት ጥሩ ዕቅድ ከኖረው የጊዮርጊስን የአማካይ ክፍል ተጋፍጦ የመጨረሻ ኳሶችን ለማድረስ የተሻለ ዕድል ይኖረዋል።
ይህን ለማድረግ ግን ተደጋጋሚ ለውጦች የተደረጉበት የቡድኑ የተከላካይ አማካይ ተሰላፊ ሚና ከፍ ያለ ነው።

ፊት መስመር ላይ ያሉት የቡድኑ ተሰላፊዎችም እንዲሁ ከግብ አስቆጣሪነቱ ሳይቦዝኑ ለጨዋታው መድረሳቸው ለአሰልጣኝ #ካሳዬ ቡድን ጥንካሬን የሚያላብስ ነው።
ቡድኑ ከኋላ ያለከፍተኛ ጫና ሲሰራቸው እና ዋጋ ሲያስከፍሉት የሰነበቱት ስህተቶች ግን ነገ ከበድ ባለ ጫና ዳግም የመፈተሻቸው ነገር ስጋት የሚጭር ይሆናል።

በቡድኖቹ የተሻለ የማጥቃት ተሳትፎ ያላቸው ተከላካዮች #ሄኖክ_አዱኛ እና #ኃይሌ_ገብረትንሳይ ወደ ፊት ለመሄድ ከተቃራኒ ቡድን የመስመር አጥቂዎች የሚገጥማቸው ፈተና ፣ #ታፈሰ_ሰለሞንን ከሙላለም መስፍን ያሚያጋፍጡ ቅፅበቶች ፣ የጊዮርጊሶቹ አቤል ያለው እና አዲስ ግደይ ከቡና የተከላካይ መስመር ፊት እና ኃላ ያሉ ቦታዎች ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ ፣ የቡና መስመር አጥቂዎች በጊዮርጊስ መሀል እና መስመር ተከላካዮች መሀል ለመግባት የሚያደርጉት ጥረት እንዲሁም የጌታነህ ከበደ እና የ#አቡበከር_ናስር ከተከላካይ መስመር ጋር የሚኖራቸውን ግብግብ በነገው ሸገር ደርቢ የምንጠብቃቸው የሜዳ ላይ ፍልሚያዎች ይሆናሉ።

ጉዳት እና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ የቡድን ዜናዎችን ለማካተት ያደረግነው ጥረት በሁለቱም ክለቦች በኩል መረጃ ባለማግኘታችን አልተሳካም።

እርስ በእርስ ግንኙነት
– ሁለቱ ቡድኖች በሊጉ 40 ጊዜ ተገናኝተው ቅዱስ ጊዮርጊስ 18 ጨዋታ ሲያሸንፍ፤ ኢትዮጵያ ቡና 6 ድል አሳክቷል። በ16 ጨዋታዎች ደግሞ አቻ ተለያይተዋል።
– የሸገር ደርቢ ምንም እንኳ አሁን አሁን ያለ ግብ የሚጠናቀቅባቸው ጨዋታዎች በርከት ቢሉም ባለፉት 40 ግንኙነቶች 73 ጎሎች ተቆጥረዋል። ቅዱስ ጊዮርጊስ 49፤ ኢትዮጵያ ቡና ደግሞ 24 ጎሎች ማስቆጠር ችለዋል።

ግምታዊ አሰላለፍ
ቅዱስ ጊዮርጊስ (4-2-3-1)
ፓትሪክ ማታሲ
ሄኖክ አዱኛ – ምንተስኖት አዳነ – አስቻለው ታመነ – ፍሪምፖንግ ሜንሱ
ሀይደር ሸረፋ – ሙሉዓለም መስፍን
አቤል ያለው – ሮቢን ንጋላንዴ – አዲስ ግደይ
ጌታነህ ከበደ

ኢትዮጵያ ቡና (4-3-3)
ተክለማሪያም ሻንቆ
ኃይሌ ገብረትንሳይ – ወንድሜነህ ደረጄ – አበበ ጥላሁን – አሥራት ቱንጆ
ታፈሰ ሰለሞን – ረመዳን ናስር – ፍቅረየሱስ ተወልደብርሀን
አቤል ከበደ – ሀብታሙ ታደሰ – አቡበከር ናስር
© ሶከር ኢትዮጵያ

👆አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ 👆
👉👉 @coffeefc 👈👈
👉👉 @bunnafc 👈👈