TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ATTENTION🚨

“ የ2 አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” - ከእገታ ያመለጠ ተማሪ

“ ‘ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም ፤ ታግተናል ’ አለችኝና ከዛ ስልኳ አይሰራም ” - የአንዷ ታጋች ተማሪ እህት

“ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው ” - የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት

ሰኞ እለት ተሳፍረው ወደ ቤተሰብ እየተጓዙ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት ያሉ ተማሪዎች በታጣቂዎች መታገታቸውን የዓይን እማኝ፣ የታጋች ቤተሰብና ዩኒቨርሲቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

አንድ ከእገታው አመለጥኩ ያለ ተማሪ ፥ ሶስት (3) አውቶብሶች የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እየተጓዙባቸው የነበሩ ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ከረፋዱ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ የሚባል ቦታ ሲደርሱ መታገታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ከ3 አውቶብሶች 2ቱን ታጣቂዎች እንዳስቆሟቸው፣ ተሳፋሪዎቹን ካስወረዷቸው በኋላ አግተው ወደ ጫካ እንዳስገቧቸው፣ እርሱ ገለባ ውስጥ ተደብቆ እንዳመለጠ ገልጾ፣ “ የሁለቱ አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” ብሏል።

ከታጋቾቹ መካከል የሚያውቃቸው የIT ፣ የአኒሚል ሳይንስ ዲፓርትመንት ተማሪዎች እንዳሉ ገልጾ፣ ያገቷቸው “የሸኔ ታጣቂዎች” መሆናቸውን አስረድቷል።

አንዷ የታጋች እህት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል፣ “ ረቡዕ 3 ሰዓት ከ28 ደቂቃ ደወለችልኝ (እየሮጡ ነበር፣ የተኩስ ድምጽም ነበር) ‘በቃ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም። ላታገኝኝ ትችያለሽ በታጣቂዎች ታግተናል’ አለችኝ። መለሽ ስደውል ስልኳ አይሰራም ” ብላለች።

ቤተሰቡ ሁሉ በጣም ከፍተኛ ጭንቀት ላይ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ታጋቾቹን በህይወት እንዲያተርፏቸው ተማጽናለች።

በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፤ የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት በበኩሉ፣ እገታው እውነት መሆኑን እንዳረጋገጠ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

ኀብረቱ በሰጠው ቃል “ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው። ‘ ገንዘቡን ካላመጣችሁ እንገድላችኋለን ’ እያሏቸው ይገኛል ” ሲል የሰማውን አስረድቷል።

የሞቱ ፣ የተጎዱ ስለመኖራቸው የደረሰው መረጃ እንደሌለ የገለጸው ማህበሩ ፣ የሚመለከታቸውን  አካላት ሁሉ ለማነጋገር ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።

በጉዳዩ ላይ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሰጠንን ምላሽ በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION🚨 “ የ2 አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” - ከእገታ ያመለጠ ተማሪ “ ‘ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም ፤ ታግተናል ’ አለችኝና ከዛ ስልኳ አይሰራም ” - የአንዷ ታጋች ተማሪ እህት “ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው ” - የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ሰኞ እለት ተሳፍረው ወደ ቤተሰብ እየተጓዙ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ከ2ኛ እስከ…
#Update

“ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” - ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ ገብረ ጉራቻ ላይ በታጣቂዎች የታጋቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው ፤ ምን እየተሰራ ነው ? ሲል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል።

የዩቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስማማው ዘገዬ፣ “ ጉዳዩን ሰምተናል። ከዚህ ድርጊት ያመለጡ ተማሪዎች ነግረውናኛል ” ብለዋል።

“ እንደነገሩኝ እኔ ማድረግ ያለብኝን ለሚመለከተው የፌደራል መስራያ ቤት፣ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” ነው ያሉት።

“ እነርሱም ‘ ለሚመለከተው የጸጥታ አካል ሪፓርት እናደርጋለን ’ ብለውኛል ” ያሉት ዶክተር አስማማው፣ “ እኔ ከእገታ ያመለጡትን ልጆች Informally communicate አድርጌአቸው ነበር ” ብለዋል።

አክለው፣ “ መከላከያ አብዛኛዎቹን ልጆች አስመልሶ መከላከያ ካምፕ ውስጥ ያደሩ ልጆች እንዳሉ ሰምቻለሁ። የተወሰኑ ደግሞ በሌላ መኪና ተሳፍረው አዲስ አበባ የገቡ እንዳሉ ሰምቻለሁ ” ነው ያሉት።

“ ግን ቀሪ ልጆች በጣም ዝናባማ ስለነበር መከላከያና ፓሊስ ሳይደርስባቸው አጋቾቹ ይዘዋቸው የሄዱ የተወሰኑ ልጆች እንዳሉ ሰምቻለሁ ” ሲሉ ተናግረዋል።

ከዩኒቨርሲቲው የወጡት ተማሪዎች ቁጥራቸው ስንት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ “ ቁጥራቸውን አናውቀውም የኛ ሲነር ተማሪዎች የመጨረሻ ግቢ የቆዬ 2ኛ፣ 3ኛና 4ኛ ዓመት ተማሪዎች ከደባርቅ ጎንደር ነው የተሳፈሩት በአውቶብስ ” ብለዋል።

“ ቁጥራቸውን በእርግጠኝነት አላውቀውም ” ያሉት ዶክተር አስማማው ፥ “ ግን በሶስት አውቶብስ የኛ ተማሪዎች እንደተሳፈሩ መረጃው አለኝ። ከ3ቱ ሁለቱ አውቶብሶችን ነው ያስቆሟቸው ” ነው ያሉት።

የታጋች ተማሪዎች ሁኔታ የሚመለከታቸው አካላትን በመጠየቅ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ተጨማሪ የሥራ ዘመን መቀጠል የሚችሉበት እድል ነበር ?

" ቴክኒካሊ ይቻላል ማድረግ (በኃላፊነት ቦታው ላይ መቀጠል)  ፤ ... ሙሉ በሙሉ በፍላጎቴ ነው ላለመቀጠል የወሰንኩት " - ዶክተር ዳንኤል በቀለ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል በቀለ የ5 ዓመት የሥራ ዘመን አብቅቷል።

ምንም እንኳን ዶክተር ዳንኤል ለተጨማሪ የኃላፊነት ዘመን በቦታው ላይ ለመቆየት እድል ቢኖራቸውም ለ2ኛ ዙር የኃላፊነት ዘመን መቀጠል እንደማይፈልጉ ወስነዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ም/ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለን የዋና ኮሚሽነሩ ስልጣናቸው ሊራዘም ይችል ነበር ወይ ? ሲል ጠይቋል።

እሳቸውም ፦

" አንዱ የሪፎርሙ ሀሳብ የኃላፊነት ጊዜው ሲያልቅ ሊለቅ ይችላል የሚል ነው። ሌላ የሚከተለውን ሰው እንዲያመጣ።

ሁል ጊዜ ቢሆን እስከመጨረሻ ድረስ በአዋጁ ላይ የተቀመጠውን ለጥጦ መጠቀም ሳይሆን አንዳንድ ጊዜ አንድ የኃላፊነት ዘመን / ዙር ጨርሶ ሌላ ሰው ይምጣ ፤ በተለይም ውስጥ ያለ ሰው መተካት ይቻላል ነው።

ዋና ኮሚሽነሩ እራሳቸው ናቸው ከዚህ በኃላ ለሁለተኛ የኃላፊነት ዘመን አልሄድም ብለው የወሰኑት " ሲሉ መልሰዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉዳይ ላይ ዶክተር ዳንኤል በቀለንም አነጋግሯቸዋል።

ሁለተኛ ዙር ላለመቀጠል በራስዎት ፍላጎት ወስነው ነው ? ቢፈልጉ ሕጉ ይፈቅድሎታል ? ሲል ጠይቋል።

ዶክተር ዳንኤል ፥ " አዎን !!! በራሴ በፍላጎቴ ነው። ቴክኒካሊ ይቻላል ማድረግ (በኃላፊነት መቀጠል) ከተቋም ግንባታ አንጻር እኔ እንደዛ አልመክርም ምክንያቱም ተቋም መገንባት ማለት አንድ ሰው ዝም ብሎ መቀጠል ሳይሆን (renewal ስለሚፈቅድ) ተቋም ፈጥረህ ከዛ ማሸጋገር ይመስለኛል። ሙሉ በሙሉ በፍላጎቴ ነው ላለመቀጠል የወሰንኩት " ብለዋል።

በቀጣይ የት ሊሰሩ ይችላሉ ? የሚለውን በተመለከተ " ያህንን ለማሰብ ጊዜም አላገኘሁም። እስካሁን ምንም አላውቅም። ቀጣይ ስራዬ ምን እንደሆነ አልወሰንኩም። " ሲሉ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” - ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ ገብረ ጉራቻ ላይ በታጣቂዎች የታጋቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው ፤ ምን እየተሰራ ነው ? ሲል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል። የዩቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስማማው ዘገዬ፣ “ ጉዳዩን ሰምተናል። ከዚህ ድርጊት ያመለጡ ተማሪዎች ነግረውናኛል ” ብለዋል።…
#Update

በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ?

ትምህርት ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ መታገታቸውን  አይዘነጋም።

ታጋቾቹን ከእገታ ለመልቀቅ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እንደጠየቁ ፤ ዩኒቨርሲቲውም ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፓርት እንዳደረገ መረጃ ተለዋውጠን ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ አለ ?

የተወሰኑ ታጋቾች ከእገታ ቢለቀቁም የተወሰኑት ግን አሁንም እንዳልተለቀቁ፣ ቤተሰቦቻቸው እና በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ የወንጌላዊያን የክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የታጋች ቤተሰቦች በገለጹት መሠረት፣ 150 የሚሆኑ ተማሪዎች ዛሬ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ግን እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ካልከፈሉ እንደማይለቀቁ ተነግሯቸዋል።

በዛሬው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ከተማ እየተመለሱ ነው የተባሉት ተማሪዎች በአጋቾች ስር ከነበሩት መካከል እና በተለያዩ ቦታዎች ተደብቀው ከእገታ ማምለጥ የቻሉ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ተናግረዋል።

የወንጌላዊያን ተማሪዎች ህብረት በበኩሉ፣ አሁንም ገና በአጋቾች እጅ ያሉ ፣ ወደ ቤተሰብ መመለስ እየቻሉ ተሽከርካሪ ያላገኙ ፣ የተወሰኑት ታጋቾች ግን እንደተለቀቁ ማረጋገጡን ጠቁሟል።

ተለቀቁ የተባሉትም ከአጋቾቹ ጋር ተግባብተው እንጂ ገንዘብ ከፍለው እንዳልሆነ የተመላከተ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በችግር ላይ እንደሆኑ መረጃው እንደደረሰው ገልጿል።

ታጋቾቹ በትልቅ ጫካ ታጉረው እንደሚገኙ እና ገንዘብ እየተጠየቁ መሆናቸውን የታጋች ቤተሰቦች ጠቁመዋል።

በዚህ ኑሮ ውድነት ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደማያገኙ ለገልጸው መንግስት ለታጋቾች እንዲደርስላቸው በእንባ ታጅበው ተማጽነዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ዙሪያ ምን እየሰራ እንደሆነ ለመጠየቅ የተደረገው ሙከራ ተደጋጋሚ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለጊዜው ሳይሳካ ቀርቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia “... የፌደራል ፓሊስ በፓትሮል መንገድ ላይ ወጥቶ እንዲሰራ ሁሉ ተደርጓል ” - ትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር የድንበር ተሻጋሪ የከባድ መኪና #አሽከርካሪዎች አገር ውስጥ ከገቡ በኋላ በታጠቁ ኃይሎች እስከ ግድያ የሚድረስ ጥቃት እንደሚፈጸምባቸው መግለጻቸውን በተደጋጋሚ መረጃ ተለዋውጠን ነበር። አሽከርካሪዎቹ፣ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እየሰጠ እንዳልሆነ…
“ ባለፉት 10 ቀናት 5 አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል ” - ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር

የአሽከርካሪዎች ግድያ፣ የተሳፋሪዎች እገታ፣ የህግ አግባብ የሌለው የ‘ኮቴ’ ክፍያ እንዳልቆመ ጣና የከባድ መኪና የአሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

“ በቅርቡ በአማራ ክልል ፤ ማክሰኝት አካባቢ አንድ ሹፌር ተገድሏል። ከዚያ በፊትም እዚያው ሌላ አሽከርካሪ ተገድሏል ” ሲል አመልክቷል።

ጥቃቱ በተለያዩ ክልሎች ሲፈጸም እንደሚስተዋል ጠቁሞ፣ “ በኦሮሚያ ክልል ‘55’ ተብሎ የሚጠራው አካባቢም አንድ አሽከርካሪ ተገድሏል ” ነው ያለው።

ከግድያው በተጨማሪ እገታም እንዳልቆመ ያስረዳው ማኀበሩ፣ “ በአጠቃላይ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል 3 አሽከርካሪዎች ተገድለው፤ በታታ የነበሩ ተሳፋሪዎች ታፍነው መወሰዳቸው መረጃ ደርሶናል (ጫንጮ ወጣ ብሎ) ” ብሏል።

ማኀበሩ፣ ከዚህ ቀደምም ጥቃቱ በተደጋጋሚ ጊዜ ሲፈጸም እንደተስተዋለ አስታውሶ፣ “ ቅርብ ቀንም እነዚህ (ከላይ የተዘረዘሩት) ጥቃቶች ተፈጽመዋል ” ሲል አስረድቷል።

“ የአሁኑ ጥቃት የቅርብ ጊዜ ጥቃት ነው። ባለፉት 10 ቀናት ውስጥ 5 አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች ተገድለዋል ” ያለው ማኀበሩ፣ ባለፉት ዓመታት ከ120 የሚበልጡ አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች እንደተገደሉ አስታውቋል።

በተያያዘም፣ የ ‘ኮቴ’ እየተባለ የሚጠየቀው ከህግ አግባብ ውጪ የሆነ ከ2,000 ብር በላይ ክፍያ ኦሮሚያ ክልል ላይ አሁንም እንዳልቆመ፣ ከክልሉ ሳይወጡ ራሱ እስከ 5 ጊዜ ለመክፈል እንደሚገደዱ ሹፌሮች ተናግረዋል።

ማኀበሩ በበኩሉ፣ ይሄው ቅሬታ ትክክል መሆኑን አረጋግጦ፣ “ ከጂቡቲ ለሚጫን እቃ የ ‘ኮቴ’ የሚለው ቃል ራሱ ከአፍ ሊወጣ አይገባም ነበር” ሲል ወቅሷል።

በመንገድ ላይ ስለሚፈጸም የታጣቂዎች ጥቃት ምን እየሰራ እንደሆነ ከዚህ ቀደም የጠየቅነው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር፣ “ ከሚኒስቴር መ/ቤታችንም ሌላም አካል ዳይሬክሽን ተሰጥቶ፣ እንዲያውም ፌደራል ፓሊስ በፓትሮል መንገድ ላይ ወጥቶ እንዲሰራ ሁሉ ተደርጓል ” ማለቱ ይታወሳል።

የ‘ኮቴ’ ክፍያውን ቅሬታ በተመለከተም ችግሩ መኖሩን አምኖ፣ “ ከኦሮሚያ ክልል መንግስትም ጋር አውርተን መፍትሄ የምንሰጥ ይሆናል ” ነበር ያለው።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ? ትምህርት ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ መታገታቸውን  አይዘነጋም። ታጋቾቹን ከእገታ ለመልቀቅ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እንደጠየቁ ፤ ዩኒቨርሲቲውም ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፓርት እንዳደረገ መረጃ ተለዋውጠን…
#Update

(ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም)

ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል።

የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት ቦታ በቡድን ከፋፍለው በእግር እያጓጓዟቸው እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህንን ነገር የሰሙት አጋቾቹ ደውለው " ልጆቻችሁ እንዲለቀቁ ገንዘብ አምጡ " ብለው በዛቱበት እና ከልጆቻቸው ጋር በስልክ በተገናኙበት ወቅት ነው።

አጋቾቹ ገንዘብ እንዲላክላቸው ፤ ለዚህም ትንሽ ጊዜ እንዲሰጡ ቢጠየቁም ለመስማት ፈቃደኞች እንዳልሆኑ የታጋች ቤተሰቦች ገልጸዋል።

የልጆቻቸው ደህንነት እጅግ በጣም በከፋ ጭንቀት ላይ እንደጣላቸው ገልጸው ልጆቻቸውን ወደ ሌላ አገር እንዳያስወጧቸው መከላከያ እና ፌደራል ፓሊስ ክትትል አድርገው እንዲታደጉላቸው ተማጽነዋል።

ቲክቫህ ያነጋገረው የወጌላዊያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረትን በበኩሉ፣ ትላንት መኪና እየጠበቁ የነበሩት መኪና አግኝተው ወደ ቤተሰብ ጉዞ ማድረጋቸውን ገልጿል።

ቀሪዎቹ ግን አሁንም ገንዘብ በታጋቾቹ እየተጠየቁ ነው ብሏል።

በታጋች ተማሪዎቹ ጉዳይ አዲስ ነገር አለ ? ሲል ቲክቫህ የጠየቃቸው የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አንድ አካል ፥ ለበላይ ሪፓርት ከማድረግ ውጪ ምንም ማድረግ እንዳልተቻለ ገልጸዋል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz • “ የውሃ አቅርቦት ተቋርጦ ችግር ላይ ወድቀናል ” - ነዋሪዎች • “ የመብራት ችግር ነው ” - የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ • “ የተቋረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀጠል እየተከታተልን ነው ” - የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ባለመኖሩ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ…
#BenishangulGumuz

° “ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ 3 ወር ሆነው። ጨለማ ውስጥ እየኖርን ነው” - የወምበራ ወረዳ ነዋሪዎች

° “ ከወረዳው መንግስት ጋር እየተየጋገርን ነው፤ በቅርቡ እንሰራዋለን ” - የደብረ ዘይት ማዕከል

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ ወምበራ ወረዳ ደብረ ዘይት ከተማ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጨለማ ውስጥ ለመኖር መገደዳቸውን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

“ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ 3 ወር ሆነው። ጨለማ ውስጥ እየኖርን ነው። የፋሲካ በዓል አካባቢ ሁለት ቀን በርቷል ከዚያ በኋላ ምንም የለም ” ብለዋል።

ችግሩ ፦
-  በኑሯቸው ላይ ፈተና እንደሆነባቸው፣
- ተማሪዎች ለመማር፣ ፕሮጀክቶችን ለመስራት እንደተቸገሩ፣ 
- ለስልክ ቻርጅ በጀኔሬተር 20 ብር እንደሚከፍሉ፣ 
- በመስሪያ ቤታቸው ጀነሬተር፣ በቤታቸው Solar Energy ስላላቸው ባለስልጣናቱ ለጉዳዩ ቸልተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

“ ግብር እየከፈልን መሰረታዊ የሆኑ አገልግሎት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ አለመጠቀም ግን አግባብነት የሌለው ቅሬታን የሚያስነሳ ጉዳይ ነው ” ብለዋል።

በወረዳው የታላቁ ህዳሴ ግድቡ በቅርበት ቢገኝም ተጠቃሚ ባለመሆናቸው የሚመለከተው አካል ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

አቶ የኔሰው የኤሌክትሪክ አገልግሎት የደብረ ዘይት ማዕከል ኃላፊ አገልግሎቱ ለምን እንደተቋረጠ ጠይቀናቸው በሰጡት ምላሽ፣ ቡለን ላይ ኤሌክትሪክ ስለተቋረጠ መሆኑን አስረድተዋል።

"እንደ ወንበራ ደብረ ዘይት ቅድሚያ የቡለን ማዕከል ራሱን የቻለ አለ። እሱ ከበራ በኋላ ነው እኛ ማብራት የምንችለው። ቡለን ከበራ ይበራል" ብለዋል።

ችግሩን ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ "ከወረዳው መንግስት ጋር እየተየጋገርን ነው፤ በቅርቡ እንሰራዋለን" የሚል ምላሽ ተሰጥተዋል።

የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ካሳሁን ከበደ ሰሞኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ "የተቋረጠው ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀጠል እየተከታተልን ነው" ብለው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ “ ሀኪሞች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው። ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት፤ ቤት እንኳ የላቸውም። በአውቶብስ ተጋፍተው ነው እየመጡ የሚሰሩት። ይህ ችግር ግን የጤና እከል የደረሰበትን ማህበረሰብ ከማገልገል አልከለከላቸውም ፤ ያንን እያደረጉ ግን ሲታመሙ እንደ ሞያተኛ ሳይሆን ለምነው ነው የሚታከሙት። ” - ዶክተር በሀሩ በዛብህ (የኢትዮጵያ ሕክምና ማኅበር የቦርድ አባል - ለቲክቫህ…
#EMA

“ ሀኪሞች ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው፤ ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት ” - የኢትዮጵያ ህምክምና ማህበር

የኢትዮጵያ ህክምና ማህበር (EMA) በየዓመቱ ሰኔ 25 ቀን የሚከበረውን “ 7ኛውን የሀኪሞች ቀን ” በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተከብሮ ነበር።

በዚህም በዘንድሮው ' የሀኪሞች ቀን ' ከጌራ የቤት ለቤት ህክምናና የሀኪሞች ቢሮ ተቋም ጋር በመሆን 2,000 ለሚጠጉ የማህበረሰብ ክፍሎች የቤት ለቤትና የጎዳና ላይ ነጻ የህክምና ለመስጠት ማቀዱን አመላክቷል።

ይኸው የነጻ ህክምና ከሐምሌ 1 /2016 ጀምሮ ነው የሚሰጠው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በተመለከተ፣ ከ34 ዓመታት ጀምሮ በአጥንት ቀዶ ህክምና እያገለገሉ የሚገኙትን የማኀበሩ የቦርድ አባልና የአባላት ጉዳይ የሚከታተሉት ዶ/ር በሀሩ በዛብህን ጠይቋል።

እሳቸው በሰጡት ቃል፣ “ ሀኪሞች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር አለባቸው፤ ኩሽና ተከራይተው ነው የሚኖሩት። ቤት እንኳ የላቸውም። በአውቶብስ ተጋፍተው ነው መጥተው የሚሰሩት ” ብለዋል።

“ ይህ ችግር የጤና እከል የደረሰበትን ማህበረሰብ ከማገልገል አልከለከላቸውም ” ያሉት ዶ/ር በሀሩ፣ “ ያን እያደረጉ ግን ሲታመሙ እንደ ሞያተኛ ሳይሆን ለምነው ነው የሚታከሙት ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ መብራት ኃይል ለአባላቱ መብራት፣ ቴሌ ለአባላቱ የአየር ሰዓት፣ ውሃና ፍሳሽ ለአባላቱ ውሃ ይሰጣሉ። የእኛ ጤና ሲታወክ እንኳ ምንም አይሰጥም። በህግም የተቀመጠ ነገር የለም ” ሲሉ አማረዋል።

“ የሥራ ሁኔታዎች ራሱ አልተመቻቹም ፤ ከሌላ አገር ጋር ሲገጻጸር እየሰራን የሚከፈለን እራሱ ውስን ነው ” ብለዋል።

“ መሬት እንኳን ቢሰጠን ምን ችግር አለው ? መኖር ነው ያቃተን። የሚከፈለን ገንዘብ በጣም ውስን ነው ” ሲሉ አክለዋል።

በዘርፉ የበዙ ችግሮች ከመኖራቸው አንጻር በርካታ ሀኪሞች ከአገር ለመውጣት እየተገደዱ መሆኑን ገልጸው፣  መንግስት ልቦና ሰጥቶት ለሚስተዋሉ ችግሮች ሁሉ መፍትሄ እንዲሰጥ በማኀበሩ ስም ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ህክምና ማኀበር / EMA ከተመሠረተ 75 ዓመታትን እንዳስቆጠረ፣ በኢትዮጵያ ከ15,000 እስከ 20,000 ሀኪሞች እንዳሉ ተመላክቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION🚨 " የበይነ መረብ (ኦንላይን) ተፈታኞች በተመደባችሁበት የፈተና ጣቢያ ተገኝታችሁ ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳስባለን " - ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ሚኒስቴር የ12ኛ ክፍል ፈተና በበይነ መረብ (ኦንላይ) እንዲሁም በወረቀት እንደሚሰጥ በዛሬው ዕለት በድጋሚ አሳወቀ። በሁለቱም መንገድ ለሚሰጠው ፈተና ዝግጅት ተደርጓል ብሏል። ትላንት እና ከትላንት በስቲያ በአዲስ አበባ ያሉ አንዳንድ…
#AddisAbaba #NationalExam

“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም ” - ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማሪ ወላጆችና ከተማሪዎች ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ስለተጠየቀበት የበየነ መረብ (ኦንላይን) የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱን ጠይቋል።

ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ምን አሉ ?

“ ፈተና በሁለት አይነት መልኩ (በኦንላይንና በወረቀት) ይሰጣል።

በኦን ላይን የሚሰጠው ዩኒቨርሲቲ ላይ ተመድበው የነበሩ አብርሆት ላይብረሪና ሁለት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ብቻ ይሆናሉ።

የተቀሩት ግን በሁሉም በግልም በመንግስም መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩ ት/ቤቶች ሆኖ በተመደቡበት (ድልድል የወጣላቸው ት/ቤቶች ያውቃሉ) መሠረት ፈተናውን በወረቀት ይወስዳሉ።

በኦንላይን ፈተና የሚወስዱት፦
- በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ 
- በሲቪል ሰርቪስ
- በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 
- በአዲስ አበባ ሳይንሰና ቴክኖሎጂ
- በጳውሎስ ሚሊኒየም የተመደቡ በዚያ ይወስዳሉ።


እንዲሁም፣ በአብርሆት ላይብረሪ ላይ የተመደቡ ተማሪዎች፣ የሁለቱ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በኦንላይን ይወስዳሉ።

የቀሩት ግን በሌላ መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩት ስለታጠፈ በወረቀት ይወስዳሉ።

በወረቀት የሚወስዱት ዩኒቨርሲቲ ነው የሚገኙት በባለፉት ሁለት አመታት እንደተሰጠው ማደሪያቸውም፣ መዋያቸውም፣ መፈተኛቸውም እዛው ይሆናል። አድረው ሲጨርሱ ነው የሚወጡት።

በኦንላይን የተመደቡት ግን ውሎ ገብ ነው። ተፈትነው ወደ ቤታቸው ሂደው አድረው ተመልሰው በጠዋት መጥተው ይፈተናሉ። ” ብለዋል።

የተፈጠረው ውዝግብ ምንድን ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፥ “ የተፈጠረ ነገር የለም። በድብልቅ መንገድ እንደምንጥ ታሳቦ ነበረ። እሱን ነበር ስንለማመድ የነበረው ” ነው ያሉት።

“ አሁን More እርግጠኛ በተኮነበት መፈተኛ ጣቢያ (ከላይ በተገለጹት) ብቻ ይሰጣል። ” ሲሉ አክለዋል።

ትምህርት ቤቶች “ ቀርቷል ” ሲሉ ተስተውለዋል፤ ታዲያ መረጃውን ከየት አግኝተውት ነው ? ቢሮው ትዕዛዝ አውርዶ ነበር ? ስንል ኃላፊውን ጠይቀናል።

ዶ/ር ዘላለም ፥ “ በዩኒቨርሲቲዎችና በሌሎች ጣቢያቸዎች እንደሚሰጥ ነገር ግን ሌሎች ጣቢያዎች የነበሩት፣ በእነርሱ ላይ ካልሆነ በስተቀር ' ቀርቷል ' ተብሎ የተሰጠ መግለጫ አልነበረም ” ብለዋል።

አክለው፣ “ ለሙከራ ስንሞክርባቸው የነበሩ እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ተማሪዎችና ቤተሰብ ላይ እንግልት እንዳይሆን እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ቀንሰናል ” ያሉት ኃላፊው፣ “ በእርግጠኝነት ሊፈጸሙባቸው ተብሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ የተወሰኑት ላይ ግን ተወስኗል ” ብለዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናው እንደቀረ ያስተላለፈው መልዕክት ነበር ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ደግሞ፣ “ ትምህርት ሚኒስቴር እኮ በገጹ ላይ አስታውቋል እንዳልቀረ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም። በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ተይዘው የነበሩት በተለያዩ ምክንያቶች ተቀንሰዋል ” ብለዋል።

ቢሮዎ ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ ለትምህርት ሚኒስቴር ጻፈው ተብሎ ሲሰራጭ የነበረው ደብዳቤ (ከላይ ተያይዟል) የቢሮ ነው ? ለሚለው ጥያቄ ፥ “አዎ። ትክክል ነው !! ” ብለዋል።

“ አሁን ባልናቸው ጣቢያዎች ማለት ነው። በፊት በ153 ጣቢያዎች ብለን ነበር ይዘን የነበረው አሁን ግን በእርግጠኝነት ይሳካል የተባለበት ቦታ ከላይ የተጠቀሱት ጣቢያዎች ብቻ ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል።

በመሆኑም በተቀመጠው መርሀ ግብር መሠረት ተማሪዎች ከምንም አይነት ውዢምብር ራሳቸውን ጠብቀው ከቢሮውና ከትምህርት ሚኒስቴር በሚወርዱ መመሪያዎች ብቻ ተረጋግተው እንዲፈተኑ አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#EthioTelecom

ኢትዮ ቴሌኮም የ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትን በዛሬው እለት አቅርቧል።

የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ሪፖርቱን በማቅረብ ገለፃ አድርገዋል።

በዚህም ተቋሙ አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢውን ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ21.7% ወይም በ16.7 ቢሊዮን ብር በማሳደግ 93.7 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።

21.79 ቢሊዮን የተጣራ ትርፍ ነው።

የእቅዱን 103.6% ማሳካቱንም አሳውቋል።

ተቋሙ የቴሌኮም ደንበኞቹንቁጥር ከአምና ተመሳሳይ ወቅት በ8.9% በማሳደግ 78.3 ሚሊዮን አድርሶ የእቅዱን 100.4% ማሳካቱን ገልጿል።

ቴሌኮሙ በበጀት አመቱ የቴሌኮም እና የዲጂታል መሰረተልማት አቅምን ለማሳደግ ምን ሰራ ?

- የ4G ኔትወርክ አገልግሎትን ወደ 124 ተጨማሪ ከተሞች እና ወረዳዎች በማስፋፋት በአጠቃላይ 4G ተደራሽ የሆነባቸውን ከተሞች ቁጥር ከ300 ወደ 424 ማሳደጉን ገልጿል።

- በተጨማሪም በ79 የሞባይል ጣቢያዎች ላይ የ5G የኔትወርክ ማስፋፊያ ስራ በማከናወን የ5ጂ ጣቢያዎችን ቁጥር ወደ 189 ማድረስ እንደቻለ ጠቁሟል።

- አዲስ አበባን ጨምሮ 5 የከልል ዋና ከተሞችን የ5G ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ተጨማሪ 4 ከተሞችን የ5G ተጠቃሚ ለማድረግ የትግበራ ስራ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ተብሏል።

የዲጂታል ገንዘብ ዝውውር እና የተቋሙ የሞባይል ገንዘብ ቴሌብር አፈፃፀም ምን ይመስላል ?

- ቴሌኮሙ የቴሌብር ደንበኞቹን ብዛት 47.55 ሚሊዮን በማድረስ የእቅዱን 107.8% ማሳካቱን አሳውቋል።

- የገንዘብ ዝውውርን በቴሌብር ዲጂታላይዝ በማድረግ በበጀት አመቱ 1.81 ትሪሊዮን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ዝውውር በቴሌብር
ተከናውኗል።

- አገልግሎቱ ከተጀመረ (May 11, 2021) ጀምሮ አጠቃላይ በኢኮኖሚው ላይ 2.55 ትሪሊየን የኤሌክትሮኒክ ገንዘብ ማንቀሳቀስ ተችሏል፡፡

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም) ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል። የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት…
#Update (No. 5)

የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ በነበሩበት በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተደጋጋሚ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለታጋቾቹ ምን አዲስ አለ ? ሲል የተማሪ ወላጆችን የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት፣ ደርባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።

ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ወቅት ድረስ ከእገታው ያልተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉ ወላጆች ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አጋቾቹ አሁንም ለአንድ ተማሪ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደጠየቋቸው፣ ያሰባሰቡትን የተወሰነ ገንዘብ ልከው ታጋቾቹን እንዲለቁላቸው ቢማጸኑም ገንዘቡ ካልተሟላ እንደማይለቋቸው ገልጸዋል።

በርካታ ተማሪዎች አሁንም እንደታገቱ መሆናቸውን እንዳረጋገጡ የገለጹት ሁለት የታጋች ቤተሰቦች፣ ጉዳዩ በሚዲያ እየተንሸራሸረ ስለሆነ መንግስት ሰምቷል ፤ ታዲያ ለምን መፍትሄ አይሰጠንም ? ሲሉ ጠይቀዋል።

የታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አካል፣ ትንሽ ታጋቾች ቢለቀቁም አብዛኛዎቹ ገና እንደሆኑ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ የተለዬ መረጃ ግን እንዳልተገኘ አስረድተዋል።

ከትምህርት ሚኒስቴር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረበላቸው ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ አቶ አብዱ ናሲር፣ ስለጉዳዩ ከፍተኛ አመራሮች እንዲጠየቁ ከመናገር ውጪ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በዩኒቨርሲቲው የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት በሰጠው ቃል፣ ታጋቾቹ ወደ ወለጋ መስመር እንደተወሰዱ መስማቱን ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 138 ታጋቾች እንደተለቀቁ መግለጹን ሪፓርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ደግሞ በሸኔ ታግተው የነበሩት 167 ተማሪዎች ናቸው ከነዚህ ውስጥ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀዋል ብሏል።

ይህንን የመረጃና በየሚዲያው " አብዛኛው ተለቀዋል " እየተባለ የሚሰራጨውን መረጃ ተመልክተው ከደቂቃዎች በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት የላኩ የተማሪ ወላጆች በጣም እንደተበሳጩ ገልጸው " ውሸት ባይዘገብስ " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://aa.ministry.et/account#/student-result ላይ በመግባት መመልከት ይችላሉ " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ውጤቱ ዙሪያ ውይይት በማድረግ የማለፊያ ነጥቡን ይፋ…
#AddisAbaba

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል !

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠጡት ቃል ፦

“ የ8ኛ ክፍል ውጤት ዛሬ ተለቋል። የማለፊያ ውጤት ወስነን ቆርጠን ይፋ አድርገናል።

ወንድም ሴትም 50ና ከዚያ በላይ ያመጡ ናቸው ወደ ሚቀጥለው ክፍል የሚያልፉት። የአካል ጉዳተኞች ማለፊያ ነጥብ 45 እና ከዚያ በላይ ነው።

78 በመቶ የሚሆኑት ተፈታኞቻችን አልፈዋል።

የ6ኛ ክፍል ውጤት በቀጣይ ሳምንት ይለቀቃል። ”


የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መመልከቻ : https://aa.ministry.et/account#/student-result
(መለያ ቁጥርና ስም ያስገቡ)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እህታቸው የታገተችባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ከሰጡት ቃል ፦ " በጣም ይገርማል በእውነት፤ እኔ እኮ በእራሳቸው ስልክ (በአጋቾቹ ማለታቸው ነው) ትናንት ጠዋትም ከሰአት በኋላም እራሴ አግኝቻታለሁ በድምፅ፣ ሰዎቹንም አግኝቻቸዋለሁ። ልጆቹ አሁንም እዚያው ነው ያሉት፤ ተፈተዋል ምናም የሚባለው ነገር ውሸት ነው። ማታ ዜና ስንሰማ ነበር። እንዴት እንዲዚህ ያለ ነገር ይሰራል እስኪ…
#Update (No.7)

• “ እኔ 50 ሺህ፣ ጓደኛዬ 30ዐ ሺህ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃዩ ነው ” - ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ

• “ እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል ” - የታጋች ተማሪ ወንድም


ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ከታገቱ 10 ቀናት አስቆጥረዋል።

ስለታጋቾቹ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ገንዘብ ከፍሎ ከእገታው የተለቀቀ ተማሪ እና የታጋች ቤተሰቦችን ስለጉዳዩ ጠይቋል።

አንድ ስሙ እንዲገለጽ ያልፈቀደ ከእገታው የተለቀቀ ተማሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ እኔ 50 ሺህ ፣ ጓደኛዬ 300 ሺ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃሉ ነው ” ብሏል።

ከታጋቾች መካከል 36 የሚሆኑት ከኦሮሚያ  ሲሆኑ 28ቱ በነጻ ሲለቀቁ ሌሎች 9ኙ ግን እዛው እደታገቱ ናቸው ፤ ከአማራ እና ደቡብ የሆኑም እንዳልተለቀቁ ገልጿል።

‘ ታጋቾች ተለቀዋል፣ 7 ታጋቾች ናቸው ያልተለቀቁት ’ የሚባለው ዜና ውሸት መሆኑን ገልጾ፣ ከገርበ ጉራቻ በእግር የ1 ሰዓት የእግር መንገድ ከሚወስድ ጫካ አሁንም ከ60 በላይ ታጋቾች እንዳሉ መመልከቱን ተናግሯል።

የአይን እማኙ፥ “ ያሳለፍኩትን ከባድ መከራ በቃላት አልገልጸውም ” ያለ ሲሆን ታጋቾቹ በምግብ እጦትና በብርድ እየተሰቃዩ በመሆናቸው መንግስትም እንዲደርስላቸው አሳስቧል።

“ ቤተሰቦቼ ድሃ ናቸው ብዬ አልቅሼ ነው የለቀቁኝ ። ጓደኛዬ 300 ሺህ ብር ባይከፍል ግን አይለቁኝም ነበር ” ብሏል።

አንድ የታጋች ወንድም በሰጡት ቃል ደግሞ ፥ “ ' ልጆች ተለቀዋል ' ይባላል ፤ በርካታ ወላጆች ግን ልጆቻቸው በእገታ ላይ ናቸው። ደውለን እየጠየቅን ነው። እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል። ግን ገንዘብ የለንም !! ” ብለዋል።

ሌላኛዋ የታጋች እህት በበኩሏ ፣ ታጋች እህቷ እስከ 3 ቀናት 40ዐ ሺህ ብር ላኪ እንደተባለች፣ ከ10 ሺህ ብር በላይ ግን ማግኘት እንዳልቻለ ገልጻላች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉዳዩ ላይ ምላሽ ለማግኘት ወደ ኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን፣ ሰላምና ጸጥታ ቢሮዎች ያደረገው ሙከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም። 

በተጨማሪም፣ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ አቅርበናል።

የአገልግሎት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ከበደ ደሲሳ ፥ " በጉዳዩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሰጠው ወጪ የተለየ ነገር የለኝም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ፣ ከቀናት በፊት በሰጠው መግለጫ በ ' ሸኔ ቡድን ታግተው ተወሰዱ ' ካላቸው 167 ታጋቾች መካከል የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ መለቀቃቸውን 7 ታጋቾች ብቻ እንደቀሩ አሳውቆ ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሁለት ወራት ከ18 ቀናት ነው መተከል የቆየሁት አንድም ቀን መብራት አልበራም " - ዶክተር መብራቱ አለሙ የኢትዮጵያ ፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሥራ አስፈፃሚ ፣ የቦሮ ዲሞክራሲ ፓርቲ (ቦሮ) የውጪ እና ዓለም አቀፍ ዘርፍ ኃላፊ ፣ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ረዳት ፕሮፌሰር ዶ/ር መብራቱ አለሙ የቦሮ ዲሞክራሲ ፓርቲን ወክለው ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር ቆይታ አድርገዋል። በዚህ ቆይታቸው…
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

• “ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚተገበረው ግን መቼ ነው ? ” - የቡለን ወረዳ ነዋሪዎች

• “ ‘ለምን አልመርጣችሁኝም ’ በማለት በበቀል ህዝብን መጉዳት ተገቢ አይደለም ” - ዶ/ር መብራቱ አለሙ


በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ‘ ለምን ፓርቲውን መረጣችሁ ’ በሚል ሰበብ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ አባላት እና ፓርቲው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

በአካባቢው ከዚህ ቀደም በነበረው የጸጥታ ችግር ሳይካሄድ ቀርቶ የነበረው ምርጫ በቅርቡ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፣ ምርጫውን ያሸነፈው የፓርቲው አባላት ላይ የ ' ቡለን ወረዳ አስተዳደር ' እስራትን ጨምሮ ድብደባ እያደረሰባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

“ እኛ የፈለግነውን የመምረጥ መብት አለን። ቦሮን መረጣችሁ በማለት እንዴት እንግልት ይደርስብናል ? ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚተገበረው ግን መቼ ነው ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

የፓርቲው የውጪና አለም ዓቀፍ ዘርፍ ኃላፊ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ከፍተኛ አመራር ዶ/ር መብራቱ አለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ አመራሮች ከምርጫ በኋላ ‘ለምን ቦዴፓን መርጣችሁ’ በሚል ሰበብ ” የሚከተሉትን ድርጊቶች በአባላቱ ላይ እየፈጸሙ መሆኑን ገልጸዋል።

➡️ ከቀበሌ ሚሊሻ አርሶ አደሮች ትጥቅ ማስፈታት
➡️ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ ግብር መጫን
➡️ የመንግስት ሠራተኞችን ማዋከብና ፣ ማስፈራራት፣ ማሰርና ማዘዋወር
➡️ ነዋሪዎችን ‘በልማት ስራ አልተገኛችሁም’ በማለት በገንዘብ መቅጣት
➡️ መንግስታዊ አገልግሎት መንፈግ ለአብነት የመታወቂያ እድሳት፣ አዲስ የመታወቂያ ጥያቄ አለማስተናገድ፣
➡️ የድጋፍ ደብዳቤ መከልከል ተጀምሯል ሲሉ ድርጊቶቹን አስረድተዋል።

“ ከነበሩት ቦታ ያለአግባብ የተዘዋወሩ ሁለት የግብርና ባለሙያዎች ቅሬታ በጽሑፍ ሲያቀርቡ የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ ወርቀቱን ተቀብሎ ቀዶ ከጣለ በኋላ ባለጉዳዮች እንዲታሰሩ አድርጓል ” ሲሉም ወቅሰዋል።

“ የባለጉዳዮችን አቤቱታ ቀዶ የጣለውን ትተው ባለጉዳዮችን አስረዋል ” ነው ያሉት።

“ ህዝቡ የፈለገውን ፓርቲ የመምረጥ መብት አለው። የፈለገውንም መርጧል ” ያሉት ዶ/ር መብራቱ ፥ “ መንግስት ደግሞ የመርጠውንም ያልመርጠውን እኩል የማገልገል ግዴታ አለበት ” ብለዋል።

“ ‘ ለምን እኔን አልመርጣችሁኝም ’ በማለት በበቀል ህዝብን መጉዳት ተገቢ አይደለም። ይህ አካሄድ መልሶ መንግስትን ይጎዳል። ይህ ድርጊት የወንጀል ተጠያቂነትን ያስከትላል ” ሲሉ አክለዋል።

“ በአጠቃላይ በወረዳው ላይ እየተካሄደ የሚገኘው ህገወጥ ወከባ የማይቆም ከሆነ በወረዳው ግጭት ሊፈጠር ይችላል ” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ቅሬታ ለፈጠረው የመብት ጥሰት ቅሬታ የወረዳውን ምላሽ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች። ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች። ከመግለጫው መካከል ፦ " በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ…
#Update

“ ሃያ (20) ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” - ቤተክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘ በጉልበት ሊወስደው ነው ’ ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል።

ጉዳዩ ከምን ደረሰ ?

ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል ፣ “ 20 ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችን እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” ብላለች።

“ ዛሬ (ሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) ግቢ ውስጥ ገብተው በጉልበት አጥረውታል። መሳሪያ በያዙ ሰዎች እያስጠበቁት ነው ያሉት ” ስትል ገልጻለች።

ይህንን ያሉት አንድ የቤተ ክርስቲያኗ አካል ፣ “ እኛም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩም፣ ለኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችም ደብዳቤ እየላክን ነው ” ብለዋል።

“ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠዋት ነው የላከነው፣ ለአቶ ሽመልስ አብዲሳም ልከናል። ገና ምንም የሰጡት ምላሽ የለም ” ሲሉ አክለዋል።

“ 40 በመቶ ገደማ ይዞታችን ነው ይወሰዳል የተባለው ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “ አሁን ግማሹን አጥረዋል። ለሁለት ግለሰቦች ነው ይሰጣል የተባለው ” ነው ያሉት።

በተጨማሪ ፣ በፍርድ ቤትም እግድ እንዲያወርድላቸው እንደጠየቁ፣ የሚጠብቁት ያስገቡትን ደብዳቤ ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ ገልጸዋል።

“ አስቸኳይ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መጥራት የምናመራ ይሆናል። በሰላማዊ መንገድ ድምፃችንን እናሰማለን። ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የምትቆመው ከሰላም ጎን ነው። የመረበሽ የማስረበሽ ዓላማ የላትም ” ብለዋል።

ቅሬታ የቀረበበት የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ሆኖም በቀጣይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ምላሹን የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
🔈#የነዋሪዎችድምጽ

“ ከሆስፒታሉ ውጪ በ3 እጥፍ ዋጋ መድኃኒት እየገዛን ነው ” - ታካሚዎች

“ የአቅርቦት እጥረት አለ ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል 

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል በመድኃኒት እጥረት ሳቢያ ታካሚዎች ከ3 እጥፍ በላይ በሆነ ዋጋ ከግል መድኃኒት ቤቶች መድኃኒት ለመግዛት እየተገደዱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረሩ።

በርካታ ታካሚዎች ዋጋው ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ህክምናቸውን እያቋረጡ መሆኑን፣ ችግሩ መቀረፍ ሲገባው ተባብሶ እንደቀጠለ አስረድተዋል።

በተለይ እንደ ሴፍትሪያክዞን፣ ዲ40% የመሳሰሉ መድኃኒቶች ከሆስፒታሉ ከጠፉ ወራት እንደተቆጠሩ ተናግረዋል።

“ ከሆስፒታል ውጪ በ3 እጥፍ ዋጋ መድኃኒት እየገዛን ነው” ያሉት ታካሚዎቹ፣ የላብራቶሪ ምርመራዎች ‘በተደጋጋሚ ተበላሽተዋል’ እየተባለ የምርመራ ከሆስፒታል ውጪ ለማሰራት እየተገደዱ መሆኑን ተናግረዋል።

ችግሩ ለምን ተፈጠረ ? ሲል ቲክቫህ የጠየቃቸው የጎንደር ዩኒቨርሲቲው ሆስፒታል ቺፍ ክሊኒካል ዳይሬክተር ዶ/ር መኳንንት መለሰ፣ “ አሁን ባለው የበጀት Ristriction፣ የፋይናንስ እጥረት ምክንያት አንዳንድ መድኃኒቶች አይኖሩም ” የሚል ምላሽ ተሰጥተዋል።

“ በወቅታዊ ችግር አሁን በወቅታዊ ችግር መንገድ ዝግ ነው። መድኃኒት ቀጥታ ከአዲስ አበባ በደጀን በኩል ነበር የሚመጣው አሁን በአፋር ክልል ነው የሚመጣው። የአቅርቦት እጥረት አለ ” ብለዋል።

➡️ ዲ 40% የተሰኘው መድኃኒት ያልነበረው “ትራውማ ካዡዋሊቲ” በዝቶ ስለነበር እንደሆነ፣
➡️ ይሁን እንጂ አሁን የመድኃኒት አቅርቦቱ እንዳለ፣ 
➡️ የላብራቶሪ ማሽኑ በመብራት መቆራረጥ ሳቢያ በመቆሙ ለሳምንት የተመላላሽ ታካሚዎች ህክምና ተቋርጦ እንደነበርና ማሽኑም እየተጠገነ መሆኑን አስረድተዋል። 

ሆስፒታሉ በቀን ከ3,000 በላይ፣ በአጠቃላይ ደግሞ 13 ሚሊዮን ለሚሆኑ ሰዎች የተለያዩ የህክምና አገልሎቶች እንደሚሰጥ ተገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
⚠️ እባካችሁ ተጠንቅቃችሁ አሽከርክሩ ⚠️

ዛሬም በትራፊክ አደጋ የበርከታ ሰዎች ህይወት አልፏል።

የዛሬው አደጋ በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ዲባንድቤ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው የደረሰው።

በዚህም የ9 ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ አልፏል።

ከሟቾች ባሻገር በ4 ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሰ ሲሆን ተጎጂዎቹም ወደ ዲላ ሪፈሪያል ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ገብተዋል።

የጮርሶ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፤  የአደጋው መንስኤ ታርጋ ቁጥሩ ኢት ኮድ (03)19178 የሆነ ሲኖትራክ፣ ከዲላ ወደ ሞያሌ ሲጓዝ ከነበረው ዶልፈን ሚኒንባስ ኮድ 0322503፣ በተመሳሳይ ከዲላ ወደ ከቡለሆራ ሲጓዝ ከነበረ FSR መኪና ታርጋ ቁጥር AA ከድ 03 74596 ጋር በመጋጨቱ መሆኑን አሳውቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🔈#የመምህራንድምጽ

“ የ3 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም ” - የአፋር ክልል መምህራን 

“ ያልተመገበ መምህር ክፍል ግባ ቢባልም ሊገባ አይችልም ” - የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበር


በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ የሚገኙ መምህራን ደመወዝ እንዳልተከፈላቸው፣ በዚህም ቤተሰብ ራሱ ማስተዳደር እንዳልቻሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

መምህራኑ፣ “ የ3 ወራት ደመወዝ አልተከፈለንም። ታዲያ ቤተሰብስ እንዴት እናስተዳድር? ” ሲሉ በአንክሮ ጠይቀዋል።

ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው የሚመለከታቸውን አካላት እንደጠየቁ፣ ሆኖም መፍትሄ እንደሌለ፣ በዚህም ችግር ላይ እንደሆኑ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ መምህራን ማኀበርም ቅሬታው አግባብ መሆኑን ገልጾ፣ “ እንደውም እስከ ርዕሰ መስተዳደሩ ቢሮ ድረስ ጋውናቸውን ለብሰው ሂደው በክልሉ ልዩ ኃይል ነው የተመለሱት ” ብሏል።

የማኀበሩ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አበበ ለቲክቫህ በሰጡት ቃል፣ “ ቅሬታቸው የቆዬ ነው። የ3 ወራት ደመወዝ ተባለ እንጂ ከ2012 ዓ/ም ጀምሮ የትምህርት ማሻሻያ፣ የደረጃ እድገት የማይሰጥበት አካባቢ አለ ” ብለዋል።

“ አሁን ላይ ደግሞ ደመወዝ ይቆረጣል። ለድርጅት ተብሎ ሁሉ ደመወዝ የሚቆረጥበት አካባቢ አለ ” ሲሉ ተናግረዋል።

መምህራኑ የ3 ወራት ደመወዝ እንደተቆረጠባቸው፣ በዚህም የክልሉ መምህራን ማኀበር፣ የክልሉ ትምህርት ቢሮ የሚመለከታቸውን አካላት ለማነጋገር  ጥረት እንዳደረጉ የገለጹት አቶ ሽመልስ፣ “ ታች ያለው አመራር የላይኛውን የሚሰማ አይደለም ” ብለዋል።

“ መምህራን ግን ለከፋ የመልካም አስተዳደር ችግር እየተጋለጡ ናቸው፤ እዚያ አካባቢም (ሰመራ) በጣም የከፋ ችግር ነው ያለው ” ሲሉ አክለዋል።

ታዲያ ማኀበሩ ለቅሬታው ምን ምላሽ አገኘ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ “ ቀደም ብለን ለርዕሰ መስተዳደሩ አቶ አወል አርባ ደብዳቤ ፅፈንላቸዋል። እሳቸውም ለታችኛው መዋቅር ችግሮቹ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ብለው በደብዳቤ አሳውቀዋል ” ብለዋል።

ሆኖም ከታች ያሉት አመራሮች ጉልበተኛ እንደሆኑ ነው አቶ ሽመልስ ያስረዱት።

“ አንድ መምህር ደመወዙ እየተቆረጠበት፣ ጉልበቱ ሌላ ጋ ከሆነ፣ ያልተመገበ መምህር ክፍል ውስጥ ግባ ቢባልም ሊገባ አይችልም። በጉልበት ቢገባ እንኳ ያስተምራል ወይ ? የሚለው ሌላ ጥያቄ ነው ” ብለዋል።

ይህ ድርጊት መማር ማስተማሩ ላይ በቀጣይ ከፍተኛ ጉዳት እንዳያስከትል ከፍተኛ ስጋት እንዳላቸው ገልጸው፣ “ ምስቅልቅሉ የወጣ አሰራር ነው ያለው ” ሲሉ ወቅሰዋል።

“ የታችኛው አመራር ለትምህርት የማያስብ፣ ለጊዜው ለፓለቲካ ተቆጥሮ የማሰጠውን አጀንዳ ብቻ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ፣ መደማመጥ የሌለበት፣ ለትውልድ የማያስብ አመራር እያየሁ ነው ” ነው ያሉት።

በአማራ ክልል ያለው የመምህራን ቅሬታ በቀጣይ ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ወላጆች ልጆቻችሁን ጠብቁ !!

በክረምት የእረፍት ጊዜ ወላጆች ለልጆቻቸው በቂ ጥበቃ እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል አሳሰበ።

የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ፣ ዛሬ (ሐምሌ 11 ቀን 2016 ዓ.ም) ከቀኑ 8 ሰዓት ገደማ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ወረገኑ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ውሃ ባቆረ ጉድጓድ የገባ ታዳጊ ህይወቱ ማለፉን ገልጸዋል።

" ውሃ ባቆረ ጉድጓድ ዋና ለመዋኘት የገባ የ13 ዓመት ታዳጊ ህይወቱ አልፏል" ያሉት አቶ ንጋቱ፣ "የኮሚሽኑ ጠላቂ ዋናተኞች የታዳጊውን አስከሬን አውጥተው ለፖሊስ አስረክበዋል " ብለዋል።

" በአዲስ አበባ ታዳጊዎችና ወጣቶች በቂ የዋና ችሎታ ሳይኖራቸው ለዋና በሚል ውሃ ባቆሩ ጉድጓዶች እየገቡ ህይወታቸውን ያጣሉ " ነው ያሉት።

አሁን ትምህርት ቤቶች ዝግ ስለሆኑ ታዳጊዎችና ወጣቶች ለጨዋታ በሚል ድርጊቱን ስለሚፈጽሙ ወላጆች በቂ ጥበቃ እንዲያደርጉላቸው አሳስበዋል።

ኮሚሽኑ አደጋውን ለመከላከል የሚያሰችሉ በሚል በተደጋጋሚ የሚያስተላልፋቸውን የጥንቃቄ መልዕክቶች ህብረተሰቡ፣ በተለይ ወላጆች፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች  እንዲተገብሩ ጠይቋል።

ችግሩ እየተደጋገመ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን፣ በዚህ አደጋ ምን ያህል ታዳጊዎች ህይወታቸውን እንዳጡ በቀጣይ የሚዳሰስ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (No.7) • “ እኔ 50 ሺህ፣ ጓደኛዬ 30ዐ ሺህ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃዩ ነው ” - ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ • “ እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል ” - የታጋች ተማሪ ወንድም ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ከታገቱ 10 ቀናት አስቆጥረዋል። ስለታጋቾቹ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ? ቲክቫህ…
#Update (No.8)

" ባነር አሰርተን ልመና ወጥተናል ገንዘብ ግን እየተገኘ አይደለም " - የታጋች ተማሪ ቤተሰብ

ትምህርት አጠናቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች “ ገብረ ጉራቻ ” የሚባል ቦታ ሲደርሱ መታገታቸው አይዘነጋም።

ተማሪዎቹ የታገቱት ሰኔ 26/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ብዛታቸው በትክክል ባይታወቅም ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከእገታው ያመለጡ ተማሪዎች በሁለት ታታ አውቶብስ የነበሩ መሆናቸውን በወቅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ከታጋቾቹ መካከል አንዳንዶቹ ከፍተኛ ብር ከፍለው መለቀቃቸውን መግለጻቸውም ይታወሳል።

የታጋቾቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የታጋቾቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የታጋች ቤተሰቦቸ፣ ልጆቻቸው ባለመለቀቃቸው ጭንቀት ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቃሏን ለቲክቫህ የሰጠች አንድ የታጋች እህት አጋቾቹ የጠየቁትን ግማሽ ሚሊዮን ብር ካልተላከላቸው ታጋቾቹን ‘ አንለቅም ’ ማለታቸውን ገልጻ፣ “ ባነር አሰርተን ልመና ወጥተናል ገንዘብ ግን እየተገኘ አይደለም ” ብላለች።

በተጨማሪም እህቷ ፤ ያሉት ታጋች ተማሪዎች ምግብ በወቅቱ እንደማያገኙና ልብስም ስለሌላቸው በብርድ እየተሰቃዩ እንደሆነ እንደገለጸችላት ተናግራለች።

" አጋቾቹ 700 ሺህ ጠይቀውናል " ያለ ሌላኛው የአንዲት ታጋች ተማሪ ወንድም፣ ታጋቿ በስቃይ ውስጥ እንዳለች ቤተሰብ ገንዘቡን ለመላክ አቅም እንዳላገኘ ገልጿል።

" ቤተሰቡ በከባድ ሀዘን ላይ ነው። በተወለድንበት ሀገር ለዛውም ንጹሐን ተማሪ ታግተው ሲሰቃዩ መንግስት ምን እየሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።

ታጋቾቹን ለማስቀቅ ምን እየሰራ ነው ? ሲል ቲክቫህ የጠየቀው የኦሮሚያ ክልል ስላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከዚህ ቀደም የሰጠው መግለጫ እንዳለ ከመጥቀስ ውጪ በጸጥታ ቢሮው በኩል ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።

ሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማትም ለጉዳዩ ምላሽ ለመስጠተ ፈቃደኛ አልሆኑም።

የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ከዚህ ቀደም በሰጡት መግለጫ፣ በ 'ሸኔ ቡድን ታግተው ተወሰዱ' ካላቸው 167 ታጋቾች መካከል የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀው፣ 7 ታጋቾች ብቻ እንደቀሩ አሳውቆ ነበር።

አንድ ከቀናት በፊት ገንዘብ ከፍሎ ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ ግን እርሱ ከነበረበት የእገታ ቦታ ብቻ ከ60 በላይ ታጋቾች እንዳሉ ለቲክቫህ ተናግሮ ነበር።

ሌላኛዋ በእገታው ላይ ያለች ተማሪ ባለችበት ጫካ ፣ በርካታ ታጋች ተማሪዎች እንዳሉ እንደተናገረች ቤተሰቦቿ ለቲክቫህ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia