አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ
165K subscribers
4.85K photos
148 videos
14 files
740 links
ስሜት፣ እምነት፣ ወኔ፣ ፍቅር፣ አልሸነፍ ባይነት የሚንፀባረቅበት የታላቁ ክለብ ኢትዮጵያ ቡና ቻናል ነው። ይህ ቻናል ሰለ ውዱ ክለባችን ኢትዮጵያ ቡና 24 ሰዐት መረጃዎችን በፍጥነት ወደእናንተ ያደርሳል።

ለማንኛውም አስተያየት እና መረጃ
@UTD14
@Bunnacoffee12

መወያያ ግሩፕ ➲ @BunnaFC
Download Telegram
ሰበር መረጃ

በቡና እና ኬንያ ፖሊስ ጨዋታ ዙርያ

ባለፈው ካፍ የቅድመማጣርያ ኣስተናጋጅ ስታድየም ሲዘረዝር።ኢትዮጵያ ምንም የተመዘገበ ኣልነበራትም።እንዲሁ የቡና ተጋጣሚ ፖሊስ ኤፍሲ ሀገር ኬንያም ምንም የተመዘገበ ኣልነበራትም።ታድያማ ይህን ጉዳይ በተመለከተ ባጋራውት ፖስት ላይ "ኣዎ ስታድየም የለንም ነገር ግን ኣሁንም ግዜ ኣለ ምክንያቱም ካፍ ያወጣው ዝርዝር መጨረሻ ላይ ለቅድመማጣርያ ሚበቃ ስታድየም ኣለኝ ሚል ካለ ዝርዝሩ ኣፕዴት ይደረጋል" ይላል ስለዚ ኣሁንም ጠብቁ ብያቹ ነበር።ታድያማ ኣዲሱ ነገር ምን መሰላቹ ?

ኬንያ ከትናንት በስትያ የደረሰው የካፍ ገምጋሚ ኣካል በመዲናዋ ናይሮቢ ለሚገኘው የናያዩ ስቴድየም ግዝያዊ ቅድመማጣርያ እንድያስተናግድ ፍቃድ ሰጥቶታል።እናማ ኬንያ ፖሊስ ቡናን በገለልተኛ ሳይሆን በሜዳው ናይሮቢ ላይ ምያስተናግድ ይሆናል።

በኛም በኩል የፌዴሬሽናችን የክለብ ላይሰንሲንግ ቢሮ ከባንክም ከቡናም ኣመራሮች ጋ ኣበበ ቢቂላን ለማስፈቀድ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ማረጋቸውን መረጃው ደርሶኛል።ስታድየሙ ላይ ምያስፈልጉ ኣንዳንድ ጥቃቅን እድሳቶችን ክለቦቹ ወጪ እንዲሸፍኑ ይፈለጋል።ይህን ሚስማሙ ከሆነ በኣበበ ቢቂላ የመጫወት ሰፊ እድል ኣላቸው።

የክለቦቹን ለወጪ ሸፍኑ ጥያቄ የሰጡትን ምላሽ ለግዜው ማልነግራቹ ይሆናል።

ምስል :-የኬንያው ሲትዝን ቲቪ ናያዮ ስታድየም ፍቃድ ማግኘቱን የሰራውን የትናንት ዜና ማየት ይቻላል።
ermiyas belayneh

#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ
የ2016 የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ሰኔ 30/2016 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲየም በወላይታ ድቻ እና በኢትዮጵያ ቡና ክለቦች መካከል መካሄዱ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ዋንጫ ውድድር እና ሥነ ስርዓት ኮሚቴ በዕለቱ በተካሄደው ጨዋታ ጨዋታውን የመሩት የጨዋታ አመራሮችና የውድድር አመራር ያቀረቡትን ሪፖርት አይቶ በመርመር ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡ ምንጭ :- የኢትዮጵያ…
ኢትዮጵያ ቡና አጥፍቶ ቢሆን ኖሮ ከገንዘብ አልፎ በዝግ ስታዲየም እንዲጮት ለመፍረድ ይሮጡ ነበር ።

