TIKVAH-ETHIOPIA
1.38M subscribers
54.6K photos
1.35K videos
197 files
3.61K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

የህዝቡን #ደህንነት እና #ሰላም ለመጠበቅ ሲል መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው ላይ የመንግስት ትእግስት #ገደብ እንዳለው በመግለፅ #ጉልበተኞችን እንደማይታገስ አስታውቀዋል።

አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉት #ሁከቶች #በሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ስም የተቀነባበሩ መሆናቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ጠቁመዋል።

ባለፉት ሦስት ቀናት በቡራዩና አካባቢው ብዛት ያላቸው ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመጠቆም፥ በተለያዩ ቦታዎች ተዘርፈው የነበሩ ንብረቶችን የማሰባሰብ ስራ መሰራቱንም ነው ያስታወቁት።

በአጠቃላይም በቡራዩ ከ300 አስከ 400 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ300 በላይ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡

በአዲስ አበባ #ገንዘብ ተከፍሏቸው ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት እንዲሁም ብሄርን መሰረት ያደረጉ ስድቦችንም ጭምር በማሰራጨት #የተጠረጠሩ ግለሰቦች መያዛቸውንም አንስተዋል።

ይህ ድርጊት #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባና በአርባ ምንጭ መታየቱን ጠቅሰዋል።

ኮሚሽነሩ በቡራዩና አካባቢው የተፈፀመውን ግድያ ለማውገዝ በርካታ ሰላማዊ ሰው መውጣቱን ጠቅሰው #የተወሰኑ ቡድኖች ግን አዝሚሚያቸው ሌላ ነበር ብለዋል።

ከእነዚህ የተወሰኑ ግለሰቦች መካከልም #ቦምብ ይዘው የነበሩ በህብረተሰቡ ትብብር መያዛቸውን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በፒያሳና በመርካቶ #ለዝርፊያ የሚቃጡ ግለሰቦች እንደነበሩ ነው የጠቀሱት።

የተወሰኑት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ ጠብመንጃ ለመንጠቅ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር #ግብግብ ገጥመው ነበር ብለዋል።

ይህንንም ተከትሎ የአምስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ይህ ግርግር ሆን ተብሎ የተጀመረውን ለውጥ #እንዳይሳካ #ታስቦበት የተከናወነ መሆኑን ነው ያነሱት።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቡራዩ⬇️

በቡራዩ ከተማና አካባቢዋ በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት የአካል ጉዳት፣ #ዘረፋና ንብረት እንዲወድም ከመስከረም 1 ቀን 2011 ጀምሮ በመቀስቀስ እና #ገንዘብ በማከፋፈል ግጭቱ እንዲነሳ በማድረግ የተጠረጠሩ ስድስት ግለሰቦችን የፌደራል ፖሊስ ፍረድ ቤት አቀረበ።

በፌደራልና በኦሮሚያ ፖሊስ ለሁለት ተከፋፍሎ የሚከናወነው ምርመራ የቀጠለ ሲሆን፥ ትናንት ከሰዓት በኋላ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምደብ ችሎት 1ኛ ተረኛ ወንጀል ችሎት ስድስቱ ተጠርጣሪዎች ቀርበዋል።

መርማሪ ፖሊስ ለተጨማሪ ምርመራ የ14 ቀን ጊዜ ጠይቆባቸዋል።

#ተጠርጣሪዎቹ ሳምሶን ጥላሁን፣ ዓለሙ ዋቅቶላ፣ ቡልቻ ታደሰ፣ ሀሺም አህሚድ፣ ሽፈራው ኢራና እና ኢሉ ዳንኤል ሲሆኑ፥ ነዋሪነታቸው በቡራዩ፣ ገፈርሳና ከታ አካባቢ ነው።

መርማሪ ፖሊስ ግለሰቦቹ #የተጠረጠሩበት በቡራዩና አካባቢዋ በደረሰው የሰው ህይወት መጥፋት፣ ንብረት መውደም እና ዘረፋ የተጠረጠሩ ናቸው በማለት መነሻ መረጃ እንዳገኘባቸው አስረድቷል።

ተጠርጣሪዎቹ በበኩላቸው ድርጊቱን አልፈፀምንም ሲሉ አስረድተዋል።

ክርክራቸውን ያዳመጠው ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራውን በ14 ቀናት ውስጥ አጠናቆ እንዲቀረብ በማዘዝ ለመስከረም 24 ቀን 2011 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በተመሳሳይ በኦሮሚያ ፖሊስ ምርመራ እየተደረገባቸው ካሉ ግለሰቦች መካከል 45 ተጠርጣሪዎቹ ትናንት ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፥ ቀሪዎቹ ዛሬ ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

©FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጋምቤላ⬆️

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የተለያዩ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ከአንድ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ቾል ኩን ለኢዜአ እንደገለጹት ህገ ወጥ መሳሪያዎችን ከትናንት በስቲያ በጋምቤላ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለው #ከላሬ ወረዳ ወደ #ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክር ነው።

በፖሊስ ከተያዙት የጦር መሳሪያዎች መካከል አራት ሽጉጦች፣ አንድ ታጣፊ ክላሽ፣ አንድ ሺህ 133 የተለያዩ ዓይነት ጥይቶች ይገኙበታል።

ከህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች ጋር ከ20 ሺህ 600 ብር በላይ #ገንዘብ ፖሊስ አብሮ በቁጥጥር ሥር መዋሉንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

በተጠርጣሪው ላይ በተደረገው ማጣራትም የጦር መሳሪያዎቹን ወደ #መሀል ሀገር የማስገባት እቅድ እንደነበረውም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በተጠርጣሪ ግለሰቡ ላይ ማስረጃ የማሰባሰብና የማጠራት ሥራ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ “የምርመራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ይላካል” ብለዋል።

ክልሉ በተለይም ከደቡብ ሱዳን ጋር በስፋት በድንበር የሚዋሰን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርካታ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህዝቡ #ተሳተፎውን እንዲያጠናክር
ጠይቀዋል።

ህግ ወጥ የጦር መሳሪዎች በሀገሪቱ ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ችግሮች በመገንዘብ ኮሚሽነሩ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር በጋራ #ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

©ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH🔝

በጌዳኦ ዞን ለሚገኙ #ተፈናቃዮች በእናተ በTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት በኩል በተሰበሰበው #ገንዘብ_ድጋፍ ለማድረግ በዛሬው ዕለት ወጣቶች ወደስፍራው አቅንተዋል።
.
.
.
አጠቃላይ የተሰበሰብው ገንዘብ ምን ያህል እንደሆነ እንዲሁም የተፈፀሙ ግዢዎችን በደረሰኝ ለእናተ የማሳያችሁ ይሆናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#YouTube ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዩትዩብ ቻናል የለውም! ከሰሞኑን በTIKVAH-ETH (Tikvah-Ethiopia) ስም ዩትዩብ ላይ እውቅና የሌላቸው፣ ሰዎችን የሚያሸብሩና የሚያስደነግጡ የተለያዩ መረጃዎች እየተሰራጩ እንደሆኑ እየተመለከትን ነው። እነዚህ የሚሰራጩት መረጃዎች በቀን ውስጥ ከ50,000 በላይ ሰዎች አንዳንዴም በመቶ ሺ የሚጠጉ ሰዎች ጋር እየደረሱ በርካቶችን እያሳሳቱ ነው። የቲክቫህ ባለቤቶች…
#YouTube

ዩትዩብ ላይ በTIKVAH-ETH ስም ሀሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ የነበሩ አካላት አጠቃላይ መረጃዎችን ከገፁ ላይ አጥፍተውታል ፤ በተጨማሪ ስሙን ከTIKVAH-ETH ወደ "Hagere Ethiopia ሀገሬ ኢትዮጵያ" ቀይረውታል።

በTIKVAH-ETH የቤተሰብ አባላት ስም የዩትዩብ ገፅ ከፍተው ሀሰተኛ መረጃዎችን ሲያሰራጩ የነበሩት አካላት ላይ አስፈላጊው የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።

ምንም እንኳን ከዚህ ቀደም ያሰራጯቸውን ሀሰተስኛና ሰዎችን ሚያሸበሩ መረጃዎች ከገፃቸው ቢያጠፉም በአንድ እና በሁለት ቀን በመቶ ሺ ለሚቆጠር የዩትዩት ተጠቃሚ ደርሰዋል ፤ እኛም እኚህ አካላት ማንነታቸውን እንደደረስንበት #በህግ የምናስጠይቃቸው ይሆናል።

በድጋሚ #ለማስታወስ TIKVAH-ETHIOPIA ዩትዩብ ላይ ምንም አይነት ቻናል #የለውም። አሁንም በቲክቫህ ስም ዩትዩብ ቻናል ከፍተው #ገንዘብ ለመሰብሰብ ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ ወገኖች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እናሳስባለን።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
" 3 የኤጀንሲው ሰራተኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል "

የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ 3 የኤጀንሲው ሰራተኞች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉን አስታወቀ።

ኤጀንሲው ፤ የህትመት ስርጭት እና አጠቃቀም ላይ መደበኛ የኦዲት ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጾ በዚህም በተገኘው ግኝት የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ  ጽ/ቤት የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና ማስረጃ ቡድን #መሪ እና 2 ባለሙያዎች በሰሩት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ሲል ገልጿል።

ኤጀንሲው የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት በደረሰው ጥቆማ ላይ ተመስርቶ ባሰባሰበው ማስረጃ ፦

- ለወረዳው ፈቃድ ሳይሰጥ የውጭ ዜጎችን #ገንዘብ_በመቀበል ጋብቻ በመፈፀም፣

- ባልተሟላ ማስረጃ የልደት ምዝገባ በማከናወን እንዲሁም በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ባለሙያዎችዎቹ ተጠርጥረው ከስራ እንዲታገዱ በማድረግ የወንጀል ምርመራ እንዲካሄድ አድርጓል ብሏል።

በተመሳሳይ ሁኔታ ኤጀንሲው ፤ #በለሚ_ኩራ ክ/ከተማ  ወረዳ 13 ጽህፈት ቤት 1 ቡድን መሪ እና ባለሙያዎች በወንጀል ጉዳዮቸው እየታየ መሆኑ አስታውሷል።

ነዋሪዎች የትኛውንም ዓይነት ቅሬታ ፣ ጥቆማ ወይም መረጃ ለመስጠት የኤጀንሲውን ነፃ የስልክ መስመር 7533 መጠቀም ይችላሉ ተብሏል።

@tikvahethiopia
#ቫት

መንግስት በመሰረታዊ ፍጆታ በሆኑ #ምግቦች ላይ #ቫት እንዲያስቀር ተጠየቀ።

መንግሥት ከድጎማ ይልቅ መሠረታዊ የዜጎች ፍጆታ በሆኑ ምግቦች ላይ የሚጣለውን የተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲያስቀር ፐርፐዝ ብላክን ጨምሮ ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት መንግሥትን ስለመጠየቃቸው ሪፖርተር አስነብቧል።

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ፍስኃ እሸቱ በሰጡት ቃል ፤ ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴና ለአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ጥያቄው በአካል መቅረቡን የገለፁ ሲሆን የጉዳዩ ዋነኛ ባለቤት የሆነው የገንዘብ ሚኒስቴር በጉዳዩ ላይ ተገቢውን ምልክታ እንዲያደርግ ጥያቄ ለማቅረብ በሚቀጥለው ሳምንት ቀጠሮ መያዙን ገልፀዋል።

ዶ/ር ፍስኃ እሸቱ ለሪፖርተር የሰጡት ቃል ፦

" ለዋጋ ግሽበት አንዱና ጉልህ አስተዋጽኦ እያደረገ ያለው ጉዳይ በተለይ በምግብ ውጤቶች ላይ የሚጣለው የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ጉዳይ ነው።

ዝቅተኛ ገቢ ያለው ኅብረተሰብ ክፍል በሚመገበው ምግብ ላይ 15 በመቶ ታክስ መጨመር ትልቅ ተፅዕኖ አሳድሯል።

ከወር በፊት ይኸው ጥያቄ ለሚመለከታቸው አካላት ቀርቧል። የገንዘብ ሚኒስትሩን ለማግኘት ጥረቶች እንደተደረጉ ነው፤ ምናልባት በሚቀጥለው ሳምንት ዕድሉ የሚሳካ ከሆነ ጥያቄውን በግምባር ለማቅረብ እየተሰራ ነው።

ጥያቄውን በአዋጅ ሳይሆን በመመርያ ደረጃ መመለስ የሚቻል ነው። የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ይሁንታ ካገኘ መስተካከል የሚችል ነው።

አነስተኛ የሆነ ገቢ ያላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚጠቀሟቸው በተለይም የአትክልት እና የፍራፍሬ ውጤቶች (ሽንኩርት ፣ ቲማቲም እና ሌሎችም) ከታክስ ነፃ ናቸው ከሚባሉት እንቁላልና ሥጋ በበለጠ ተዘውታሪ በመሆናቸው፣ መንግሥት ከእነዚህ ምርቶች የሚሰበሰበው ቫት እንዲቀር ተጠይቋል።

ፐርፐዝ ብላክ የምርት ውጤቶቹን ቫት በማከል ነው ለሸማች የሚያቀርበድ ይህም ምርቶችን በጣም በረከሰ ዋጋ እንዳያቀርቡ አንዱ እንቅፋት ሆኗል።

ኢትዮጵያ ውስጥ #የዋጋ_ንረት_መባባስ የጀመረው #የተጨማሪ_እሴት_ታክስ አሠራር ከመጣ ወዲህ መሆኑን ጥናት ያስረዳል።

መንግሥት ለሚያከናውናቸው ሥራዎች #ገንዘብ እንደሚያስፈልገው ሳይረሳ ነገር ግን በሁሉም ምግብ ፍጆታዎች ላይ ሳይሆን ኅብረተሰቡ በመሠረታዊነት የሚጠቀምባቸውን ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ማድረግ ይገባዋል። "

🍏🥬🫑🥕🍋🍌🍇🍎🍓🍍🧄🥔🍅🌶

#ቫት ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ (20) ዓመታት በፊት ያወጣውን የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ማዘጋጀቱ ይታወሳል።

ረቂቅ አዋጁ መንግሥት ከቫት ታክስ የሚሰበስብበትን መሠረት የሚያሰፋ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በሥራ ላይ ያለው አዋጅ በ1994 ዓ.ም. ከወጣ በኋላ በ2001 ዓ.ም. እና በ2011 ዓ.ም. ለሁለት ጊዜያት መጠነኛ ማሻሻያዎች ተደርጎበት የቀጠለ ሲሆን ፣ አዲስ እየወጣ ያለው የተጨማሪ እሴት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ሲፀድቅ የበፊቱን ይሽራል ተብሏል፡፡

በረቂቅ አዋጁ በሰንጠረዥ ሁለት አንቀጽ ስምንት ከታክስ ነፃ የሆኑ አቅርቦቶች መዘርዝር ሥር የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመርያ ላይ ዝርዝራቸው የሚወሰን የምግብ አቅርቦቶች እንደሚኖሩ የተደነገገ ሲሆን የትኞቹ ናቸው በሚለው ላይ ምንም ተጨማሪ ማብራሪያ አለመስፈሩ ታውቋል፡፡

Credit : ሪፖርተር ጋዜጣ (www.Ethiopianrepoter.com)

@tikvahethiopia
#የፖሊስ_ማሳሰቢያ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፤ በትራፊክ መብራቶች  እና በመስቀለኛ መንገዶች ላይ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ንግድ እና የልመና ተግባራት ላይ በተሰማሩ ግለሰቦችና #ገንዘብ_በሚሰጡና በሚገበያዩ አሽከርካሪዎች ላይ በህጉ መሰረት ጠንካራ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል አስጠነቀቀ።

በልመና ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ የሚሰጡ እና ግብይት የሚፈፅሙ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

በሚኒስትሮች ም/ቤት የወጣው የትራንስፖርት መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 #በትራፊክ_መብራት ላይ ወይም #በመስቀለኛ_መንገድ ላይ በልመና ተግባር ለተሰማሩ ሰዎች ገንዘብ የሰጠ ወይም ግብይት የፈፀመ አሽከርካሪ ቅጣት እንደሚጣልበት ይደነግጋል፡፡

" ይሁን እንጂ #የአሽከርካሪዎች ደንብ አክባሪ አለመሆን በእነዚህ መንገዶች ላይ የሚከናወኑ ህገ-ወጥ ንግድና የልመና ተግባራት እንዲስፋፉ ምክንያት ሆኗል " ሲል ፖሊስ ገልጿል።

የትራፊክ ደንቡ አለመከበር #ለትራፊክ_አደጋ መጨመር እና ጤናማ የትራፊክ ፍሰት እንዳይኖር እንቅፋት ከመፍጠሩ ባሻገር በተለይ የትራፊክ መብራቶች ባሉባቸው ጎዳናዎች የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች የሚፈፀምባቸው ቦታዎች እየሆኑ መምጣታቸውን ፖሊስ አስረድቷል።

ያንብቡ : https://telegra.ph/Addis-Ababa-Police-01-04

@tikvahethiopia
#AmharaRegion #Gojjam

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋርዱላና ኧሌ ዞኖች ተነስተው ለደን ምንጣሮ ስራ ወደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እያመሩ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ጎዛምን አካባቢ በ " ፋኖ ታጣቂዎች " የተያዙ የቀን ሰራተኞችን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረገ መሆኑን የምልመላና የቅጥር ሂደቱን የፈፀመው " ኒኮቲካ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር አሳውቋል።

የታገቱት ሰራተኞች ብዛታ 272 እንደሆነ ተነግሯል።

የድርጅቱ የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሙልጌታ አለነ ምን አሉ ?

" በአጠቃላይ 4 ሺህ ሰራተኛ ነው ያስፈቀድነው። 272 ሰራተኛ ከጋርዱላና አሌ ዞን ወስደን መንገድ ላይ ችግር ገጥሞናል። ችግሩን በአካል እኔው እራሴ ሄጄ በሽማግሌም፣ በምንም እንዲፈታ እየሞከርን ነው " ብለዋል።

ቁጥርን በተመለከተ ፤ " ከጋርዱላ 246 እና ከአሌ 38 በድምሩ 282 ሰራተኞች ነው የሄዱት " የሚባለው እጅግ በጣም ስህተት ነው ብለዋል። " ዶክመንት አለን እያንዳንዱ ዶክመንት ስላለን በዛ ነው የምናወራው ፤ የሰው ልጅ ነው የወስድነው ማንም እየተነሳ ይሄ ነው ማለት አይችልም። ስንወስዳቸውም በህጋዊ መንገድ ተፈራርመን ነው። ቁጥራቸው 272 ነው " ብለዋል።

ይሄን ያህል ብዙ ኪ/ሜ ርቀት ሄዶ ለህዳሴ ግድብ ሰራተኛ መመልመሉን ምን አመጣው ? ለሚለው ጥያቄ ፤ " ጠንካራ ሰራተኞች ስለሆኑን ነው " ሲሉ መልሰዋል። ባለፈው ዓመት ድርጅቱ በተመሳሳይ ከየክልሉ ከአማራ፣ ከቤኒሻንጉል፣ ከደቡብ፣ ከሁሉም ሰራተኛ ወስዶ እንደነበር አስታውሰው በተደረገው ግምገማ በስራቸው ውጤታማ ስለሆኑ ነው ደብዳቤ ተፅፎ ሰራተኞቹ የተወሰዱት የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

በአማራ ክልል ውስጥ ጦርነት እንዳለና መረጋጋት እንደሌለ እየታወቀ ለምን በዚህ መንገድ እንዲሄዱ ተደረገ ? በሚል ለቀረበው ጥያቄ ፤ " እኛ የያዝነው የሀገር ፕሮጀክት ነው። ውል ገብተናል በውሉ መሰረት መስራት አለብን። መንገዱም ሌላ መንገድ የለውም አምናም (በ2015 ዓ/ም) ከ2 ሺህ በላይ ሰራተኞችን ከኮንሶ ስንወስድ በዚሁ በራሱ መንገድ ነው። አሁንም ህዳር ላይ ነበር የምንገባው ባለው ሁኔታ ሳንገባ ቀረን ሲረጋጋ ተረጋግቷል ግቡ ተባልን ገባን " ሲሉ መልሰዋል።

' ከፋኖ ታጣቂዎች ለታጋቾች #ገንዘብ ተጠይቋል ፣ ድርጅቱ ገንዘብም ሰጥቷል '' እየተባለ ስለሚነገረው ጉዳይ በተመለከተ ፤ " እኛ ሙሉ መረጃ በሁለት ቀን እንሰጣለን ከዚህ በላይ ማለት ያለብኝ የለም " ብለዋል።

የሰራተኞቹ ደህንነትን በተመለከተ " ደህንነታቸው በጣም ሰላም ነው " ብለዋል። ይህን ያረጋገጡት እዛው ቅርብ ስለሆነ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን በአካል እዛው አካባቢ በቅርብ ሆነው እየተከታተሉ እና #በሽምግልና ልጆችን ከእገታ ለማስወጣት ጥረት እያደረጉ እንደሆነ አስረድተዋል።

ድርጅቱ በኢትዮጵያ የንግድ ህግ የተመዘገበ ከመላው ሀገሪቱ ሰራተኞችን ለስራ እየመለመለ የሚቀጥር እንደሆነ አሳውቀዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በ 'ፋኖ ታጣቂ ኃይሎች' የተያዙ ሰራተኞች ቤተሰቦች ሰራተኞቹ ፦
* አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ እንዳሉ፣
* ጫካ ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ፣
* ምግብም እያገኙ እንዳለሆነ፣
* ወታደራዊ ስልጠና እንዲወስዱና ወደ ውጊያ ውስጥ እንዲገቡ የማስገደድ ሁኔታ እንዳለ፣
* የግድያ / ርሸና ዛቻም እንደሚደርስባቸው ተናግረዋል።

ወጣቶቹ ታግተው ከተወሰዱ 4ኛው ሳምንት እየጀመረ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ይህ ነው የሚባል መፍትሄ የሰጣቸው አካል እንደሌለ ቤተሰቦች ገልጸዋል። የፌዴራልም የክልል መንግሥትም ዝም ማለታቸው እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት ' የአማራ ፋኖ የጎጃም ቃል አቀባይ ነኝ ' ያሉት ፋኖ ማርሸት ፀሀዩ ፤ " ... ከተቻለ በ72 ሰዓታት ውስጥ ወጣቶቹን ለቀይ መስቀል እናስረክባቸዋልን " ብለዋል።

ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ምን አሉ ?

➢ " እኛ ያረጋገጥነው እነዚህ ልጆች አውቀውም ይሁን ተጭበርብረው ጎጃም ውስጥ ወደሚገኘው የብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ሲወሰዱ ነው ያገኘናቸው " ብለዋል።

➢ የታገቱ ወጣቶች ብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እየተወሰዱ ስለመሆኑን ምን ማስረጃ አላችሁ ? ለሚለው ጥያቄ ፤ " ተጨባጭ የሆነ ማስረጃ አለን። በወታደራዊ ቋንቋ ጠርናፊ የሚባል ቃል አለ ይህ ማለት አንድን የሚንቀሳቀስ ወታደራዊ ኃይል፣ ምልምል / የታጠቀ ኃይል የሚመራ ማለት ነው። የነዚያ ተጓዦች ተርናፊዎች የአስር አለቃ ማዕረግ ሳይቀርብያላቸው አክቲቭ ወታደሮች መሆናቸውን ከራሰቸው መታወቂያ ዕዛቸውን፣ ኮራቸው፣ ክ/ጦራቸውም ፣ ሻለቃቸውን የሚጠቅስ መታወቂያ ይዘዋል። የመከላከያ አርማ ያለው መታወቂያና አክቲቭ መሆናቸውን አረጋግጠናል " ብለዋል።

➢ "ከያዝናቸው ውስጥ ያነጋገርናቸው ወደ መሰረታዊ ውትድርና እንደሚገቡ እንደሚያውቁ ፣ በዛ ያሉት ግን ግንዛቤው እንደሌላቸው ግን ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚከፈላቸው ነው ያረጋገጥነው" ሲሉ አክለዋል።

➢ ሌላው ከተለያየ ኢትዮጵያ ክፍል ወደህዳሴ ግድብ የሚሄዱ ሰራተኞችም ሆነ ጎብኝዎች አዲስ አበባን ረግጠው ፣ በአምቦ አድርገው በነቀምት ፣ አሶሳ ነው ወደ ጉባ የሚገቡት በአማራ ክልል አቋርጠው የሚሄዱበት ታሪክ አልነበረም ሲሉ ተደምጠዋል። " አሁን ላይ በአማራ ክልል ውጊያ እንዳለ እየታወቀ በአ/አ አማራ ክልል አድርገው ወደ ጉባ የሚሄዱበት ምክንያት የለም " ሲሉ አክለዋል።

➢ የወጣቶቹን ቀጣይ ዕጣ ፋንታ በተመለከተ እኚሁ ቃል አቀባይ ፤ " ስለ ፋኖ ዓላማ ፣ ስለ አማራ ትግል አስፈላጊውን ትምህርት ሰጥተናቸው ለቀይ መስቀል ልናስረክባቸው በዝግጅት ላይ ነን " ብለዋል። " ቀይ መስቀል ወደኛ እየመጣ ስለሆነ ከተቻለ በ72 ሰዓት ካልሆነም በ100 ሰዓት ውስጥ ለማስረከብ ዝግጁ ነን። ሁኔታውን አጥንተው ስለሚገቡ በደረሱበት ሰዓት እናስረክባለን። " ብለዋል።

➢ በታጋቾች ላይ እየተፈፀመነው ስለሚባለው የግድያ ዛቻ፣ በግዳጅ ወደ ውጊያ እንዲገቡ የማድረግ ጉዳይ ተጠይቀው ፤ " ከያዝናቸው 240 ሰዎች ፦
• አንድም ሰው የአካል ድብደባ ደርሶበት ከሆነ፣
• በግድ ፋኖ እንዲሆን ጠብመንጃ እንዲሸከም ተገዶ ከሆነ ፣
• አንድም ሰው ያለ ፍላጎቱ እኛ የፈለግነውን ፕሮፖጋንዳ እንዲናገር ተገዶ ከሆነ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፣ ሂውማን ራይትስዎች አስፈላጊው አጣሪ ኮሚቴ ልከው ማጣራት ይችላሉ " ብለዋል።

የጋርዱላ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ኩናሎ ምን አሉ ?

° የፌዴራል መንግሥት ፤ የአማራ ክልልም መንግሥት ከዞኑ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን ነገር ግን እስካሁን ውጤት እንዳልመጣ ተናግረዋል።

° ታጋቾች #በነፍስ_ወከፍ_300_ሺ_ብር እንዲከፍሉ መጠየቁን ነገር ግን ለማስቀለቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን መረጃ ያገኘው ከቪኦኤ ሬድዮ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AmharaRegion #Gojjam ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋርዱላና ኧሌ ዞኖች ተነስተው ለደን ምንጣሮ ስራ ወደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እያመሩ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ጎዛምን አካባቢ በ " ፋኖ ታጣቂዎች " የተያዙ የቀን ሰራተኞችን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረገ መሆኑን የምልመላና የቅጥር ሂደቱን የፈፀመው " ኒኮቲካ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር አሳውቋል። የታገቱት ሰራተኞች ብዛታ 272…
#Update

" 4 ሚሊዮን ብር ለማስለቀቂያ ከፍለናል ሰነዱ በእጄ አለ፤ ከለቀቋቸው በኃላ ድጋሜ በመያዝ 6 ሚሊዮን ብር ጠይቀዋል " - ቀጣሪ ድርጅቱ

ወደ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለደን ምንጣሮ ስራ በግል ድርጅት ተመልምለው ወደ ስፍራው በአማራ ክልል፣ በምስቅው ጎጃም ፣ ጎዛመን በኩል አቋርጠው ሲጓዙ የካቲት 18/2016 ዓ/ም " በፋኖ ታጣቂዎች " ታገቱ የተባሉ ሠራተኞች እስካሁን ከእገታ አልተለቀቁም ሲል ቀጣሪው ድርጅት ገለጸ።

የቀጣሪው ድርጅት ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሙልጌታ አለነ ፤ ላለፉት 24 ቀናት ታግተው የሚገኙትን 272 #የቀን_ሰራተኞች ጉዳት ሳያገኛቸው ለማስለቀቅ መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ/ም 4 ሚሊዮን ብር በተለያዩ 3 ሰዎች አማካኝነት ክፍያ ፈፅመናል ብለዋል።

አቶ ሙልጌታ ፤ " ገንዘቡን #ተቀበሉን ከዛም ለቀቋቸው ከለቀቋቸው በኃላ እንደገና ጎዛመን የሚባል ቦታ ላይ ለዋናው አስፓልት 5 ኪ/ሜ ሲቀር እንደገና ሌላ ኃይል መልሶ ያዛቸው። ... የውሸት የውሸት ፖለቲካ የእውነት አምላክ ይፍረድልን ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረድልን " ሲሉ ተናግረዋል።

" 4,000,000 ብር (4 ሚሊዮን) ነው #የከፈልናቸው " ያሉት አቶ ሙልጌታ ፤ " የከፈልኩበት ሰነድ በእጄ አለ ፤ በ3 ሰው ስም ነው የገባው። ' አስገባ ' ተባልኩኝ አስገባሁ ተለቀቁ እንደገና ከተለቀቁ በኃላ ሌላ ቡድን ያዛቸውና ለእያንዳንዱ መኪና አሁን 1,500,000 ብር ተጠይቋል ፤ ልጆቹን ለቀይ መስቀል ነው አሳልፈን የምንሰጠው ብለውን እየጠበቅን ነው " ብለዋል።

መጋቢት 1 ተለቀው እና ድጋሚ ተይዘው ከሆነ ከቀናት በፊት ቃለ ምልልስ በሰጡበት ወቅት ይህን ገንዘብ ለአጋቾቹ #መክፈላቸውንና ተለቀው መያዛቸውን ለምን እንዳልተናገሩ ተጠየቀው ፤ " አንደኛ የነበርኩት እዛው አካባቢ ነው ለደህንነቴ አስቸጋሪ ነበር። ሁለተኛ ደግሞ ልጆቹን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረኩ ነበር በዛ የተነሳ ነው " ሲሉ መልሰዋል።

ስራ አስኪያጁ ፤ ሰራተኞቹ #ከእገታው_ተለቀው መሄድ ከጀመሩ በኃላ በድጋሚ በቡድኑ ሌላ ክንፍ የተያዙት እዛው በምስራቅ ጎጃም ፣ ማቻከል ወረዳ አማኑኤል አካባቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ሲጓዙበት የነበረ 4 ተሽከርካሪ ቁልፍም በታጣቂዎች መወሰዱን ገልጸዋል።

6 ሚሊዮን ብር ማስለቀቂያ መጠየቁን አመልክተዋል።

' የአማራ ፋኖ የጎጃም ቃል አቀባይ ' እንደሆኑ የገለጹት ፋኖ ማርሸት ፀሀይ ግን ምንም አይነት የገንዘብ ጥያቄ አላቀረብንም ፤ ገንዘብም አልተቀበልንም ፣ ድርጅቱ ስም ማጥፋት ነው የያዘው ብለዋል።

ፋኖ ማርሸት " ይሄ ኒኮቲካ የሚባለው የኮንስትራክሽን ድርጅት የፋኖን ስም በዓላማ እያጠፋ ያለ ተቋም ነው። ምርኮኞች የተያዙት በ4ኛው ክ/ጦር በሚያስተዳድረው ቀጠና ነው። ክፍለ ጦራችን #አማኑኤል / ማቸከል፣ ጎዛመን እስከ ደ/ማርቆስ እና ልጆቹ አሁን ያሉበትን በረሃ ያጠቃልላል። ስለዚህ በዚህ ቀጠና እስካሉ የኛ ሙርከኞች ናቸው " ብለዋል።

" #ገንዘብ_የጠየቀ_አካል_የለም። ተጭነውባቸው ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም የመጡባቸው የአውቶብሶቹ ባለቤቶች (4 አውቶብሶች) ' አውቶብሶቻችን ስጡን ' ሲሉ  አንሰጥም የሚል መልስ ሲሰጣቸው ' ለፋኖ ገንዘብ እንስጥና ድጋፍ አድርገን አውቶብሶቻችን ይመለሱ ' አሉ እኛ የገንዘብ ችግር የለብንም ፤ ገንዘብ አንጠይቅም አውቶብሶቹ ግን ቀይ መስቀል መጥቶ ልጆቹን ሲረከብ ተጭነው የሚሄዱባቸው ናቸው ብለን አቆይተናል " ብለዋል።

ልጆቹ ከነበሩበትም #እንዳልተንቀሳቀሱ ፣ ኒኮቲካም ሊቀበል እንዳልመጣ ገልጸው ድርጅቱ " የፋኖን ስም እያጠፋነው " ሲሉ ከሰዋል።

" እነዚህ ልጆች ታጋቾች ሳይሆኑ #ምርኮኞች ናቸው። ምርኮኞቹን ደግሞ ለቀይ መስቀል የምናስተላልፍበት ምክንያት ፦
1. እኛ ተንቀሳቃሽ ኃይል ስለሆንን፣
2. ለነሱ የምንመግበውን ምግብ ለወታደራችን ማዋል ስላለብን ፣
3. ዓለም አቀፍ የጦርነት ህግን አክብረን የምንዋጋ የነፃነት ታዋጊዎች / ኃይሎች መሆናቸውን ለማረጋገጥ ነው " ብለዋል።

እስካሁን ቀይ መስቀል እንዳልመጣ በአካል ከመጡ እናስረክባለን ሲሉ ተናግረዋል።

የተያዙት ደግሞ ድርጅቱ እንዳለው " 272 " ሳይሆኑን 246 ብቻ ናቸው ብለዋል።

ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን አሁን ጉዳዩ ከእኛ ከአቅማችን በላይ ነው ሲል አሳውቋል።

አቶ ሙልጌታ አለነ ፤ " ለሚመለከተው ሁሉ ስራውን ለሚያሰራን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም በፅሁፍ አሳውቀናል ምንም መፍትሄ የለም #የድሃ_ልጅ ነው እየተሰቃየ የሚገኘው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የአማራ ህዝብ እውነቱን ብቻ አይቶ ይዳኘን ፣ እነዚህ ወንድም ህዝቦች ናቸው የመጡት ለስራ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰራተኞቹን ጉዳይ እንደሚያውቅ ፣ ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ጋር በመሆን እየሰራበት እንደሆነ ገልጾ ለጊዜው ለታጋቾች ደህንነት ሲባል ከዚህ በላይ አስተያየት እንደማይሰጥ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከቪኦኤ ሬድዮ /ጋዜጠኛ ዮናታን ዘብዲዮስ ማግኘቱን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በማህበራዊ ሚዲያ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ብቻ ከማህበረሰቡ መልካም ባህልና ወግ የተቃረኑ አፀያፊ የፈጠራ ታሪኮችን / ወሬዎችን እየፈበረኩ በማሰራጨት የህዝብን ደህንነት ስጋት ላይ የሚጥሉ #ዩቲዩበሮችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 " አማረ እና ቤተሰቦቹ " በተባለ ህንፃ ላይ ቢሮ ተከራይተው የተለያዩ የዩቲዩብ ገፆችን በመክፈት የማህበረሰቡን ሥነ ልቦና የሚጎዱ የፈጠራ ታሪክ በማሰራጨት የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች በህዝብ ጥቆማና በፖሊስ ክትትል ተይዘዋል።

አሁን ላይ የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምርመራ እየተጣራ ይገኛል፡፡

በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል መቅደስ መብራት መኮንን የተባለችው ግለሰብ ፦
- ሮሄ፣
- ልዩነት፣
- ጣዕም፣
- አዲስ አለም፣ 
- ዘይቤ፣
- ህይወት፣
- እይታ፣  እና ዩኒት ህይወት የተባሉ የዩቲዩብ ገፆችን በመክፈት በስራ አስኪያጅነት ስትመራ የነበረች ናት ተብሏል፡፡

ብሩክ ወርቅነህ ጌታሰው የተባለ ግለሰብ ደግሞ ገፆቹን በምክትል ስራ አስኪያጅነት እና በአስተባባሪነት ሲመራ ነበር።

ናትናኤል አበራ በቀለ፣ እየሩሳሌም አስማረ ምህረት እና ምህረት ያሲን ቲጋ የተባሉት ግለሰቦች ደግሞ በፕሮግራም አቅራቢነት እንዲሁም ናትናኤል ዮሃንስ አሸነፊ በካሜራ ባለሙያነት ሲሰሩ የነበሩ ናቸው።

ከላይ ከተጠቀሱት 8 የዩቲዩብ ገፆች በተጨማሪ #ክህሎት እና #ሲንግል የተባሉ ሌሎች ሁለት የዩቲዩብ ገፆችም በዚያው ህንፃ ላይ የፈጠራ ወሬ ሲፈበርኩ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

ፖሊስ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ እና ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ ተከራይተው በሚሰሩበት ህንፃ 8ኛ እና 13ኛ ፎቅ በሚገኘው ቢሮአቸው ላይ በህግ አግባብ ባደረገው ብርበራ የፈጠራ ወሬ ለመቅረፅ እና ለማሰራጨት የሚጠቀሙባቸው የኤሌክትሮኒክ እቃዎች ተይዘዋል፡፡

ግለሰቦቹ መረጃውን ለማሰራጨት የሚያስችል ከሚመለከተው አካል የተሰጠ የህጋዊነት ማረጋገጫ ሆነ ፈቃድ እንደሌላቸው በምርመራ ሂደት ተረጋግጧል።

እነዚህ ተጠርጣሪዎች ሃሰተኛና የፈጠራ ወሬዎቹን የሚሰራጩት ታሪኩን ለሚተውኑላቸው ግለሰቦች #ገንዘብ_በመክፈል ሲሆን በወቅቱ ጉዳዩን በጥልቀት ሳይረዱ እና መረጃው ሳይኖራቸው የማያውቁትን የፈጠራ ታሪክ ሊሰሩ ለቀረፃ ስራ የተጠሩ ሌሎች 3 ሰዎችን ፖሊስ አግኝቷል፡፡   
 
መሰል የውሽት ታሪኮችን ቀልብ በሚስብ መልኩ እያቀናበሩ በማሰራጨት በህብረተሰቡ ላይ መደናገርን የሚፈጥሩ ሌሎች ግለሰቦችም ተለይተው የታወቁ  እና በቁጥጥር ስር ለማዋል የክትትል ስራው ተጠናክሮ የቀጠለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia