TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

ግለሰብን አግተው የዘረፉ የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመሰረተ።

አንድን ግለሰብ አስገድደው በያዙት ተሽከርካሪ ውስጥ በማገት ዶላርና የተለያዩ ንብረቶቹን ወስደዋል የተባሉ 3 የፖሊስ አባላት ላይ የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቷል።

3ቱ የፖሊስ አባላት ፦
ኮንስታብል ክብሩ በለጠ
ረ/ሳጅን ያለምሰው ዱሬ
ረ/ሳጅን ባህረዲን አለሙ ይባላሉ።

1ኛው ተከሳሽ በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ መምሪያ የተጠርጣሪ አስተዳደር ስር የጥበቃ አባል፣

2ኛው ተከሳሽ የተጠርጣሪ ክትትል እና ኦፕሬሽን ክፍል የኢኮኖሚ ነክ ጉዳዮች ወንጀሎች የፍርድ ቤት አስገዳጅ አባል፣

3ኛው ተከሳሽ በፎረንሲክ ምርመራ መምሪያ ስር በሹፌርነት ሲሰሩ ነበር።

ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ በ9 ሰዓት አካባቢ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 '  ጆን ጋራዥ  ' አካባቢ ካልተያዘ ሲቪል ከለበሰ ግብረአበራቸው ጋር በመሆን አንድ የግል ተበዳይን አስገድደው 3ኛ ተከሳሽ ለስራ አላማ የተረከበው ተሽከርካሪ ውስጥ በማገት ያስገባሉ።

አግተው ተሽከርካሪ ውስጥ ካስገቡም በኃላ ከግል ተበዳዩ ፦
° 2 ሺህ 600 ዶላር፣
° 2 የእጅ ስልክ
° 50 ሺህ ብር አስገድደው በመውሰድ ከተሽከርካሪው ገፍትረው ጥለውት እንደሄዱ በዐቃቤ ህግ የቀረበው የክስ መግዘብ ያስረዳል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዐቃቤ ሕግ የተመሰረተውን ክስ ዝርዝር ለተከሳሾች እንዲደርሳቸው ካደረገ በኋላ ጉዳያቸውን ማረሚያ ቤት ወርደው  እንዲከታተሉ በማዘዝ ለሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ፖሊስ ሰኔ 17/2016 ዓ/ም አንዲት መና ከበደ የተባለች የ26 ዓመት ወጣት ሴትን በመኪና ስርቆት ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ስር አውሏል።

ፖሊስ፥ ግለሰቧ ጥዋት 12:30 ገደማ ' ቤተል ቢጫ ፎቅ ' አካባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-B32912 አ.አ የሆነች ተሽከርካሪን የግል ተበዳይ መኖሪያ ቤቱ ደጃፍ ላይ ሞተር ሳያጠፋ አቁሞት ጃኬት ለመደረብ በገባበት ይዛ መሰወሯንና ከግማሽ ቀን ፍለጋ በኋላ ሰሚት አካባቢ መያዟን አስረድቷል።

ፖሊስ ግለሰቧንም ከነተሽከርካሪው ፎቶ በማንሳት አሰራጭቷል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ግለሰቧን እናውቃታለን ያሉ ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ፤ መኪናውን መውሰድ አለመውሰዷን በግልጽ ባያሰፍሩም የሃብታም ልጅ እንደሆነች ፣ ስህተት እንደተፈጠረና ከወንጀሉ ነጻ ተብላ ወደ ቤት መግባቷን ጽፈዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ይፋ ባደረገው መረጃ በተሽከርካሪ ስርቆት የተጠረጠረችው ግለሰብ መና ከበደ ክስ እንደተመሰረተባት አሳውቋል።

በዛሬው ዕለት ፍርድ ቤት መቅረቧንም አመልክቷል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ግለሰቧ ተሽከርካሪውን በመስረቋ ፓሊስ ምርመራ አጣርቶ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረትባት ማድረጉን አስረድቷል።

" በአንዳንድ  ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ' ግለሰቧ ተለቃለች ' እና ' ወንጀሉን ሳታውቅ ነው የፈፀመችው ' የሚሉ መረጃዎች እየተሰራጩ  ይገኛል " ያለው ፖሊስ የግል ተበዳይ መኪናቸው መሰረቁን ለፖሊስ እንዳመለከቱ ግለሰቧም ተሽከርካሪውን ለረጅም ሰዓት ይዛ መሰወሯ  ታሳቢ በማድረግና ድርጊቷም በማስረጃ በመረጋገጡ ዓቃቤ ህግ በተሽከርካሪ ስርቆት ክስ መመስረቱን አሳውቋል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
#AddisAbaba⛽️

በአዲስ አበባ የሚታየው የነዳጅ እጥረት በቀጣይ ቀናት እንደሚፈታ የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢዎች ድርጅት አሳውቋል።

የነዳጅ እጥረት በከተማዋ መከሰቱን የገለጸው ድርጅቱ " እጥረቱ ያጋጠመው በዒድ አል አድሃ አረፋ በዓል ምክንያት እሑድ ሰኔ 9 በማግሥቱ ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ነዳጅ ከጂቡቲ ባለመጫኑ ነው " ብሏል።

የነዳጅ ማጓጓዝ ሒደቱ አምስት እና ስድስት ቀናትን የሚወስድ መሆኑንና አሁን የሚስተዋለው እጥረት በመጪዎቹ ቀናት እንደሚፈታ አሳውቋል።

ከሱሉልታ መጠባበቂያ ቤንዚን ከአዋሽ መጠባበቂያ ደግሞ ናፍጣ እየተጓጓዘ መሆኑንም በማመልከት የነዳጅ ችግሩ በእርጠኝነት በ2 ቀናት እንደሚፈታ ተናግሯል።

በየተለያዩ የነዳጅ ማደያዎች ላይ ከሚታየው የነዳጅ እጥረት ባለፈ ማደያዎች ነዳጅን ከተጠቃሚዎች እንደሚደብቁ አሽከርካሪዎች ለሪፖርተር በሰጡት ቃል ገልጸዋል፡፡

ሕገወጥ በሆነ መንገድ በውኃ ፕላስቲኮች ጭምር የሚሸጡ መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም ምክንያት ባለፉት ሳምንታት በመዲናዋ ነዳጅ ለመቅዳት የሚጠብቁ ረዣዥም የተሽከርካሪ ሠልፎች መታየታቸውንና አሁንም እጥረቱ እንዳለ አክለዋል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከኮሪደር ስራው ጋር በተያያዘ ከመገናኛ ወደ ቦሌ የሚወስደው መንገድ ከሃያት ሆስፒታል በኋላ ከነገ ሰኔ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ሙሉ ቀንና ምሽትን ጨምሮ ለማንኛውም አይነት ተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረግ ተገልጿል።

አሽከርካሪዎች ሃያት ሆስፒታል ጋር ሳይደርሱ በፊት እና ከሆስፒታሉ አጠገብ ያሉትን የቀኝ መታጠፊያዎችን እንዲጠቀሙ የአ/አ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ጥሪ አቅርቧል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በ5ቱ ኮሪደር ልማት ስራ 16 ሺህ ሰዎች የስራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል " - ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ከተማ  ፦ ° መንገዶችን የማስፋት ፣ ° የመንገድ ዳሮችን የማሳመር ፣ ° የእግረኛና የሳይክል ብስክሌት መሄጃዎችን መስራት ° የቴሌ፣ የመብራት ኬብሎችን ወደ መሬት መቅበር ° የውሃ ፍሳሽ መሄጃዎችን መስራት ° ፕላዛዎችን መስራት የሚያጠቃልለው የኮሪደር ልማት ስራ በ5 ኮሪደሮች በመሰራት ላይ…
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ፤ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ የክረምት ወቅቱ ሳይጠናከር ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ከተማው አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

እስካሁን ባለው የፒያሳ እና የአራት ኪሎ መስመር እንዲሁም ከሜክሲኮ እስከ ሳር ቤት ያለው ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተመርቋል።

ከዚህ ቀደም ፦
- ከ4 ኪሎ - ፒያሳና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ ፣
- ከ4 ኪሎ አደባባይ በእንግሊዝ ኤምባሲ መገናኛ ፣
- ከሜክሲኮ ሳር ቤት በጎተራ ወሎ ሰፈር አደባባይ፣
- ከ4 ኪሎ መስቀል አደባባይ ቦሌ ድልድይ ፣
- ከቦሌ ድልድይ በመገናኛ እስከ አፍሪካ ኮንፌሽን አጠቃላይ 5 የኮሪደር ስራ እየተሰራ እንደሆነ መነገሩ ይታወሳል።

በከተማው እየተሰራ ያለው የኮሪደር ስራ ፥

ብዙሃን የሚጠቀሙበትን የእግረኞች መንገድ ማስፋት ምቹ ማድረግ፣
የተሽከርካሪ መንገዶችን ማስፋት፣ መታደስ ያለባቸውን የአስፋልት መንገዶች ማደስ፣
አላስፈላጊ ናቸው የተባሉ የመንገድ ማካፈያዎችን አንስቶ መንገድ ማስፋት፣
የመኪና ማቆሚያዎችን የመስራት፣
የመንገዶችን ዳር ማሳመር፣
የቴሌ፣ የመብራት ኬብሎችን ወደ መሬት መቅበር
ዘመናዊ የውሃ ፍሳሽ መሄጃዎችን መስራት
የሳይክል መንገድ መስራት
ፕላዛዎችን መስራት ሌሎች ተያያዥ ስራዎች የሚያጠቃልል ነው።

አብሮም ደረጃቸውን የጠበቁ መጸዳጃ ቤቶች እየተሰሩ ነው።

ሁሉንም የኮሪደር ስራዎች የክረምቱ ወቅት ሳይጠናከር ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እየተሰራ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማ አስተዳደሩ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

እንደ ከተማ አስተዳደሩ መረጃ ስራዎች በሳምንት 7 ቀን ለ24 ሰዓት (ማታ እና ቀን) እየተሰሩ ይገኛሉ።

ከዚህ ቀደም በአጠቃላይ ከ16 ሺ በላይ ለሆኑ ወጣቶች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸው መገለጹ ይታወሳል።

በሌላ በኩል ፥ ህንጻዎችን የማደስ ፣ ወደ ንግድ / ቢዝነስ ማዕከልነት የመቀየር እና በስታንዳርድ የተቀመጠውን መስፈርት / የህንጻዎች ቀለም ጭምር) እንዲያሟሉ እየተደረገ ነው ተብሏል።

ሌላው ደግሞ የኮሪደር ልማት በሚከናወንባቸው አካባቢዎች እና በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚገኙ የንግድና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከተለመደው የሥራ ሠዓት በተጨማሪ ቢያንስ እስከ ምሽቱ ሶስት ሰአት ድረስ ክፍት በማድረግ የንግድ እና የአገልግሎት ስራዎች እንዲካሄዱ  የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ወስኗል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ የወረቀት የነዋሪነት መታወቂያ ሙሉ በሙሉ መቆሙ ይፋ ሊደረግ ነው።

ከተማዋ በነዋሪነት ለመዘገበቻቸው ነዋሪዎች ለዘመናት በወረቀት ስትሰጥ የነበረውን የነዋሪነት መታወቂያ /City Residency ID/ ካርድ ሙሉ ለሙሉ ማቆሟን ይፋ ታደርጋለች።

አ/አ በዘመናዊ የከተማ አስተዳደር የከተማ የነዋሪነት መታወቂያን በተደራጀ መልኩ በመስጠት ከ75 ዓመት በላይ እድሜን አስቆጥራለች።

የወረቀት መታወቂያን ለመጨረሻ ግዜ ተሰናብታ ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል መሻገሯን ሰኔ 25/2016ዓ.ም ይፋ እንደምታደርግ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የትግርኛ እና የአፋን ኦሮሞ የቋንቋ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ አመራሮች የማጠቃለያ ፈተና እንደወሰዱ ተነገረ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፤ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ለ5 ተከታታይ ወራት የትግርኛ እና አፋን ኦሮሞ ቋንቋ ትምህርት ሲሰጥ እንደቆየ ተነግሯል።

ትላንትና የማጠቃለያ ፈተና እንደተሰጠ ተገልጿል።

ከክ/ከተማው በተገኘ መረጃ ፥ ከክፍለ ከተማ እስከ ወረዳ የሚገኙ 371 አመራሮች በትግርኛ እና በአፋን ኦሮሞ የቋንቋ ትምህርት ለ5 ወራት ሲከታተሉ ቆይተዋል።

አመራሮቹ ከአፍ መፍቻ ቋንቋቸው ተጨማሪ ቋንቋ ተምረው ትላንት የማጠቃለያ ፈተና መውሰዳቸው ተገልጿል።

የቋንቋ ትምህርቱ ሲሰጥ የነበረው ከጋራ ጉሪ 1ኛ ደረጃ  ትምህርት ቤት ጋር በመቀናጀት እንደነበረ ተነግሯል።

ክ/ከተማው ፤ ብልፅግና ፓርቲ በሀገሪቱ አምስት የስራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ ትኩረት በመስጠት እየሰራ ይገኛል ብሏል።

#AddisAbaba
#LamiKuraCommunication

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

አዲስ አበባ ፖሊስ ከሰኔ 5 እስከ ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ/ም ለ15 ቀናት በሁሉም ክ/ከተሞች ኦፕሬሽን ማካሄዱን አሳውቋል።

በርካታ የወንጀል ተጠርጣሪዎችንና ኤግዚቢቶችን በቁጥጥር ስር እንዳዋለም ገልጿል።

በተደረገው ኦፕሬሽን ፦
➡️ ከዚህ ቀደም የተሰረቁ 8 የተለያዩ ተሽከርካሪዎች ማስመለሱን ፤
➡️ ለወንጀል ፈፃሚዎቹ ሀሰተኛ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በተለጣፊ እስቲከር ሲያዘጋጁ የነበሩ ግለሰቦች ሀሰተኛ ሰሌዳ ለማዘጋጀት ከሚጠቀሙበት ኮምፒውተር ፣ ላፕቶፕ ፣ ፍላሽ እና ካሜራ ጋር በቁጥጥር ስር እንዳዋለ፤
➡️ የመኪና መያቸውን
➡️ ሞተር ብስክሌት በመጠቀም የቅሚያ ወንጀል የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ከ700 በላይ ሞባይል ስልኮች ማስመለሱን፤
➡️ የተሰረቀ እቃ ከሚገዙ ህገወጦች ላይ 108 ላፕቶፕ ߹6 ኮምፒዩተር ߹11 ካሜራዎች ߹ 2 ቴሌቪዥንና የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ከሸሸጉበት ቦታ መያዙን
➡️ 2 ክላሽ ከመሰል 120 ጥይቶች ጋር፣ 67 ልዩ ልዩ ሽጉጦች ከ568 መሰል ጥይት ጋር እንዲሁም 2 ኋላ ቀር መሳሪያ ከእነ ተጠርጣሪዎቹ በኦፕሬሽኑ መያዙን አመልክቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ኮንትሮባንድ ፣ ሀሰተኛና ሰነዶችን እና መድኃኒቶች በኦፕሬሽኑ መገኘታቸውን ገልጿል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው 24 ኮንደሚኒዬም ውስጥ መድሃኒት የማከፋፈልም ሆነ የመሸጥ ፍቃድ የሌላቸውና በህገ-ወጥ መንገድ መድሃኒት እያዘጋጁ ሲያከፋፍሉ የተገኙ ግለሰቦች ተዘዋል፡፡

ግለሰቦቹ ያዘጋጇቸውና ለገበያ ሊያቀርቧቸው የነበሩ ፦
° 169 ብልቃጥ መድሃኒቶች ፣
° 40 ግሉኮስ ፣
° በርካታ የመድሃኒት ብልቃጦች እና ህገ-ወጥ ስራቸውን ለመስራት የሚገለገሉበት አንድ ማሽንን ጨምሮ ፕሪንተር እና ላፕቶፕ በኤግዚቢትነት መያዙን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ህፃን ሶሊያን ዳንኤል ተገኝታለች። • " 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ ልትሰወር መቻሏል ተጠርጣሪዋ ገልጻለች " - የአዲስ አበባ ፖሊስ ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ባደረገው ጠንካራ ክትትል ሱሉልታ ከተማ ላይ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።…
#AddisAbaba

የሁለት ዓመቷን ሶሊያና ዳንኤል የተባለችውን ህፃን በመጥለፍና በከባድ ስርቆት ወንጀል የተከሰሰችው ግለሰብ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥታለች።

የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባት ቤዛዊት በቀለ የተባለችው ግለሰብ በሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራበት ከነበረበት ቤት (ሳሪስ አዲስ ሰፈር) መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ/ም ህጻን ሶሊያናን ይዛ በመሰወር ሱሉልታ ከተማ " ኖኖ መና አቢቹ " ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህፃኗን ሸሽጋ በተቀመጠችበት በአዲስ አበባ ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋሏን ይታወሳል።

ግለሰቧ በቁጥጥር ስር ከዋለች በኃላ የአ/አ ፖሊስ ምርመራ የማስፋት ስራ በመስራት ከዚህ ቀደም በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችባቸው አምስት የተለያዩ ቤቶች ልዩ ልዩ ንብረቶችን መስረቋን አረጋግጧል።

ከሰረቀቻቸው ንብረቶች መካከልም 2 ላፕቶፕ ፣ 1 ሞባይል ስልክ እና ሌሎች የተለያዩ ዕቃዎች ፖሊስ ባደረገው ጥረት ከሸጠችበት በምሪት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡

በግለሰቧ ላይ ምርመራ ተጣርቶ በከባድ ስርቆት እና ህፃን ልጅ መጥለፍ በሚል ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ልዩ ልዩ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ቤዛዊት በቀለ በ18 ዓመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ፤ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት ስራ የክረምት ወቅቱ ሳይጠናከር ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ከተማው አስተዳደር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። እስካሁን ባለው የፒያሳ እና የአራት ኪሎ መስመር እንዲሁም ከሜክሲኮ እስከ ሳር ቤት ያለው ተጠናቆ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተመርቋል። ከዚህ ቀደም ፦ - ከ4 ኪሎ - ፒያሳና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ዙሪያ…
#AddisAbaba

" በትልቅ ቁጠባ በ33 ቢሊዮን ነው እየተተገበረ ያለው " - ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

የአዲስ አበባ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ፥ የከተማው 5ቱ ኮሪደር ስራ እየተተገበረ ያለው በ33 ቢሊዮን ብር እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህን የተናገሩት ለብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል ነው።

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች ፥ መጀመሪያ ላይ የ5ቱም ኮሪደር ስራ ሲጠና ኮንሰልታንቶችና አጥኚው ቡድን መንገድ እና የመንገድ መሰረተ ልማት የሚፈጀው ከ40 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ እንደገለጹ አስረድተዋል።

" ይህ እንግዴ በወቅቱ ጥናት ነው በዚህ ተለዋዋጭ ገበያ " ያሉት ከንቲባዋ " እስካሁን ድረስ የተጠኑትን 5 ኮሪደሮች እየተገበርን ያለነው በ33 ቢሊዮን ነው " ብለዋል።

በ33 ቢሊዮን ብር እየተተገበረ ያለው ስራም " ትልቅ ቁጠባ የተተገበረበት ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

ስራው ብክነትን በመከላከል፣ የሚወጣውን ወጪም አስፈላጊ ነገር ላይ ብቻ እንዲሆን እየተደረገ ነው ብለዋል።

አንዳንድ በከተማው አስተዳደር የሚሰሩ ስራዎችም ለኮንትራክተሮች እንዳልተሰጡ የተናገሩት ከንቲባዋ ፥ ለአብነት የሜክሲኮ መንገድ በኮንትራክተር ሳይሆን በራስ አቅም መሰራቱን ገልጸዋል።

#TikvahEthiopia
#AddisAbaba

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት  #አዲስአበባ

ነገ በአዲስ አበባ የሚዘጉ መንገዶች ይኖራሉ።

ስለሆነም ነገ ለስራ፣ ለቤተሰብ ለጓደኛ ጥየቃ ለሌላም ጉዳዮች ፕሮግራም የያዛችሁ ፕሮግራማችሁን ከልሱ።

መንገድ የሚዘጋው " ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም " በሚል የጎዳና ላይ ሩጫ ስለሚካሄድ ነው።

ሩጫው መነሻውን መስቀል አደባባይ እንደሚያደርግ ተገልጿል።

ከዛም በባምቢስ፣ ዑራኤል አደባባይ ወደ ቀኝ፣ ፒኮክ መናፈሻ ፣ ሰላም መንገድ ፣ በወሎ ሰፈር ፣ ደንበል ፣ ፍላሚንጎ በማድረግ መስቀል አደባባይ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡

በዚህም  ፦
- ከ22 ወደ ዘሪሁን ህንፃ
- ከዘሪሁን ህንፃ ወደ ዑራኤል አደባባይ
- ከአትላስ መብራት ወደ ዑራኤል አደባባይ
- ከቦሌ ሩዋንዳ መታጠፊያ ወደ ወሎ ሠፈር
- ከወሎ ሠፈር ጀምሮ እስከ ጋዜቦ አደባባይ ውስጥ ውስጡን ወደ ዋናው መንገድ የሚያስወጡት መንገዶች
- ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ኦሎምፒያ አደባባይ
- ከኤግዚብሽን ወደ ፊላሚንጎ
- ከጥላሁን አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ
- ከለገሃር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከቴሌ ማቋረጫ (ክቡ) ባንክ ወደ ስታድየም
- ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ
- ከካዛንቺስ ሼል (ኢንተር ኮንትኔታል ሆቴል) ወደ ባምቢስ
- ከዑራኤል አደባባይ ላይ እና ታች ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:30 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ከዛሬ ምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ ደግሞ በተጠቀሱ መንገዶች ላይ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ተከልክሏል።

#AddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION🚨 " የበይነ መረብ (ኦንላይን) ተፈታኞች በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይ) እንዲሁም በወረቀት እንደሚሰጥ በዛሬው ዕለት በድጋሚ አሳወቀ። በሁለቱም መንገድ ለሚሰጠው ፈተና ዝግጅት ተደርጓል ብሏል። ትላንት እና ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ ያሉ አንዳንድ…
#AddisAbaba #NationalExam

“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም ” - ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማሪ ወላጆችና ከተማሪዎች ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ስለተጠየቀበት የበየነ መረብ (ኦንላይን) የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱን ጠይቋል።

ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ምን አሉ ?

“ ፈተና በሁለት አይነት መልኩ (በኦንላይንና በወረቀት) ይሰጣል።

በኦን ላይን የሚሰጠው ዩኒቨርሲቲ ላይ ተመድበው የነበሩ አብርሆት ላይብረሪና ሁለት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ብቻ ይሆናሉ።

የተቀሩት ግን በሁሉም በግልም በመንግስም መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩ ት/ቤቶች ሆኖ በተመደቡበት (ድልድል የወጣላቸው ት/ቤቶች ያውቃሉ) መሠረት ፈተናውን በወረቀት ይወስዳሉ።

በኦንላይን ፈተና የሚወስዱት፦
- በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ 
- በሲቪል ሰርቪስ
- በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 
- በአዲስ አበባ ሳይንሰና ቴክኖሎጂ
- በጳውሎስ ሚሊኒየም የተመደቡ በዚያ ይወስዳሉ።


እንዲሁም፣ በአብርሆት ላይብረሪ ላይ የተመደቡ ተማሪዎች፣ የሁለቱ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በኦንላይን ይወስዳሉ።

የቀሩት ግን በሌላ መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩት ስለታጠፈ በወረቀት ይወስዳሉ።

በወረቀት የሚወስዱት ዩኒቨርሲቲ ነው የሚገኙት በባለፉት ሁለት አመታት እንደተሰጠው ማደሪያቸውም፣ መዋያቸውም፣ መፈተኛቸውም እዛው ይሆናል። አድረው ሲጨርሱ ነው የሚወጡት።

በኦንላይን የተመደቡት ግን ውሎ ገብ ነው። ተፈትነው ወደ ቤታቸው ሂደው አድረው ተመልሰው በጠዋት መጥተው ይፈተናሉ። ” ብለዋል።

የተፈጠረው ውዝግብ ምንድን ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፥ “ የተፈጠረ ነገር የለም። በድብልቅ መንገድ እንደምንጥ ታሳቦ ነበረ። እሱን ነበር ስንለማመድ የነበረው ” ነው ያሉት።

“ አሁን More እርግጠኛ በተኮነበት መፈተኛ ጣቢያ (ከላይ በተገለጹት) ብቻ ይሰጣል። ” ሲሉ አክለዋል።

ትምህርት ቤቶች “ ቀርቷል ” ሲሉ ተስተውለዋል፤ ታዲያ መረጃውን ከየት አግኝተውት ነው ? ቢሮው ትዕዛዝ አውርዶ ነበር ? ስንል ኃላፊውን ጠይቀናል።

ዶ/ር ዘላለም ፥ “ በዩኒቨርሲቲዎችና በሌሎች ጣቢያቸዎች እንደሚሰጥ ነገር ግን ሌሎች ጣቢያዎች የነበሩት፣ በእነርሱ ላይ ካልሆነ በስተቀር ' ቀርቷል ' ተብሎ የተሰጠ መግለጫ አልነበረም ” ብለዋል።

አክለው፣ “ ለሙከራ ስንሞክርባቸው የነበሩ እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ተማሪዎችና ቤተሰብ ላይ እንግልት እንዳይሆን እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ቀንሰናል ” ያሉት ኃላፊው፣ “ በእርግጠኝነት ሊፈጸሙባቸው ተብሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ የተወሰኑት ላይ ግን ተወስኗል ” ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናው እንደቀረ ያስተላለፈው መልዕክት ነበር ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ደግሞ፣ “ ትምህርት ሚኒስቴር እኮ በገጹ ላይ አስታውቋል እንዳልቀረ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም። በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ተይዘው የነበሩት በተለያዩ ምክንያቶች ተቀንሰዋል ” ብለዋል።

ቢሮዎ ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ ለትምህርት ሚኒስቴር ጻፈው ተብሎ ሲሰራጭ የነበረው ደብዳቤ (ከላይ ተያይዟል) የቢሮ ነው ? ለሚለው ጥያቄ ፥ “አዎ። ትክክል ነው !! ” ብለዋል።

“ አሁን ባልናቸው ጣቢያዎች ማለት ነው። በፊት በ153 ጣቢያዎች ብለን ነበር ይዘን የነበረው አሁን ግን በእርግጠኝነት ይሳካል የተባለበት ቦታ ከላይ የተጠቀሱት ጣቢያዎች ብቻ ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል።

በመሆኑም በተቀመጠው መርሀ ግብር መሠረት ተማሪዎች ከምንም አይነት ውዢምብር ራሳቸውን ጠብቀው ከቢሮውና ከትምህርት ሚኒስቴር በሚወርዱ መመሪያዎች ብቻ ተረጋግተው እንዲፈተኑ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ በተገነቡት መሰረተ ልማቶች ላይ ቆሻሻ የጣሉ ፣ ከተፈቀደላቸው መንገድ ውጪ የሄዱ እንዲሁም በመንገድ አካፋዮች ላይ የተተከሉ ዛፎችን ' በግዴለሽነት ' በተሽከርካሪ በመግጨት ጉዳት ያደረሱ አካላት መቀጣታቸውን አሳውቋል።

3 ተቋማት ከተፈቀደ ቦታ ውጪ ቆሻሻ በመጣል እንደየጥፋት ደረጃቸው 100 ሺሕ ፣ 50 ሺ እና 20 ሺሕ ብር ተቀጥተዋል።

5 አሽከርካሪዎች በመንገድ አካፋይ ላይ የተተከሉ ዘንባባ ዛፎችን ገጭተው በመጣላቸው እንደየጥፋት ደረጃቸው ከ150 እስከ 300 ሺሕ ብር መቀጣታቸውን አሳውቋል።

11 ሰዎች ደግሞ ከተፈቀደው የእግረኞች መንገድ ውጪ በመሄዳቸው ከ150 እስከ 1000 ብር እንደተቀጡ ገልጿል።

ነዋሪዎች የተገነቡትን መሰረተ ልማቶች እንዲጠብቁ እና እንዲንከባከቡ ራሳቸውንም ከቅጣት እና ከትራፊክ አደጋ እንዲከላከሉ ጥሪ አቅርቧል።

(የቅጣት ደረሰኞቹ ከላይ ተያይዘዋል)

#AddisAbaba #MayorOffice

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://aa.ministry.et/account#/student-result ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ

የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ይፋ አድርገዋል።

በዚሁ መሰረት የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንዲሆን በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።

የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን ከወሰዱ 85,219  በመንግስት እና በግል ት/ቤቶች በቀን እና በማታ ትምህርታቸውን ከተከታተሉ ተማሪዎች መካከል 67,903 የሚሆኑት ማለትም 78.9% ያህሉ 50% እና በላይ ማምጣታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ተማሪዎች https://aa.ministry.et/account#/student-result ላይ በመግባት መለያ ቁጥር እና ስም በማስገባት ውጤታቸውን መመልከት ይችላሉ።

በቀጣይ ጥቂት ቀናት የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት በተመሳሳይ ይፋ የሚደረግ መሆኑ ተገልጿል።

#AddisAbabaEducationBureau

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ አካል ጉዳተኛ በመምሰል ስትለምን የነበረች ተጠርጣሪ ከእነ ግብረአበሯ መያዟን አስታወቀ።

ግለሰቦቹ በቀን እስከ 500 ብር ድረስ እንደሚያገኙ ታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዋ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይኖራት ነው አካል ጉደተኛ በመምሰል ወገቧን በጎማ በማሰር ዊልቸር ላይ በመሆን ስትለምን ትላንት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው " #መገናኛ " አካባቢ በህብረተሰቡ ጥቆማ የተያዘችው።

ግለሰቧን ከቦታ ወደ ቦታ ሲያንቀሳቅሳት የነበረው ተጠርጣሪም ተይዟል።

ተጠርጣሪዎቹ ዊልቸሩን በቀን 35 ብር ተከራይተው ለ8 ወር እንደተጠቀሙና በቀን እስከ 500 መቶ ብር እንደሚያገኙ ከሰጡት ቃል ማወቅ እንደተቻለ ፖሊስ አስረድቷል።

ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይኖርባቸው ጉዳተኛ በመስምሰል የሚያታልሉ እንዳሉ ህብረተሰቡ ሊገነዘብ ይገባል ሲል ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://aa.ministry.et/account#/student-result ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ይፋ…
#AddisAbaba

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል !

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠጡት ቃል ፦

“ የ8ኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ተለቋል። የማለፊያ ውጤት ወስነን ቆርጠን ይፋ አድርገናል።

ወንድም ሴትም 50ና ከዚያ በላይ ያመጡ ናቸው ወደ ሚቀጥለው ክፍል የሚያልፉት። የአካል ጉዳተኞች ማለፊያ ነጥብ 45 እና ከዚያ በላይ ነው።

78 በመቶ የሚሆኑት ተፈታኞቻችን አልፈዋል።

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል። ”


የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መመልከቻ : https://aa.ministry.et/account#/student-result
(መለያ ቁጥርና ስም ያስገቡ)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ይደረጋል፤ ከ2 እስከ 3 ወር ባለው ጊዜ ወደ ተግባር ይገባል " - የአ/ አ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን

በአዲስ አበባ ከተማ ጥዋትና ማታ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ ነው።

ጎዶሎ ቁጥር እና ሙሉ ቁጥር የኮድ 2 ተሽከርካሪዎችን በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ የሕግ ማዕቀፍ መዘጋጀቱ ተነግሯል።

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ፥ በሁለት እና በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ በከተማው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች ወደ ፈረቃ እንዲገቡ ይደረጋል ብሏል።

" ጥዋት ስራ መግቢያ እና ስራ መውጫ ሰዓት አካባቢ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ይታያል " ያለው መ/ቤቱ " ይህንን ለመቀልበስ ባለስልጣን መ/ቤቱ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ጥናት አስጠንቶ በአዲሱ ዓመት ተግባራዊ የሚደረጉ የፍሰት ማሻሻያዎች አሉ " ብሏል።

ከነዛ ውስጥ አንዱ የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ የሚንቀሳቀሱበት እንደሆነ ገልጿል።

የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ቅድመ ዝግጅት መደረጉንና የሕግ ማዕቀፍም መዘጋጀቱን በጣም ከዘገየ ከ2 እስከ 3 ወር ወደ ተግባር እንደሚገባ አስረድቷል።

" ይሄ ፍሰቱን ያሻሽላል " ያለው መ/ቤቱ " ፒክ ሀወር / ስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ጎዶሎና ሙሉ ቁጥር ተብሎ ፕሮግራም ወጥቶለት ለምሳሌ ዛሬ ሙሉ ቁጥር የሚንቀሳቀስ ከሆነ ነገ ጎዶሎ ቁጥር በፈረቃ እንዲንቀሳቀስ የሕግ ማዕቀፍ ረቂቅ ተዘጋጅቷል ሌሎችም ቅድመ ሁኔታዎች እየተመቻቹ ነው " ሲል አሳውቋል።

የኦሮሚያ እና ፌዴራል ታርጋ ሳይጨምር የአዲስ አበባ ታርጋ ብቻ ያላቸው ተሽከርካሪዎች ከ755 ሺህ በላይ እንደሆኑ የተገለጸው የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ከነዚህ ውስጥ የሚበዙት ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በመሆናቸው ነው ጥዋት እና ማታ በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚደረገው ብሏል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

#AddisAbaba #ኮድ2

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

የትራፊክ ማኔጅመንት የራሱን የተቋሙን በከፍተኛ ቦታ ላይ የሚገኙ ኀላፊን ማብራሪያ " የእኔ አቋም አይደለም " አለ።

በአዲስ አበባ ከተማ የኮድ 2 ተሸከርካሪዎች በፈረቃ እዲንቀሳቀሱ ሊደረግ መሆኑን ይህም ከ2 እስከ 3 ወር ባለው ጊዜ ወደ ተግባር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ማሳወቁ ይታወቃል።

መ/ቤቱ ይህንን ያሳወቀው በአንድ ከፍተኛ አመራሩ ነው።

በዛሬው ዕለት ደግሞ እራሱ ባለስልጣን መ/ቤቱ " ይሄ ወደፊት በጥናት የሚሆን እንጂ በቅርቡ  ተግባራዊ የሚሆን አይደለም " ብሏል።

መ/ቤቱ ፤ " ' በአዲስ አበባ ከተማ  ጥዋት እና ማታ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ ነው ' በሚል ርእስ በተቋሙ የትራንስፖርት ቁጥጥር ደንብ ማስከበር ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር /ተወካይ/ አቶ አያሌው ኢቲሳ ለሸገር ኤፍ ኤም የሰጡት ማብራሪያ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አቋም አይደለም "  ብሏል።

" ግለሰቡ ' ጎዶሎ ቁጥር እና ሙሉ ቁጥር የኮድ 2 ተሽከርካሪዎችን በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ የሕግ ማዕቀፍ መዘጋጀቱንና የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን፥ በሁለት እና በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ በከተማው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች ወደ ፈረቃ እንዲገቡ ይደረጋል ' ያሉት ከተቋሙ ያገኙትን መረጃ ተንተርሰው አይደለም " ሲል አክሏል።

"ጎዶሎ ቁጥርና ሙሉ ቁጥር ኮድ 2 ተሽከርካሪዎችን በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ የሕግ ማዕቀፍ ወደ ፊት ከመንግስት በሚሰጥ አቅጣጫ ተጠንቶ የሚሆን እንጂ በአሁኑ ወቅት ይህንኑ ተግባራዊ የሚደረግበት ሁኔታ የለም " ብሏል።

በአዲስ አበባ የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች ከ2 እስከ 3 ወር ባለው ጊዜ በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ መሆኑን ያሳወቁት የአ/አ ትራፊክ ማኔጅመንት ፦
- የትራንስፖርት ቁጥጥር ደንብ/ማስ/ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
- የተቋሙ ተወካይ
- በተቋሙ ውስጥ የሚሰሩ
- የህግ ማዕቀፍም ተዘጋጅቶ ማለቁን በእርግጠኝነት የተናገሩ ሰው ናቸው።

ነገር ግን ይህ መረጃ ይፋ ከሆነ ከአንድ ቀን በኋላ ተቋሙ " የግለሰቡ ማብራሪያ እኛን አይወክልም ፤ ማብራሪያውን የሰጡት ከተቋሙ መረጃ አግኘትውም አይደለም " ብሏል።

ይህን ማስተባበያ የተመለከቱ አስተያየት ሰጪዎች ቀድሞውኑ የህዝቡ ትርታ ለማድመጥ የተደረገ ነው ብለውታል።

" እንዴት አንድ ተቋም የራሱን ሰራተኛና ከፍ ባለ ቦታ የሚገኝ ኃላፊ እኔን አይወክልም ይላል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

በመሰረቱ ይህ ተግባራዊ ይደረግ ቢባልም የማይሆን እንደሆነ አስምረውበታል።

#AddisAbaba #ኮድ2

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተራዘሟል በአዲስ አበባ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ  እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ። ምዝገባው ሰኔ 30 ያበቃል መባሉ ይታወሳል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር  ቢሮ ይፋ ባደረገው መረጃ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ 248,469 የኪራይ ውል ምዝገባ ተከናውኗል። አሁንም ምዝገባው እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል። ነገር ግን ፦ - በርካታ ተመዝጋቢ በመኖሩ…
#AddisAbaba

" ለሁለተኛ ዙር አይራዘምም " - የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፤ የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት ምዝገባ  ለሁለተኛ ጊዜ የማይራዘም መሆኑ አሳውቋል።

ቢሮው በመጀመርያው የምዝገባ ወቅት የነበረው መጨናነቅ እንዳይደገም ነዋሪዎች ከወዲሁ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት በነዋሪዎች ጥያቄ መሰረት መራዘሙን ያስታወሰው ቢሮው " ነገር ግን አሁንም መዘናጋት እንደሚታይ " ገልጿል።

ባለፍነው ሰኔ 1 ጀምሮ ሰኔ 30 ይጠናቃቀል ተብሎ በነበረው ስምምነት በመጀመርያዎቹ ምዝገባ ቀናት ከፍተኛ የሆነ መቀዛቀዝ እንደነበር  ፤ ነገር ግን በወሩ መጨረሻ አካባቢ ከፍተኛ ቁጥር የነበረው ተዋዋይ መገኘቱን አመልክቷል።

በዚህም በቀን ከ30,000 በላይ ነዋሪ ይመዘገብ እንደነበር ተጠቁሟል።

በነዋሪዎች ጥያቄ የውል ስምምነቱ እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ/ም ቢራዘምም አሁንም መዘናጋት እንደሚታይ ተጠቁሟል።

የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት ለሁለተኛ ጊዜ የማይራዘም በመሆኑና በመጀመርያው የምዝገባ ወቅት የነበረው መጨናነቅ እንዳይደገም ነዋሪዎች ከወዲሁ እንዲመዘገቡ ቢሮው ጥሪ ቀርቧል።

#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministrationBureau

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንደሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በከተማዋ በሚገኙ የመንግሥት እና የግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው፥ በ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85,046 ተማሪዎች መካከል 80,198 ተማሪዎች ወይም 94.3 በመቶዎቹ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡

የተማሪ ወላጆች ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን የመለያ ቁጥር እና ስም በማስገባት ውጤት መመልከት ይችላሉ። ወይም ከስር የተቀመጠውን የቴሌግራም ቦት ይጠቀሙ፡፡

ውጤት ለማየት፦ https://aa6.ministry.et/#/result

በቴሌግራም ቦት፦ @emacs_ministry_result_qmt_bot

@tikvahuniversity