- በተላለፈው ቅጣት እንደ እግር ኳስ ወዳድ ቅር ተሰኝተናል ። ቅር የተሰኘነውም ኢትዮጵያ ቡና ላይ በተላለፈው ቅጣት አይደለም እኛ የእጃችንን ነው ያገኘነው ምክንያቱም በአደራ የምንጮትበትን ንብረት ጎድተናል ይሄንንም እኛው ደጋፊዎች እንዳጠፋን እኛው መካስ አለብን እናምናለን ። ነገር ግን በወላይታ ዲቻ ስፖርት ክለብ ላይ የተላለፈው ቅጣት ቅር ያሰኘናል 350 ሺህ ብር ቀርቶ 350 ሚሊዮን ቢሆን እራሱ አያስተምርም ለወደፊቱ ከመሰል ጥፋት አይመልስም ። ይሄ ገንዘብ ከፈረደበት መንግስት በጀት ይከፈላል ይታለፋል ነገር ግን እንደ ስፖርታዊ ጨዋነት ቡድንን የሚያስተምረው ጋጥወጥ የሆኑ ተጫዋቾች , አሰልጣኝ ስታፍ እና ደጋፊውን መቅጣት ሲቻል ነው ። ተጫዋቾች ሜዳ ላይ ካደረጉት አስነዋሪ ድርጊት አልፈው በየ ሶሻል ሚድያዎች ላይ የዘረኝነት በደል አድረገው ለሌላ አለማ መፈጸሚያ ለማድረግ ሲሳተፉ እያየን ነው ። ስለዚህ ስፖርታዊ እርምት እንፈልጋለን ። ደጋፊዎች ከስፖርት ይልቅ ፖለቲካዊ ይዘት ለማድረግ እየተሯሯጡ ይገኛሉ ለዚህም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የማያዳግም እርምት እንዲወስድ እንፈልጋለን ።

ለምሳሌ ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ ቡና ከሀዋሳ ከነማ ጋር ባደረገው ሜዳ ላይ ላደረሰው ስፖርታዊ ጨዋነት ጥሰት በፕርሚየር ሊጉ ላይ የነበሩትን ቀሪ 5 ጨዋታዎች በዝግ ስታዲየም እንዲጮት መወሰኑ አይዘነጋም ።

ማንም ይሁን ማን ለሚያደረስው ስፖርታዊ ጨዋነት ጥሰት የማያዳግም ቅጣት እንዲጣልበት እንፈልጋለን እኛም ኢትዮጵያ ቡናዎች ብንሆንም ሜዳ ላይ ለምናደርሰው ስፖርታዊ ጨዋነት ጥሰት እናወግዛለን ለሚጣልብን ቅጣት በጸጋ እንቀበላለን

ፍትህ ለኢትዮጵያ እግር ኳስ

#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መስከረም 10 2017 እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ለተሳታፊ ክለቦች አሳውቋል !


#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ስም ፦ እስራኤል ሻጎሌ
#ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ
👉 አርባምንጭ ከተማ (2011-2012)
👉 ነገሌ አርሲ (2014-2015)
👉 ባቱ ከነማ (2016)
#የሚጫወትበት_ቦታ፦ አጥቂ
#ቁመት፦ 1.77m
#ኪሎ፦ 63kg
በኢትዮጵያ ቡና የሚቆየው፦ 3 ዓመት
እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ቡና መጣህ


#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#ስም ፦ ኦካይ ጁል
#ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ
👉 ጉለሌ (2013-2014)
👉 ለገጣፎ ለገዳዲ (2015)
👉 አላባ ከነማ (2016)
#የሚጫወትበት_ቦታ፦ የአማካኝ ተከላካይ
#ቁመት፦ 1.79m
#ኪሎ፦ 70kg
በኢትዮጵያ ቡና የሚቆየው፦ 3 ዓመት
እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ቡና መጣህ


#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ስም ፦ ዳዊት ሽፈራው
⚽️ቀድሞ_የተጫወተበት_ክለብ፦
⭐️ወሊሶ ከተማ (2013-2014)
⭐️ጉለሌ ክ/ከተማ (2015)
⭐️ቢሾፍቱ ከተማ (2016)
⚡️የሚጫወትበት_ቦታ፦ የመስመር አጥቂ
👤ቁመት፦ 1.77m
👤ኪሎ፦ 65kg
በኢትዮጵያ ቡና የሚቆየው፦ 3 ዓመት

እንኳን ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ቡና መጣህ

#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ የጋና ብሔራዊ ቡድን እና የአሻንቲ ኮቶኮ ግብ ጠባቂ የሆነውን በቻን የሐገራት የጋና ብሔራዊ ቡድን ቋሚ በረኛ እና ምክትል አንበል Ibrahim Danlad እና ብሩንዲያዊ የፊት አጥቂ Nkurunziza Alfred Umurundi ጋር የውል ስምምነት አድርጓል።
በቀጣይ ሳምንት ሁለቱም ተጫዋቾች ለኢትዮጵያ ቡና ለሁለት ዓመት የሚያቆያቸውን የውል ስምምነት በእግር ኳስ ፌዴሬሽን በመገኘት ውላቸውን ያፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ
Photo
እንደ ደጋፊ ሳይሆን እንደ እግርኳስ ወዳድ ስለ ኢትዮጵያ ቡና ስላለው ሂደት ቻናላችን ይሄን አቅጣጫ አስቀምጧል ።

ጠንካራ ጎን

በኢትዮጵያ ቡና አመራር እና የቦርድ አባላት

- የኢትዮጵያ ቡና አስተዳደራዊ ሁኔታ እና መዋቅሩ የተረጋጋ መንፈስ ያለው እና ከአመት አመት በፋይናንስ ረገድ ቡድኑ ፈርጣማ እንዲሆን የተቻላቸውን እየሰሩ ይገኛሉ ። ለምሳሌ ለአንድ ቡድን የጀርባ አጥንት ናቸው የሚባሉትን ድርጅቶች በስፖንሰር ሺፕ እየተፈራረመ ከአመት አመት የተረጋጋ ፋይናንስ እንዲኖረው አድርጎታል ። ይሄም አቅጣጫ በአንድ ሰው ብቻ የሚመራ አለመሆኑ ይበል የሚያሰኝ ነው ። በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የተጫዋቾች ደሞዝ ጣራ በነካበት እና ትልቅ ቡድን የሚባሉት እራሱ መንገጫገጭ ሲደርስባቸው ኢትዮጵያ ቡና በተረጋጋ መንፈስ እየሄደ ይገኛል ። ሌላው ደግሞ በኳስ ወዳዱ ማህበረሰብ እንዲመረጥ የሚያደረገው ለታዳጊዎች የሚሰጠው ነጻነት እና ተስፋ ነው ። በቅርቡ እንኳን ከታዳጊ በመገኘት በብሄራዊ ቡድን የሚጮቱ ተጫዋቾች አፍርቷል ። ለምሳሌ :- ጋቶች , አማኑኤል ዮሀንስ , አቡበከር ናስር , ቃልኪዳን ዘላለም , ቶካ ጀምስ , አህመድ ረሺድ እና ብዙ ተጫዋቾች ናቸው ። አሁን ካሉ እና የወደፊት ተስፋ ናቸው ከምንላቸው ለምሳሌ :- አማኑኤል አድማሱ , በፍቃዱ አለማየሁ , ይታገሱ , ኤርምያስ የሚገኙ ይሆናሉ ። ነገም እንዚህን የሚመስሉ ታዳጊዎች የሚፈሩ ይሆናል ። ይሄም የኢትዮጵያ ቡና አስተዳደራዊ መዋቅሩ የተለየ እና ምቹ ያደርገዋል ።

በኢትዮጵያ ቡና የተጫዋቾች እና የአሰልጣኞች ቡድን አባላት ላይ

- ግልጽ ነው አንድ እና አንድ የሚታወቀው ነገር ሰራተኞች ብቻ ሳይሆኑ ደጋፊዎች መሆናቸው ግልጽ ነው ። በአንድ መንፈስ ለመለያ መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ሰራዊቶች ናቸው ። ለዚህም ጥሩ ምሳሌ :- በሸገር ደርቢ ምኞት ደበበ አቡበከር ናስር ላይ ላደረሰው ጥፋት የሚክያስ መኮንን አጸፋዊ መልስ ያሳየናል ። ምሳሌ 2:- በኢትዮጵያ ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ላይ የታዘብነው ብሩክ በየነ ተቀይሮ ለመግባት በሚዘጋጅበት ሰአት መሀመድ ኑር መጫወቻ ጫማውን ሰቶት በባዶ እግር አይተነዋል ። ይባስ ብሎ ሁለተኛው ጎል ሲቆጠር በባዶ እግሩ ወደ ተጫዋቾች ሲሮጥ እና ደስታውን ሲገልጽ አይተናል ። ከዚህ በላይ አንድነት , ፍቅር , መሰዋእትነት ከኢትዮጵያ ቡና ውጪ የት ይገኛል ?

ደጋፊዎች ጋር

- ስለ ኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ለማስረዳት ቃላቶች ብቁ አይደሉም ከመጠን በታች ናቸው ።

በክፍል 2 ደካማ ጎኖችን ይዘን እንቀርባለን ። በያንዳንዱ ስራችን አስተያዮታቹን በመወያያ ግሩፕ ላይ ጻፉልን ።

ምንጊዜም ኢትዮጵያ ቡና


#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️ 
@coffeefc  💛🤎
➡️ 
@coffeefc  💛🤎

👉ሮቤል ተክለሚካኤል ከ 3አመት ከግማሽ ቆይታ ቡሀላ ከ ቡና ጋር ተለያይቷል !!

ከክለባችን ጋር በነበረህ ቆይታ እናመሰግናለን በሄድክበት ይቅናህ ሮባ

#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
#የኢትዮጵያ_ቡና_እና_አሰልጣኝ_ነፃነት_ክብሬ_ውላቸውን_አደሱ
በ2014ዓ.ም የውድድር ዘመን የኢትዮጵያ ቡና የተቀላቀሉት አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ ዛሬ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ለአንድ ዓመት የሚያቆያቸውን የውል ስምምነት አድርገዋል። ባለው የውድድር ዘመን ከአሰልጣኝ ኮቫዞቪች ኒኮላ ቡድኑን ተረክበው በፕሪሚየር ሊጉ 3ኛ ሆነው የጨረሱ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ ዋንጫ የኢትዮጵያ ቡናን ሻምፒዮን ማድረግ ችለዋል።
የኢትዮጵያ ቡና አሰልጣኝ ነፃነት ክብሬ በ2017 ዓ.ም ክለባችን ላለበት ኢንተርናሽናል እና የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጠንካራ ቡድን ገንብተው እንደሚመጡ እያመነ ፤ ከወዲሁ ከስራ ባልደረቦቻቸው እና ተጫዋቾቻቸው ጋር የኢትዮጵያ ቡና ወደ ስኬት እንደሚወስዱት በመተማመን ነው።


#Ethiopiabunna #football #Ethiopiancoffeefc #Ethiopia



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሳቻ ጎዝዲ ቀበሌ በተከሰተው ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ ምክንያት በዜጎቻችን ላይ በደረሰው አስከፊ የህይወት አደጋ ገፃችን  አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ የተሰማውን ልባዊ ሐዘን ይገልፃል።



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
እውነት ኢትዮጵያ ቡና ለተጫዋቾች ደሞዝ መክፈል አቃተው ?


የሁላችንም ጥያቄ ይሄ ነገር ግን ከአመት አመት የተጫዋቾች ዝውውር ላይ ዲስኩራቸውን ሲያሰሙ ማዳመጥ የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰብ አመት በዓል ከሆነ ሰነበትበት ብሏል ።

በቅርቡ እንኳን አሰልጣኝ ካሳዬ አራጌን ሲያመጣ ጣልቃ አንገባም የፈለገውን ሁሉ እናደርግለታለን እንደግፈዋለን ከዛን ዋንጫ እንበላለን ተባለ ። እውነት መስሎት ኢንጅነሩ በተደገሰለት ድግስ ተገኝቶ ያማረውን የሚበላ መስሎት በጆሮው የሰማውን ተከትሎ በወርሀ ክረምት ከተፍ አለ ። ለጊዜው ላንተ አጨዋወት የሚስማሙት ተጫዋቾች እነዚህ ናቸው ቀጣይ አመት ሊጉን ስትላመድ ምትፈልገው ይመጣሉ ተባለ አመቱ በጥሩ ሆይሆይታ ተጓዘ እንደለመዱት ክረምት መጣ እኛ ያልሰራነው ወጥ መባል ተጀመረ ቡድኑን ለከፍተኛ ሊግ እንኳን በማይመጥኑ ተጫዋቾች ተሞሉ ቀጥሎ ለደጋፊው ምን ዲስኩር ተነገረ ለካሳዬ አጨዋወት ተጫዋቾች ብቁ አይደሉም ስለዚህ አይፈርሙም ተባለ ተነዛ ተንዛዛ ። በቅርቡ እንኳን የታዘብነው አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተባለ አይ ውበቱ የጠየቀው ደመወዝ አግባብ አይደለም በአቅማችን ብለን አሰልጣኝ እና  አካል ብቃት የሚያሰራ አሰልጣኝ በዶላር ከውጪ አመጣን እውነትም ለውበቱ አቅም የለንም እኛ መግባቢያችን እንግሊዝኛ መቀመጫችን ለንደን ነው ። አይ ቀልድና ፌዝ ። በፈጣሪ እርዳታ በደጋፊው እንባ በተጫዋቾች አንድነት በነጺ እና ታፌ ጉልበት 13 አመት የራቀን የዋንጫ ረሀብ አስታገሱልን እንደነሱማ ስራ ሌላ 13 አመት ምናልባት ዝንተ አለም ስኬት ይናፍቀን ነበር ። በቅርቡ ከአንድ ድንቅ ተጫዋችን ጋር አውርተን ነበር ምንድነው ነገሩ ደጋፊዎች ለምን ዝም ትላላቹ ሙሉ ተጫዋቾች እኮ እንደሚለቁ እየነገሩኝ ነው ቀጣይ ምንድነው ምንሆነው ሊግ ረጅም ውድድር ነው ስኳድ መስፋት አለበት ባለን ተጫዋቾች ላይ ማጠናከር እንጂ አዲስ ቡድን መገንባት እኮ አቅም መጨረስ ነው ። ሁለት የውጭ ዜጋ ስለፈረሙ አትታለሉ አፍ ማዘጊያ ነው የሚል ምክሩን ለገሰን ሚመለከታቸውን ለቡድኑ ቅርብ የሆኑትን ለማናገር ሞከርን እኛ እናቃለን የናተ ስራ መደገፍ ነው ተባልን ። ስለዚህ ለኛ ሚመጥነውን ስለሚያቁ ሌላ 13 ዓመት በንዴት በእንባ በቁጭት በተስፋ በሌላ ቡድን እየቀናን ተጫዋቾች ብቅ እያደረግን ለሌላው የምንለግስ ከራሳችን በላይ ለሌሎች ቡድን የምንጨነቅ የዋህ ቢባል ኢትዮጵያ ቡና ብንል ምን ያንሰናል ።

ይባስ ብሎ እንኳን ለሊግ ለሰፈር ቡድን ማይመጥን አለ ይሉናል ያማል ቅኔው

ይሁን እስኪ አንድ ቀን አለ



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🙌ለኛ ለኢትዮጵያ ቡና ክለብ ደጋፊዎች ውዱ አማካዩን አማኑኤል ዮሀንስን ከክለባችን መሰናበቱን መስማት በከባድ ህመም ነው።

👉አማኑ ገና ከታዳጊነቱ ጀምሮ  የኢትዮጵያ ቡና ክለብ ማሊያን ብቻ በመልበስ የቡድናችን ወሳኝ አካል ሆኖ በሁሉም ቦታ የደጋፊዎችን ልብ አሸንፏል። ወደ ሌላ ክለብ መሄዱ በስፖርቱ አለም ለውጥ የማይቀር መሆኑን የሚያሳዝን ነው።

...ሆኖም በአማኑኤል ክለቡን መልቀቅ ስናዝን፣ ለኢትዮጵያ ቡና ክለብ ላደረገው ነገር ሁሉ ያለንን አድናቆትና ፍቅር ልንገልጽ ይገባል።

...አማኑኤል የኢትዮጵያ ቡናን 8 ቁጥር ማሊያ ለበሰም  አለበሰም በቡድናችን እና በደጋፊዎቻችን ላይ የማይጠፋ አሻራ ጥሏል። የእሱ ተሰጥኦ፣ ትጋት እና ለጨዋታው ያለው ፍቅር ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ደጋፊዎች አነሳስቷል፣ እና የእሱ ከቡና መውጣት  በጣም ልብ የሚሰብር ነገር ነው።

...አማኑኤል በዚህ የስራ ዘመኑ አዲስ ምዕራፍ ሲጀምር መልካም ምኞታችንን እናቀርባለን። በአዲሱ ክለቡ ጥሩ ብቃቱን እያሳየ እና ትልቅ ስኬትን እንደሚያስመዘግብ ተስፋ እናደርጋለን። እናም እሱ ሲሄድ በሌላ ማልያ ስናየው ቢያሳዝነንም የኢትዮጵያ ቡና ክለብ አባል ሆኖ የሰጠንን ትዝታዎችን እና ጊዜያትንም ማስታወስ አለብን።

....አማኑኤል እንወድሃለን እና ከእኛ ጋር ያሳለፍከውን ጊዜ ሁሌም እናከብራለን።

😢በማጠቃለያው የአማኑኤል ዮሃንስ መሰናበት ለኢትዮጵያ ቡና ክለብ አሳዛኝ ቀን ነው!



አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና- አደገኞቹ
➡️  @coffeefc  💛🤎
➡️  @coffeefc  💛🤎

Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Forwarded from Botton Creater ✅
🔞🔞🔞🔞ከ 18 አመት በታች ለሆናችሁ የተከለከለ ነው!🔞🔞🔞🔞