TIKVAH-ETHIOPIA
1.38M subscribers
54.6K photos
1.35K videos
197 files
3.61K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የሕዝብ_በዓላት_እና_የበዓላት_አከባበር_ረቂቅ_አዋጅ_.pdf
#Update

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የሕዝብ በዓላትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የወጣውን ረቂቅ አዋጅ #አጽድቋል

ረቂቅ አዋጁ የተወሰኑ ማስተካከያዎች እንደተደረጉበት ተመላክቷል።

አዋጁ በ1 ድምፀ ተቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ " አዋጅ ቁጥር 1334/2016 " ሆኖ ነው የጸደቀው።

የጸደቀው አዋጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሕዝብ በዓላት እና የበዓላትን አከባበር የሚመለከት ሲሆን ፤ ክልሎች በራሳቸው ነባራዊ ሁኔታ ህግ አውጥተው በክልል ደረጃ የሚከበሩ አዋጆችን አከባበር መወሰን ይችላሉ ተብሏል።

ይህ የሚመለከተው እንደ ኢሬቻ፣ ጊፋታ፣ ጨምባላላ፣ አሸንዳ ፣ ሻደይ ፣ አሸንድዬ ፣ ...ሌሎችንም ሲሆን ክልሎች በራሳቸው አዋጆችን አውጥተው አከባበሩን መወሰን እንደሚችሉ ተመላክቷል።

https://t.me/tikvahethiopia/87926

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፓይለቱ ወደ ኃላ እንዲመለስ ተነግሮት ነበር ፤ ከዛ በኃላ ግን አውሮፕላኑ የት እንደገባ አልታወቀም " - የማላዊ ፕሬዜዳንት የተሰወረው የማላዊ አውሮፕላን አልተገኘም። በአውሮፕላኑ ውስጥ ከም/ፕሬዜዳንቱ ጋር የቀድሞው ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ ባለቤት / የቀድሞ ቀዳማዊ እመቤት ሻኒል ዲዚምቢሪ እንደሚገኙበት ተነግሯል። አንዳንድ ሚዲያዎች እና የቀድሞ የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ " በጣም ድቅድቅ…
#Update

የማላዊ ምክትል ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ ባለስልጣናትን ይዞ ሲጓዝ የነበረውን ከራዳር እይታ የተሰወረው አውሮፕላን #ስብርባሪ ተገኘ።

አውሮፕላኑ መከስከሱ ተረጋግጧል።

ምንም የተረፈ ሰው የለም።

በአውሮፕላኑ ውስጥ ምክትል ፕሬዜዳንቱ ሳውለስ ቺሊማን እና የቀድሞው ፕሬዜዳንት ባኪሊ ሙሊዚ ባለቤት / የቀድሞ ቀዳማዊ እመቤት ሻኒል ዲዚምቢሪን ጨምሮ 10 ሰዎች ነበሩ።

ሁሉም መሞታቸው ነው የተሰማው።

Photo Credit - Hopewell

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የታገተችው ታዳጊ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ታግታ ከተወሰደች በኃላ ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር የተጠየቀባት የታዳጊዋ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ጉዳይ እስከአሁን እንቆቅልሽ ሆኖ ቀጥሏል። መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ ልዩ ቦታው " ዓዲ ማሕለኻ " ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታግታ የተሰወረችው ታዳጊ ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ከታገተች ዛሬ ግንቦት 10/2016 ዓ.ም 60 ቀናት አስቆጥራለች። ታጋች…
#Update

ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኘች።

ለ91 ቀናት ታግታ የተሰወረችው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ ተገድላ ተገኝታለች።

ለወላጆችዋ ዛሬ መርዶ ተነግሯቸዋል።

የአስከሬን የአሸኛነት ስነ-ሰርዓት ዛሬ በአቡነ አረጋዊ ቤተክርስትያን ዓድዋ እንደሚፈፀም ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በተማሪ ማህሌት ተኽላይ ግድያ ዙሪያ ፓሊስ የሚሰጠው መረጃ ተከታትለን የምናቀርብ ይሆናል።

በተማሪ ማህሌት ተኽላይ እገታና ስወራ ጉደይ የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ለወራት ተከታታይ መረጃ ሲያቀርብ እንደነበር አይዘነጋም።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ማህሌት ተኽላይ ! መጋቢት 10 ቀን 2016 ዓ.ም በዓድዋ ከተማ  " ዓዲ ማሕለኻ " ከሚባል ስፍራ ነው ታግታ የተሰወረችው። የታገተችው ቋንቋ ወደምትማርበት ትምህርት ቤት ስትሄድ ነው። ባጃጅ ይዘው በመጡ ሰዎች ነበር የታገተችው። ማህሌት ተኽላይ ታግታ ከተወሰደች በኃላ አጋቾች ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ ወላጅ አባቷ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረው ነበር። የዓድዋ ከተማ ፓሊስም ፥ ከሳምንታት…
#Update #Adwa

ከ3 ወር በላይ ታግታ አድራሻዋ ጠፍቶ ዛሬ በግፍ መገደለዋ የተረጋገጠው ተማሪ ማህሌት ተኽላይ አጋቾችዋ ገድለው እንደቀበሯት ማመናቸውን ፓሊስ አስታወቀ።

የትግራይ ማእከላይ ዞን ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ሃላፊ ኮማንደር ፀጋይ ኣስፍሃ ዛሬ ለ104.4 የመቐለ ኤፍኤም በስልክ በሰጡት ቃል ፥ በእገታው እና ግድያው የተጠረጠሩ መያዛቸውን ገልጸዋል።

ግለሰቦቹ ለፓሊስ በሰጡት ቃል ተማሪ ማህሌትን ገድለው በዓድዋ የፓንአፍሪካ ዩኒቨርስቲ ሊገነባበት የመሰረተ ደንጋይ የተጣለበት ቦታ መቅበራቸውን ቦታው ድረስ በመምራት አሳይተዋል ፤ አምነዋል ብለዋል። 

ተጠርጣሪዎቹ  ማህሌትን እንዴት እንዳገቷት ፣ አግተው ወዴት እንደወሰዱዋት ፣ እንዴት ገድለው እንደቀበርዋትና አስከሬንዋ የተቀበረበት ቦታ ጭምር በዝርዝር ለፓሊስ ማሰየታቸውን ኮማንደሩ በሰጡት መረጃ አረጋግጠዋል።

የተማሪ ማህሌት ተኽላይ አስከሬን ከተቀበረበት ጉድጓድ የማውጣት ስነ-ሰርዓት በመከናወን ላይ መሆኑ የገለፁት ኮማንደር ፀጋይ ፤ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ ተጨማሪ ምርመራ ይደረግበታል ብለዋል።

#TikvahEthiopiaMekelle

@tikvahethiopia
@TikvahEthiopiaTigrigna
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የተማሪ ማህሌት ተኽላይ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ።

የማህሌት አስክሬን አጋቾች ከቀበሩበት ወጥቶ የአስከሬን ምርመራ ተጠናቅቆ ዛሬ ከቀኑ 9:00 ሰዓት በዓድዋ አቡነ አረጋዊ ቤተክርስትያን የቀብር ስነ-ሰርዓት ተፈጽሟል።

የቀብር ስነ-ስርዓቱ የክልል ፣ የዞን እና የሃይማኖት መሪዎች እንዲሁም በርካታ የዓድዋ ነዋሪዎች ተገኝተው ነበር።

ተማሪ ማህሌት ተኽላይ በዓድዋ  ከተማ " ዓዲ ማሐለኻ " የሚባል ቦታ ታግታ ከተወሰደች በኃላ አጋቾች ለማስለቀቂያ 3 ሚሊዮን ብር ቤተሰቦቿን ጠይቀው ነበር።

የት እንደ ደረሰች ላለፉት 91 ቀናት ሳይታወቅ ቆይቶ ማህሌት ተገድላ ፤ ተቀብራ አስክሬኗ ዛሬ ተገኝቷል።

ከእገታው እና ግድያው ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎች ተይዘው ገድለው የቀበሩበትን ቦታ ለፖሊስ መርተው በማሳያት አስክሬኗ እንዲወጣ እና ምርመራ እንዲደረግ ተደርጓል።

የትግራይ ማዕከላይ ዞን ወንጀል ምርመራ ኃላፊ ኮማንደር ፀጋይ ኣስፍሃ ፥ አጋቾቹ የጠየቁትን ብር ቤተሰቦቿ አቅም ስለሌላቸው መክፈል ባለመቻላቸው ማህሌትን ገድለው እንደቀበሯት ገልጸዋል።

#Adwa #Tigray

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ስራ #ደመወዝ ° " ያለስራና ደመወዝ በመቆየታችን ከፍተኛ ችግር ላይ ወድቀናል " - የመንግስት ሰራተኞች ° " ጉዳዩን እናውቀዋለን እየተወያየንበት ነው ፥ በአጭር ቀናት መፍትሄ ይሰጣቸዋል " - የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባለስልጣን የደቡብ ክልል መበተኑን ተከትሎ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመደቡ የ " ውሀ ስራዎች ኮንስትራክሽን ሰራተኞች " ከስራ እና ከደመወዝ ውጭ ሆነው ወራት እንደተቆጠሩ…
#Update

የሰራተኞቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

" ...  እንዴት ምላሽ ተከልክሎት ለሀገር የሚጠቅም ሰራተኛ ጎዳና ሲወጣ ዝም ይባላል " - ሰራተኞች

የደቡብ ክልል መበቱኑን ተከትሎ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተመደቡ የውሀ ስራዎች ኮንስትራክሽን ድርጅት ሰራተኞች " እስካሁን ደሞዝ ስላልተከፈለን ጎዳና ላይ ልንወጣ ነው " ማለታቸውን መረጃ ሰጥተናችሁ ነበር።

በወቅቱ ይህን ችግር አስመልክተን ጥያቄ ያነሳንላቸዉ የርዕሰ መስተዳድሩ ልዩ አማካሪ አቶ ንጉሴ አስረስ ፤ " ችግሩን እናዉቀዋለን " በማለት በጥቂት ቀናት መፍትሄ እንደሚገኝና ሰራተኞችንም እንደሚያናግሩ ገልጸውልን ነበር።

ይሁንና ለወራት ደሞዝ ያልተከፈላቸዉና አሁንም ከስራ ውጭ እንደሆኑ የነገሩን ሰራተኞቹ ዛሬም በባሰ ችግር ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው እስካሁን ያናገራቸው አካል እንደሌለ ነግረውናል።

ሰራተኞቹ በተደጋጋሚ ጊዜ ውሀ ልማት ኮንስትራክሽን ቢሮን ለማነጋገር እንደጣሩ ነገር ግን ሊያናግራቸው እንዳልፈለገ ጠቀሙዋል።

" ለምን ሊያነጋግረን እንዳልፈለገ ግልጽ አልሆነልንም ፤ እንዴት ለሀገር የሚጠቅም ሰራተኛ ጎዳና ሲወጣ ዝም ይባላል "  በማለት ቅሬታቸውን በድጋሜ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ያነጋገርናቸው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ውሀ ልማት ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ ኢንጅነር ሻምበል አብዬ  ፤ " እስካሁን ድረስ ሰራተኛዉ ስራ ያልጀመረዉ እጃችን ላይ ፕሮጀክት ስላልነበረ ነው ፤ አሁን ላይ ግን ፕሮጀክቶች እየተፈራረምን በመሆኑ በቅርቡ ወደስራ ይገባሉ " ብለዋል።

" ወደ ስራ ቦታቸዉ ሆሳዕና ከተማ ጥሪ ከተደረገላቸዉ በኋላ ' የትራንስፖርት ክፍያ አልተከፈለንም ' ለተባለዉ የኛ ድርጅት ከሲቪል ሰርቪስ የተለየ በመሆኑ ነው " ያሉት ኃላፊው " አሁን ላይ ያለው የሰራተኛዉ ችግር ይገባናል አይደለም ሰራተኞቻችን ሆነዉ ይቅርና ማንም ኢትዮጵያዊ እንዲህ አይነት ችግር ላይ ሲሆን መፍትሄ መፈለግ ይገባል " ብለዋል።

" አሁን ላይ እየሄድንበት ያለነዉ የመፍትሄ መንገድ አለ " በማለት በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ነገር ይኖራል ሲሉ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን እስከመጨርሻ ይከታተላል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የፐርፐዝ ብላክ አካውንቶች ታገዱ። የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አካውንቶች በመንግስት ታግደዋል። ድርጅቱ አካውንት ሲታገድብኝ ይህ በዓመት ለ3ኛ ጊዜ ነው ብሏል። የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጰያ ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ዶክተር ፍስሐ እሸቱ ፥ የድርጅቱ አካውንቶች ለምን እንደታገዱ ምክንያቱን እንደማያውቁት ገልጸዋል። በአመት ውስጥ ምክንያቱ  ሳይታወቅ ለሶስት ጊዜ አካውንታቸው መታገዱን አመልክተዋል። ስለ…
#Update

" መጀመሪያ 250 ሚሊዮን ብር ከዛ 200 ሚሊዮን ብር ጉቦ ጠየቁን " - ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ

የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሀገር ጥለው አሜሪካ መግባታቸው ተሰምቷል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ ዛሬ አሜሪካ ሆነው መግለጫ ሰጥተዋል።

" ከሀገረ የወጣሁት በግፈኞች ምክንያት ተገድጄ ነው " ብለዋል።

ባልፈው የግላቸውን ጨምሮ የድርጅቱ የባንክ አካውንቶች በሙሉ በመንግስት መታገዱን መግለጻቸው ይታወሳል።

ይህን በተመለከተ በሰጡት ቃል፥ " አካውንቶቹ የታገዱት ጽንፈኛ የፋኖ ታጣቂ ኃይሎችን በመርዳት፣መሳሪያ በማዘዋወር በሙስና ወንጀል፣ በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር በሚል እና በሌሎች ነው  " ብለዋል።

" እኛ ምርመራ ይደረግ እያልን ነበር በኃላ እውነቱ ጫና የሚደረገው ብላክሜል ለማድረግ እና አስፈራርቶ የሚፈልጉትን ነገር ለመቀበል ነበር " ሲሉ ተደምጠዋል።

ዶ/ር ፍስሃ መጀመሪያ 250 ሚሊዮን ብር ከዛ ግን 200 ሚሊዮን ብር ጉቦ ክፈሉ እንደተባሉ ተናግረዋል።

ለዚህም " የስልክ እና ሌሎች ማስረጃዎች አሉን " ብለዋል።

" መቼ እና እንዴት ገንዘቡ እንደሚከፈል ፣ በምን ሁኔታ እንደሚከፈል ጭምር ፣ መቼ ገንዘቡ እንደሚወጣ ጭምር ነው ትዕዛዝ የተሰጠን " ሲሉ ገልጸዋል።

" ሰዎቹ ልክ ቼኩን እንደወሰዱ በማግስቱ ሁሉም እግድ እንደሚነሳ ቃል ገብተው ነበር " ብለዋል። 

" ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋርም እናገናኛችኋለን ስብሰባም ትቀመጣላችሁ ብለው ነበር " ሲሉ ጠቁመዋል።

የተጠየቀው ጉቦ የማይሰጥ/ የማይከፈል ከሆነ ግን ከማሰር እስከ መግደል የሚደርስ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ዛቻና ማስፈራሪያ እንደተሰነዘረባቸው ገልጸዋል።

አጠቃላይ በጠራራ ጸሀይ እንዝረፋችሁ የሚል " የማፊያ " ስራ ነው የተሰራው ሲሉ አክለዋል።

" ሆን ተብሎ በደረሰብኝ ጫና፣ ማስፈራራትና ዛቻ እኔን አጥቅቶ ገንዘብ ለማግኘት ፣ ድርጅቱንም ለመቆጠር በሚሰራው ስራ ሀገር ለቄቄ ወጥቻለሁ " ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈጻሚው ፤ " ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይሄ ሁሉ ሲደረግ ያውቃሉ ብዬ አላስብም ፤ በእሳቸው የአመራር ዘመን እንደዚህ አይነት በአፍሪካ ሆነ በዓለም የሚዘገንን የዝርፊያና ሙስና ስራ ሲሰራ ዝም ብለው ያያሉ ብዬ አላምንም " ሲሉ ተደምጠዋል።

" እኛ ከቢዝነስ ውጭ ምንም የፖለቲካ ፍላጎት የለንም ፤ ' ፅንፈኞችን ይደግፋሉ ፣ መሳሪያ ያዘዋውራሉ ' የሚለው ክስ በሬ ወለደ ነው ከኛ ጋር አይገናኝም " ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩም ያለው ችግር በሰላም ይፈታ ዘምድ መፍትሄ እንዲፈልጉላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

" ከአሁን በኃላ ከማንም ጋር መስራት አንፈልግም ፤ በሚኒስትር ደረጃ ያሉትን አነጋግረናል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ውጭ  መፍትሄ የሚሰጠን የለም " ብለዋል።

" ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ለደህንነታችን ዋስትና ይስጡንና ስራችንን በሰላም እንስራ " ብለዋል።

" ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ውጭ ችግራችንን የሚፈታልን የለም ፤ ከሳቸው ውጭ ያየነው ነገር ቢኖር ከፍተኛ ሙስና የማፊያ ሰራ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከእሳቸው ውጭ ባሉት የበታች ሰዎች ምንም እምነት የለንም " ብለዋል።

ከዚህ ባለፈ ሽምግልና እንደሚሞከር ጠቁመው አስፈላጊ ከሆነም የአሜሪካ ኤምባሲ ጣልቃ ገብቶ እንዲያግባባ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።

ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ላይ  " ሰዎቹ " እያሉ የጠሯቸው (200 ሚሊዮን ብር ጉቦ የጠየቋቸው) እነማን እንደሆኑ ፣ የስልጣን ደረጃቸው ፣ የተቋም ኃላፊነታቸው ምን እንደሆነ በግልጽ #ስማቸውን_ጠቅሰው አልተናግሩም።

" በደረሰብኝ የእስርና ግድያ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ሀገር ለቅቄ ወጥቻለሁ " ያሉት የኢትዮጵያዊ አሜሪካዊው ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ  ከሀገር ሲወጡ የገጠማቸው ነገር ስለመኖሩ የሰጡት ቃል የለም።

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Kenya ጎረቤት ኬንያ ታቃውሞ እየናጣት ነው። መንግሥት በታክስ ላይ ጭማሪ ሊያደርግ ማቀዱን ተከትሎ በተለይም ወጣቱ ለተቃውሞ አደባባይ ወጥቷል። ከወጣቶቹ ሰልፍ ጋራ በተያያዘ ትላንት አንድ ሰው #ተገድሏል፡፡ ግድያው የተፈጸመው በፖሊስ በተተኮሰ ጥይት ነው ተብሏል። ዛሬም በናይሮቢና የተለያዩ ከተሞች ተቃውሞ ሲካሄድ ውሏል። ተቃዋሚዎቹ በሚቀጥለው ሳምንት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚካሔድ የተቃውሞ…
#Update

በነገው ዕለት በኬንያ ምድር አንቀጥቅጥ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሏል።

ይህ ሰልፍ የሀገሪቱ መንግስት ያረቀቀውን የፋይናንስ ረቂቅ አዋጅን የሚቃወም ነው።

የተቃውሞ ሰልፉ አይቀሬ እንደሆነ ያወቀው የሀገሪቱ መንግሥትም በአገር ውስጥ ጉዳይ እና ብሔራዊ አስተዳደር ካቢኔ ሚኒስትር በኩል ሰልፉ በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።

ዛሬ በሰጠው ይፋዊ መግለጫ ማንኛውም ተቃዋሚ የመንግስትም ሆነ የግል ንብረትን እንዳያወድም ወይም እንዲያወድም እንደማይፈቀድለት አፅንዖት ሰጥቷል።

የተቃውሞ ሰልፈኛው የሚሄድበትን አቅጣጫ ቀደም ብሎ ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ እጅባና ጥበቃ እንዲደረግለት ማድረግ አለበት ተብሏል።

ሰልፈኞቹ ሰልፉን በፍጹም ሰላማዊ መንገድ ማድረግ እንዳለባቸው ያሳሰበው የሀገሪቱ መንግስት ትጥቅ ታጥቆ ሰልፍ መውጣት እርምጃ ሊያስወስድ እንደሚችል አስጠንቅቋል።

ተቃዋሚ ሰልፈኞች ፦
- የውሃ፣
- የኃይል አቅርቦት
- ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶች የሚሰጡት ወሳኝ ቦታዎች ላይ እንዳያገኙ ተከልክለዋል።

በተጨማሪ በህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ጣልቃ መግባት እንደማይችሉ ተገልጿል።

በምንም መልኩ በየብስ ፣ በባቡር፣ በባህር ፣ በአየር ትራንስፖርት ላይ ጣልቃ መግባት እንደ ሌለባቸው ምንም ይሁን ምን ለሀገሪቱ ህግ የበላይነት ሁሉም ሰው ሊታዘዝ እንደሚገባ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ሁሉም ተቃዋሚዎች ሰልፉን ሁከት እና ብጥብጥን በማያበረታታ መንገድ እንዲያደርጉ እንዲሁም ደግሞ ፦
° ሰልፉን መሳተፍ የማይፈልጉ / ተቃውሞ ማድረግ የማይፈልጉ
° የፖሊስ አባላትን ፣
° የመንግስት አካላትን ማስፈራራት ፣ ማስጨነቅ እና መተንኮስ እንደሌለባቸው ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

#Kenya

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኬንያ ናይሮቢ፣ ሞምባሳን ጨምሮ በተለያዩ የኬንያ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች መደረግ ጀምረዋል። በወጣቶች መሪነት እየተካሄዱ ባሉት በነዚህ ሰልፎች ላይ መንግሥት ተጨማሪ ታክስ ለመጣል ያረቀቀውን የፋይናንስ ረቂቅ አዋጅ ሙሉ በሙሉ እንዲተወው እየተጠየቀበት ነው። መንግሥት በረቂቁ ላይ አንዳንድ ማሻሻያ አደረጋለሁ ቢልም ተቃዋሚዎች ግን " የምን አንዳንድ ነው ? ሙሉ ረቂቁን ተወው " የሚል አቋም እንደያዙ…
#Update

በኬንያ ተቃውሞ ሰዎች ተገደሉ።

የፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ መንግሥት ያረቀቀውን አዲስ የታክስ ሕግ የተቃወሙ ኬንያውያን የአገሪቱን ፓርላማ ቅጥር ጊቢ ጥሰው ገብተዋል።

ፖሊስ በከፍተኛ ቁጥር የወጡ ተቃዋሚ ወጣቶችን ለመበተን ጥይት እና አስቀሽ ጭስ ተኩሷል።

እስካሁን ድረስ ቢያንስ 5 ሰዎች በጥይት የተመቱ ሲሆን ሁለቱ ሕይወታቸው አልፏል።

ከጥቂት ሰዓታት በፊት የአገሪቱ ም/ ቤት አባላት ከፍተኛ የሆነ ተቃውሞ ገጥሞት የነበረውንና በተለያዩ ምርት እና አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ ታክስ የሚጥለውን ረቂቅ ሕግ አጽደቀዋል።

" አዲሱ የቀረጥ ሕግ ኑሯችንን ያስወድድብናል " ሲሉ የቆዩት ኬንያውያን ወጣቶች ከአገሪቱ ፓርላማ ፊት ለፊት የተቃውሞ ድምጻቸውን ለማሰማት በከፍተኛ ቁጥር ወጥተዋል።

ከፖሊስ ቁጥጥር አቅም በላይ የሆኑ አብዛኛዎቹ ወጣቶች የሆኑ ተቃዋሚዎች የፓርላማውን በር ጥሰው ገብተዋል።

በመቶዎች የሚቆጠሩ የፓርላማ አባላት ከምክር ቤቱ ምድር ቤት ለመደበቅ ሲሯሯጡም ተይተዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ፥ ተቃዋሚዎች አንደኛውን የፓርላማውን ክፍል በእሳት ማያያዛቸውን ቢቢሲ እና የኬንያ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ ከታገቱ ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም ሰባት ወራት ይሆናቸዋል። እንደቀላል ነገር በወጡበት ቀሩ ” - የታጋች ባለቤት ከ6 ወራት በፊት ወደ ባቱ (ዝዋይ) ለስራ ጉዳይ እየተጓዙ በታጣቂዎች ታገቱ ከተባሉ 6 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች መካከል 3ቱ ቢለቀቁም 3ቱ ግን እንዳልተለቀቁ ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም የሚችለውን ሁሉ…
#Update

“ በታጣቂዎች ከታገቱ 9 ወራት አለፉ፤ ያሉበትን እንኳ አናውቅም። ወደ ማን እንጩህ ? ”- የታጋች ባለቤት

መስከረም 19 ቀን 2016 ዓ.ም በታጣቂዎች ታግተው የተወሰዱ 3 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች ደብዛቸው እንደጠፋ መሆኑን የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

ወደባቱ ለስራ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት በታጣቂዎቸ ታገቱ የተባሉት ሠራተኞቹ ያልተለቀቁት አጋቾቹ ገንዘብ ጠይቀው ከ2.8 ሚሊዮን ብር ከተላከ በኋላ እንደሆነ የታጋች ቤተሰቦች ከዚህ ቀደምም ገልጸው ነበር።

አሁንስ ምን አዲስ ነገር አለ ? 

- አቶ ልዑል አስፋወሰን
- አቶ ሰይፉ እንዳለ
- አቶ አብዩ ደገፋው የተባሉ ሠራተኞች በህይወት ይኑሩ አይኑሩ አይታወቅም።

ትላንት ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ 2 የታጋች ቤተሰቦች ስለ 3ቱም ታጋቾች ምንም የሰሙት ፍንጭ እንኳ እንደሌለ ገልጸዋል።

አንዷ የታጋች ባለቤት “ በታጣቂዎች ከታገቱ 9 ወራት አለፉ ፤ ያሉበትን እንኳ አናውቅም። ወደ ማን እንጩህ ? ” ሲሉ ሀዘን ያጀበው ጥያቄ አንስተዋል።

የሰው ልጅ ለ9 ወራት ያህል ያለበት እንኳን አለማወቅ ከባድ ሀዘን መሆኑን ፤ ኤሌክትሪክ ኃይልን በቅርቡ ቢጠይቁም ካቅሙ በላይ እንደሆነበት መግለጹን ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ ያቀረበለት የኤሌክትሪክ ኃይል ጉዳዩ ከአቅሙ በላይ እንደሆነበት መግለጹ ይታወቃል።

#TikvahEthiopaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

በቦሊቪያ የተሞከረው መፈንቅለ መንግሥት ከሸፈ።

ሙከራው ሰዓታትን እንኳን አልቆየም።

የፕሬዜዳንቱን ቤተመንግሥት በኃይል ሰብረው ገብተው የወረሩት ወታደሮች ከቤተመንግሥቱ አካባቢ መሄዳቸው ተሰምቷል።

ፕሬዜዳንት ሉዊስ አርሴ ፤ ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡትን የሠራዊቱን አዛዥ ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ከስልጣን አውርደው በሌላ ተክተዋል።

አዲሱ የሠራዊት አዛዥ ጆሴ ዊልሶን ሳንቼዝ ሁሉም ቤተመንግሥት የመጡ ወታደሮች ወደ የመጡበት ወታደራዊ ሰፈር /ክፍል እንዲመለሱ አዘዋል።

ይህን ተከትሎም ወታደሮቹ ከስፋራው ለቀው ሄደዋል።

ፕሬዝዳንት አርሴ አዲስ የአየር ኃይል አዛዥ እና የባህር ኃይል አዛዥም ሾመዋል።

ፕሬዝዳንቱ ወታደሮች ቤተመንግሥቱን ሰብረው መግባታቸውን እና መውረራቸውን ተከትሎ ህዝቡ በነቂስ ተደራጅቶ ወደ ጎዳና እንዲወጣና የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ እንቅስቃሴውን እንዲያከሽፍ እና ዴሞክራሲውን እንዲያስጠብቅ ጥሪ አቅርበው ነበር።

በዚህም በርካቶች የሀገሪቱን ባንዲራ ይዘው በቤተመንግሥቱ አካባቢ ተሰብሰበው ነበር።

ፕሬዝዳንቱ ሙከራው መክሸፉን ተከትሎ ህዝቡን  በእጅጉ አመስግነዋል።

ወታደሮችን እየመሩ ቤተመንግሥት የገቡት ጄነራል ጁዋን ጆሴ ዙኒጋን ምንም እንኳን የመፈንቅለ መንግሥቱ መሪ ነኝ ብለው በግልጽ ባይናገሩም ፥ " ጥፋት ይቁም ፤ ሀገራችንን ወደ ድህነት መምራት ይቁም፣ ሠራዊታችንን ማዋረድ ይቁም " ሲሉ ተደምጠው ነበር።

ጦሩ ዴሞክራሲን ወደነበረበት ለመመለስ እና የፖለቲካ እስረኞችን ነጻ ለማድረግ እንደሚጥርም ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ዙኒጋን አዲስ የሚኒስትሮች ካቢኔ እንደሚቋቋም ከአሁን በኃላ ሀገሪቱ አሁን ባለው መንገድ እንደማትቀጥልም ገልጻው ነበር።

ጄነራል ዙኒጋን ከሽፏል ከተባለው የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በኃላ ቀጣይ ዕጣፋንታቸውን እና በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለጊዜው አልታወቀም።

ቦሊቪያ 🇧🇴 ፦ በደቡብ አሜሪካ የምትገኝ ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖሩባት ሀገር ናት።

#Bolivia
#failedcoup

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ወታደሮችን እየመሩ የቦሊቪያው ፕሬዚዳንት አርሴ ቤተ መንግስትን በኃይል ሰብረው በመግባትና በመውረር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያደረጉት ጄነራል ሁዋን ሆዜ ዙኒጋ በሀገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው እስር ቤት ገብተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት እና ምክትል ፕሬዜዳንት በጋራ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ። ስራ መልቀቂያውን ያስገቡት ፤ " በፍትህ እና የዳኝነት ሰርዓቱ ለውጥ ለማምጣት ያሰብናቸው ፣ ያቀድናቸው የጀመርናቸው ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች ለማሳካት የሚያስችል ሁኔታ ማግኘት ስላልቻልን ነው " ብለዋል። ሰኞ ሰኔ 17/2016 ዓ.ም የተፃፈው የስራ መልቀቅያ ደብዳቤ በበርካታ የማህበራዊ…
#Update

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጥያቄያችን ለመመለስ ቃል ስለገባ የስራ መልቅቅያ ጥያቄያችን ትተነዋል " - የትግራይ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ያስገቡትን የመልቀቂያ ደብዳቤ እንደተውት አሳወቁ።

ፕሬዜዳንቱና ምክትል ፕሬዜዳንቱ ይፋ ባደረጉት መግለጫ ፤ ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም ያቀረቡት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ተከትሎ ሰኔ 18 /2016 ዓ.ም ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ውይይት ማደረጋቸውን ገልጸዋል።

በዚ ውይይት ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ለመመለስ ቃል በመገባቱ ስራ የመልቀቅ ጥያቄያቸውን እንደተውት አሳውቀዋል።

ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ምን እንደሆኑ በግልፅ ያላብራሩ ሲሆን ከላይ እስከ ታች የሚገኘው የፍርድ ቤት አካል ስራውን ተረጋግቶ እንዲሰራ መልእክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዜዳንቱና  ምክትል ፕሬዜዳንቱ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸው ተከትሎ የወረዳና የዞን ፍርድ ቤቶች ስራ የማቆም አድማ መምታት ጀምረው ነበር

ከክልሉ ፕሬዜዳንት ከተደረገው ውይይት በኃላ ችሎቶች ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በአካል ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

ከመቐለ ውጪ በመላው ክልል ያሉ ፍርድ ቤቶች መደበኛ አገልግሎት መስጠት መቀጠላቸው የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የፕሮቶኮል ሹም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa በሀዋሳ ከተማ የስፓርት ውርርድ ( #ቤቲንግ ) ቤቶች እየታሸጉ / እየተዘጉ ይገኛሉ። ይህ ተከትሎ የስፖርት ውርርድ ቤት ባለቤቶች " እንዴት የንግድ ፈቃድ እያለን ይዘጋብናል ? " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል። እነዚህ የስፖርት ውርርድ ቤቶች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክኒያቶች ተዘግተው የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ተከፍተው ነበር። አሁን ላይ ተመልሰው መዘጋት/መታሸግ መጀመራቸው…
#Update

" የስፖርት ውርርድ ቤቶችን የመዝጋትና የመክፈት አሰራር አድሎአዊነት የተንጸባረቀበት ነው " - ቅሬታ አቅራቢዎች

" የተከፈቱ ቤቶች ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያመጡ ናቸው " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ ያሉ የስፖርት ውርርድ ቤቶች  " ህጋዊ አይደሉም ፣ በብዛት  የተከፈቱበት አካባቢም የትምህርትና የመኖሪያ ሰፈር ነው " በሚል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቢዘጉም ከቀናት ቆይታ በኋላ ግን የተወሰኑት ተከፍተዉ ስራ ጀምረዋል።

ይህንን ተከትሎ ፥
- ለምን ሁሉም በህግና ስርአት እየሰራ እና ግብርም እየከፈለ እያለ በከፊል ተከፍቶ በከፊል ይዘጋል ?
- ቤቶቹን የመዝጋትና የመክፈት ስራን የሚሰራዉ የከተማው ፖሊስ አሰራሩ አድሏዊነት የታየበት ነው፤
- ገንዘብ ሰጥተው የሚያስከፍቱ ሰዎችም እንዳሉ እየተሰማን ነው ሲሉ የስፖርት ውርርድ ቤታቸው የተዘጋባቸዉ ግለሰቦች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የከተማዉ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ፥ አሁን ላይ ተከፍተዉ ወደስራ የተመለሱት ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያቀረቡ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

በተጨማሪም " ለሀገር ፈጽሞ ጥቅም የማይሰጠዉ የቨርቹዋል አሰራር አሁንም እንደተከለከለ ነው። ካሁን በፊት እንደህግ ያስቀመጥነዉ የመኖሪያ ቤትና የትምህርት ቤቶች ዙሪያ የተጣለዉ ክልከላ ዛሬም ቀጥሏል " ብለዋል።

ከዚህ ውጭ አከፋፈቱን በተመለከተ የሚነዛዉ ስም ማጥፋት አግባብ አለመሆኑን ገልጸዉ ማንኛዉም አካል ህጋዊ ሆኖ ከመጣ ድርጅቱን ማስከፈት እንደሚችል ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና እና የሪሚዲያል ማጠቃለያ ፈተና ውጤቶች መቼ ይፋ ይደረጋሉ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና እና የዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና መቼ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል። የትምህርት ሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ፥ የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ውጤት ከሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ…
#Update

የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኳል።

የተማሪዎቹ ውጤት ዛሬ ለተቋማቱ መላኩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል።

በዚህም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የዘንድሮው የመውጫ ፈተና ለ57 የመንግሥት እና ለ124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ244 የቅድመ ምረቃ መርሐግብሮች መሰጠቱ ይታወቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቴፒ #አሽከርካሪዎች ° “ ከቴፒ ቡና ጭነን ለመውጣት ተከልክለን ከቆምን ወር ሊሞላን ነው ” - አሽከርካሪዎች ° “ ክልል ኮሚቴ አቋቁቁሞ ነገሩን እያጣራ ነው ”- ቡናና ሻይ ባለስልጣን የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይንቀሳቀሱ በመከልላቸው ያለምንም መፍትሄ ከሦስት ሳምንታት በላይ ለመቆም እንደተገደዱ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል። “ ለሥራ የምንወጣው ቤተሰቦቻችንንም ለማስተዳደር…
#Update

“ አሁንም ድረስ ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ ” - አሽከርካሪዎች 

“ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” - ቡናና ሻይ ባለስልጣን

ከቴፒ የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይወጡ ከዚህ ቀደም ተከልክለዋል ከተባሉት 24 ተሽከርካሪዎች መካከል 3ቱ አሁንም እንዳልተለቀቁ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ አንድ አሽከርካሪ፣ “ አሁንም ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ። ደቡብ ምዕራብ ቦንጋ ከተማ በቡናና ሻይ ባለስልጣን ግቢ ውስጥ አቁመዋቸዋል ” ብለዋል።

ሌሎችም አሽከርካሪዎች፣ በበኩላቸው ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተው፣ ተሽከርካሪዎቹ ቦንጋ የቆሙት ቴፒ ከወጡ በኋላ ቡናው ' Commercial ነው ’ ተብሎ መሆኑን አስረድተዋል።

የተለቀቁት ተሽከርካሪዎችም ቢሆኑ የተለቀቁት ከአንድ ወር መጉላላት በኋላ በመሆኑ በኑሮ ላይ ከባድ ጉዳት እንደገጠማቸው አስረድተው፣ “መጨረሻ ላይ ቡናው Local ነው ተብሎ ተለቀቅን፣ በዚህ ጉዳይ ሲጀመር መጠየቅ ያለበት ሹፌር አልነበረም” ብለዋል።

ከአሽከርካሪዎቹ በኩል ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ጥያቄ ያቀረበላቸው የቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻፊ ዑመር፣ “ ስንመረምር 3ቱ መኪና Local ብለው የጫኑት የExport ቡና ሆነ ” ብለዋል።

“ ስለዚህ የExport ቡና መሸጥ ህገ ወጥ ነው። አገርን ዶላር ማሳጣት ነው። 3ቱ መኪና እዛው ቆመው ነው ያሉት በፓሊስ እጅ ነው ” ሲሉ ተናግተዋል።

አቶ ሻፊ “ አሁን ላይ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” ብለው “ እንደዚህ ያደረጉ አካላትም ለህግ እንዲቀርቡ ለደቡብ ምዕራብ ደብዳቤ ፅፈናል ” ሲሉ አክለዋል። 

ትክክለኛ የችግሩ ምንጭ ማነው ? በማለት ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አቶ ሻፊ፣ “በሁሉም Side አለ” ብለዋል።

“ ላኪዎቹ የ Local አስመስለው Exportable ቡና ሲገዙ በጥሩ ዋጋ ስለሚሸጡ። ለአገር አያስቡም። አቅራቢው ደግሞ ቡናን በአፈርና ውሃ እያሸ ወደ Local እንዲገባ ስለሚያደርግ ችግር አለበት” ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው፣ “አሽከርካሪዎቹም ቢሆኑ እያወቁ ነው የተሻለ ዋጋ ስለሚከፈላቸው ቴፒ ሂደው የሚጭኑት። ሲጀመር የExports ቡና ማከማቻ፣ Localን ወደ Export የሚለየው አዲስ አበባ ነው። ቴፒ የሚያስሄዳቸው ነገር የለም” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል። ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው…
#Update

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ ከትላንትና ጀምሮ በጦርነት ምክንያት ከቤትን ንብረታቸው ተፈናቅለው እስካሁን በመጠለያ የነበሩ የሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማፀብሪ ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ መጀመሩን አሳውቋል።

ከማይ ዓይኒ፣ ከማይ አንበሳ፣ ከመድኃኔዓለም እና ውሕደት ከተባሉ ቀበሌዎች የተፈናቀሉ ከአንድ ሺሕ አምስት መቶ በላይ ተፈናቃዮች ትላንት ተመልሰዋል።

ዛሬም ማይ ፀብሪን ጨምሮ የፀለምቲ ወረዳ ስድስት ቀበሌዎች ተፈናቃዮች ተመልሰዋል።

አንዳንድ ቃላቸውን ለቪኦኤ የሰጡ ተመላሾች ህዝቡ " እንኳን ደህንና መጣችሁ ! " ብሎ በመልካም ሁኔታ እንደተቀበላቸው ፤ ታጣቂዎች ግን እስካሁን እንዳልወጡ፣ ትጥቅም እንዳላወረዱ ይህ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸዋል።

ይህ አካባቢ ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልላዊ መንግሥት ስር የጠለምት ወረዳ አስተዳደር ተብሎ ነበር።

የጠለምት አማራ ወሰንና ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ አለቃ አለነ አሰጋ ፤ " የጠለምት ወረዳ አስተዳደር የጸጥታ መዋቅር፣ ከዛሬ 3 ቀናት በፊት በግዳጅ ሥራ እንዲያቆም ተደርጓል " ብለዋል።

አለቃ አለነ ፥ በሥራ ላይ የቆየው ፖሊስ እና የጸጥታ መዋቅሩ ወደ ዓዲኣርቃይ አካባቢ መንቀሳቀሳቸውን ገልጸዋል።

እርሳቸው ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ግን ከአካባቢው አለመልቀቃቸውን ጠቁመዋል።

በአካባቢው የጸጥታ ስጋት መኖሩን ጠቁመው፣ መንግሥትም ይህንኑ ተገንዝቦ፣ ነዋሪው ኅብረተሰብ የራሱን የጸጥታ መዋቅር እንዲዘረጋ ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል፡፡

አለቃ አለነ የጠለምት የወሰንና የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ እንደመሆናቸው በአካባቢው ላይ ያላቸውን የወሰን እና የማንነት ጥያቄውን በቦታው ላይ እያሉ ማቅረባቸውን እንደሚቀጠሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ፌደራል መንግሥት የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው የትግራይ እና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈናቃዮች ወደቦታቸው ከተመለሱ በኃላ ከነዋሪው ህብረተሰብ ጋራ በመሆን የጋራ አስተዳደር ከአቋቋሙ በኋላ የሚነሳው ጥያቄ በሕዝበ ውሳኔ / ሪፈረንደም ምላሽ ቢያገኝ የተሻለ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍርዱ ለሚዲያ 16 ዓመት ከተባለ በኃላ ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዳለ ሰምቻለሁ " - ጸጋ በላቸው " ጉዳዩ ለቢሮዉም ሆነ ለኔ አዲስ ነው " - ወ/ሮ ወይንሸት ብርሀኑ በሀዋሳ ከተማ የዳሽን ባንክ ሰራተኛ ከሆነችዉ ጸጋ በላቸዉ ጋር በተያያዘ በጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሶ  የነበረው ኮንስታብል የኃላመብራት ወ/ማርያም " ለብዙዎች አስተማሪ ይሆናል " በተባለ መልኩ የ16 አመት ጽኑ እስራት…
#Update

" ውሳኔዉ መስተካከሉ አስደስቶኛል ጥንካሬም ሆኖኛል " - ጸጋ በላቸዉ

" የይግባኝ ዉሳኔዉን ተከትሎ ፍርዱ ወደ 10  መቀነሱ ልክ አልነበረም " - የክልሉ ዋና ዐቃቤ ህግ


• ግለሰቡ በ14 ዓመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጣ ተፈርዷል።

በሀዋሳ ፥ የዳሽን ባንክ ሰራተኛዋን ጸጋ በላቸዉ ላይ የጠለፋ ወንጀል የፈጸመዉ የጸጥታ አባሉ ምክትል አስር አለቃ የኋላመብራቱ  ወልደማርያም የጠየቀው ይግባኝ ተቀባይነት አግኝቶ ፍርዱ ከ16 አመት ወደ 10 መውረዱ ተሰምቶ ነበር።

በወቅቱ በዉሳኔዉ ያዘነችዉ ተበዳይ ጸጋ በላቸዉ ቅሬታ ውስጥ መግባቷን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ ያሳለፈዉ ውሳኔ አግባብ አለመሆኑንና ቅጣቱ በጣም እንዳሳመማት ገልጻ  ቅሬታ ማቅረቧን መዘገባችን ይታወሳል።

ይህን የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሳኔ በመቃወም ይግባኝ የጠየቀዉ የክልሉ ዐቃቤ ህግ ቅጣቱ መውረዱ ከህግ አንጻር አግባብ አይደለም ብሎ በመከራከር የቅጣት ማቅለያውን ውድቅ በማድረግ ቅጣቱ ተስተካክሎ የ14 አመት ከ6 ወር ውሳኔ ተሰጥቷል።

በዚህ የፍርድ ሂደት አስተያየቷን በመልእክት ያጋራችን ወይዘሪት ጸጋ በላቸዉ በፍርዱ መስተካከል  ደስታ እንደተሰማትና ይህም  ጥንካሬ  እንደሚሰጣት ገልጻልናለች።

" እንደኔ አይነት ጉዳት የደረሰባችሁ እህቶች ሁሉ ወደህግ በመሄድ መጠየቅን አትፍሩ " የምትለው ጸጋ ፥ ከመጀመሪያውም በህግ ላይ እምነት እንደነበራት ተናግራለች።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ኃላፊው አቶ ማቶ ማሩ ፥ " ምንም እንኳን ሚዲያዎች ለዚህ ኬዝ የሰጡት ትኩረት ጉዳዩን ታዋቂ ቢያደርገውም ክልሉ ለሴት ልጅ ጥቃት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ በርካታ ጠንካራ ውሳኔዎች ተላልፈዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይህ የጸጋ በላቸዉ ኬዝ ማህበረሰቡን ያስተምራል ለተጎጅዋም ፍትህ ይሰጣል ብለን ስንከታተለዉ የነበረ ጉዳይ ከመሆኑ በላይ ድርጊቱን የፈጸመዉ ግለሰብ ማህበረሰብ ይጠብቃል ተብሎ ኃላፊነት የተሰጠዉ በመሆኑ ትኩረት ሰጥተነው ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ማቶ ከወራት በፊት የተሰጠውን የይግባኝ ውሳኔ ህጋዊ ድጋፍ የለውም ብሎ በመቃወም የክልሉ ዐቃቤ ህግ ፍርዱ እንዲስተካከል የጣረው ለዚህ ነበር  ብለዋል።

ቅጣቱ ከ10 ወደ 14 አመት መስተካከሉን ገልጸው " እንደክልል በዚህ አመት ብቻ ከ256 በላይ ሴቶችንና ህጻናትን የተመለከተ ኬዝ በትኩረት ይዘን እየሰራንበት ነው በተወሰኑት ላይም አስተማሪና  ጠንካራ ውሳኔዎች እየተሰጡ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12:00 በፌዴራል ፖሊስ " #ለጥያቄ_ይፈለጋሉ " በሚል ከቤታቸው ተወስደው መታሠራቸውን ቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ዘግቧል። ቀደም ብሎ ፥ የሰንበት ት/ ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን…
#Update

መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር ተፈቱ።

የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር መለቀቃቸውን የማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ዋና ሥራ አስኪያጁ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ለእስር የተዳረጉት።

ከሁለት ወራት በኋላ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016  ዓ.ም  ከእስር  መለቀቃቸውን  ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ተችሏል።

#MahibereKidusanTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DireDawa በድሬዳዋ ከተማ " ሰልባጅ ተራ / አሸዋ " ከጥዋት አንስቶ እስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ያልተቻለ ከባድ የእሳት አደጋ ደርሷል። አደጋው ጥዋት 1:45 የተነሳ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ለመቆጣጠር ማስቸገሩን ድሬ ቲቪ የሶማልኛ ቋንቋ ክፍል ዘግቧል። በቃጠሎ እስካሁን በሰዎች ሕይወት ላይ የደረሰ የሞት አደጋ ባይኖርም ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱ ግን ተጠቁሟል። አሁንም እሳቱን…
#Update #DireDawa

በድሬዳዋ ከተማ አሸዋ የገበያ ስፍራ የተከሰተው እሳት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

በተለምዶ ' አሸዋ ' በመባል በሚጠራው የገበያ ስፍራ ዛሬ ጠዋት ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ፥ በርካታ የመሸጫ ሱቆችና ማሽላ ተራ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በስፍራው ተገኝተው ሁኔታውን ተመልክተዋል።

የአደጋውን መንስኤና የጉዳት መጠን በምርመራ በማጣራት ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

የእሳት አደጋው ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ ከፍተኛ ርብርብ ላደረጉ ነዋሪዎች የጸጥታ ኃይል ምስጋና አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከድሬ ቴሌቪዥን ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia