TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
55K photos
1.37K videos
199 files
3.67K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም) ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል። የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት…
#Update (No. 5)

የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ በነበሩበት በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተደጋጋሚ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለታጋቾቹ ምን አዲስ አለ ? ሲል የተማሪ ወላጆችን የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት፣ ደርባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።

ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ወቅት ድረስ ከእገታው ያልተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉ ወላጆች ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አጋቾቹ አሁንም ለአንድ ተማሪ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደጠየቋቸው፣ ያሰባሰቡትን የተወሰነ ገንዘብ ልከው ታጋቾቹን እንዲለቁላቸው ቢማጸኑም ገንዘቡ ካልተሟላ እንደማይለቋቸው ገልጸዋል።

በርካታ ተማሪዎች አሁንም እንደታገቱ መሆናቸውን እንዳረጋገጡ የገለጹት ሁለት የታጋች ቤተሰቦች፣ ጉዳዩ በሚዲያ እየተንሸራሸረ ስለሆነ መንግስት ሰምቷል ፤ ታዲያ ለምን መፍትሄ አይሰጠንም ? ሲሉ ጠይቀዋል።

የታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አካል፣ ትንሽ ታጋቾች ቢለቀቁም አብዛኛዎቹ ገና እንደሆኑ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ የተለዬ መረጃ ግን እንዳልተገኘ አስረድተዋል።

ከትምህርት ሚኒስቴር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረበላቸው ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ አቶ አብዱ ናሲር፣ ስለጉዳዩ ከፍተኛ አመራሮች እንዲጠየቁ ከመናገር ውጪ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በዩኒቨርሲቲው የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት በሰጠው ቃል፣ ታጋቾቹ ወደ ወለጋ መስመር እንደተወሰዱ መስማቱን ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 138 ታጋቾች እንደተለቀቁ መግለጹን ሪፓርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ደግሞ በሸኔ ታግተው የነበሩት 167 ተማሪዎች ናቸው ከነዚህ ውስጥ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀዋል ብሏል።

ይህንን የመረጃና በየሚዲያው " አብዛኛው ተለቀዋል " እየተባለ የሚሰራጨውን መረጃ ተመልክተው ከደቂቃዎች በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት የላኩ የተማሪ ወላጆች በጣም እንደተበሳጩ ገልጸው " ውሸት ባይዘገብስ " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (No. 5) የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ በነበሩበት በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተደጋጋሚ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር። ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለታጋቾቹ ምን አዲስ አለ ? ሲል የተማሪ ወላጆችን የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት፣ ደርባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል። ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት…
#Update

እህታቸው የታገተችባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ከሰጡት ቃል ፦

" በጣም ይገርማል በእውነት፤ እኔ እኮ በእራሳቸው ስልክ (በአጋቾቹ ማለታቸው ነው) ትናንት ጠዋትም ከሰአት በኋላም እራሴ አግኝቻታለሁ በድምፅ፣ ሰዎቹንም አግኝቻቸዋለሁ። ልጆቹ አሁንም እዚያው ነው ያሉት፤ ተፈተዋል ምናም የሚባለው ነገር ውሸት ነው። ማታ ዜና ስንሰማ ነበር። እንዴት እንዲዚህ ያለ ነገር ይሰራል እስኪ ? " ብለዋል።

ከቀናት በፊት እጅግ በርካታ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጨርሰው ወደ ቤት ሲመለሱ በታጣቂዎች መታገታቸው ይታወቃል።

ትላንትና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል እስከ ትላንት ድረስ አብዛኛዎቹ ታጋቾች እንዳልተለቀቁ ፤ ትንሽ ታጋቾች ግን እንደተለቀቁ አሳውቀዋል።

በተለያዩ ሚዲያዎች " በርካታ ታጋቾች ተለቀዋል " የሚለውን ዜና የሰሙ የታጋች ቤተሰቦች በድርጊቱ ተበሳጭተዋል፤ አዝነዋል። ለምን ውሸት ይዘገባል ? ሲሉም ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Africa #Kenya " በሙስና የተዘፈቀውን ካቢኔዎትን ይበትኑ ! " - የኬንያ አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ምክር ቤት ምንም እንኳን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጁን ቢሰርዙም ተቃውሞው ቀጥሏል። የኬንያ አብያተ ክርስትያናት ፕሬዜዳንቱ ካቢያናቸውን እንዲበትኑ ጠይቀዋል። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና በርከታ ኬንያውያን ሩቶ በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና እንዲያጸዱ ጥሪ እያቀረቡ…
#Kenya #Update

ሩቶ ካቢኔያቸውን በተኑ።

ለሳምንታት በህዝብ ተቃውሞ ስትናጥ የከረመችው ኬንያ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ የካቢኔ ሚኒስትሮቻቸውን በተኑ።

ሩቶ ዛሬ ነው ይህን እርምጃ የወሰዱት።

የፕሬዜዳንቱ እርምጃ በመላው ሀገሪቱ ለተነሳው የፀረ መንግሥት ተቃውሞ እንደምላሽ ነው የተወሰደው።

ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ፥ የካቢኔያቸው ተቀዳሚ ዋና ጸሐፊ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ እንዲሁም ምክትል ፕሬዝደንት ራጋቲ ጋቻጉ ሲቀሩ ሌሎቹን ሚኒስትሮቻቸውን በሙሉ ማሰናበታቸውን ተናግረዋል።

ፕሬዝደንቱ እርምጃውን የወሰዱት የሕዝባቸውን ድምፅ በመስማት መሆኑን ተናግረዋል።

#DW
#CitizenTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈 #የሕዝብድምጽ " ይኸው በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ በዋናው ከተማ አሶሳ እና በተለያዩ ወረዳዎች መብራት ከጠፋ ወደ 1 ወር እየተጠጋ ነው። መቼ  ነው ችግሩ የሚፈታው ? ማነው የሚነግረን ? ምንም የሰማነው ነገር የለም። ለበርካታ ቀናት ጨለማ ውስጥ ቁጭ ብለናል። ከዛሬ ነገ መፍትሄ ይሰጠናል ብለን እየጠበቅን ነው። ተሰቃየን የሚመለከታችሁ አካላት ስለፈጠራችሁ መፍትሄ ስጡን !! ህዝቡ ጨለማ ውስጥ ነው…
#Update

ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አግኝቷል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ላለፉት 17 ቀናት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ እንደነበር ገልጿል።

ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በሚገቡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይም ተደጋጋሚ ስርቆት ስለሚፈፀም የተቋረጠውን ኃይል መልሶ የማገናኘት ሥራውን ፈታኝ አድርጎት እንደነበር አስታውቋል።

ለቀናት መስመሩን ለማገናኘት ጥረት ሲደረግ ቆይቶ ዛሬ ተሳክቷል።

ከቀኑ 9:05 ሰዓት ጀምሮ አካባቢዎቹ ኤሌክትሪክ አግኝተዋል።

" በአንድ አካባቢ የሚፈፀም የኃይል መሰረተ ልማት ስርቆት ተፅዕኖው ሰፊ ነው " ያለው መ/ቤቱ " በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የኃይል መቋረጥ በግልፅ የታየው ይኸው ነው " ብሏል።

በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ህብረተሰቡ እና የሚመለከታቸው የመስተዳድር አካላት ለመሰረተ ልማቱ ጥበቃ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

#EEP

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update እህታቸው የታገተችባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ከሰጡት ቃል ፦ " በጣም ይገርማል በእውነት፤ እኔ እኮ በእራሳቸው ስልክ (በአጋቾቹ ማለታቸው ነው) ትናንት ጠዋትም ከሰአት በኋላም እራሴ አግኝቻታለሁ በድምፅ፣ ሰዎቹንም አግኝቻቸዋለሁ። ልጆቹ አሁንም እዚያው ነው ያሉት፤ ተፈተዋል ምናም የሚባለው ነገር ውሸት ነው። ማታ ዜና ስንሰማ ነበር። እንዴት እንዲዚህ ያለ ነገር ይሰራል እስኪ…
#Update (No.7)

• “ እኔ 50 ሺህ፣ ጓደኛዬ 30ዐ ሺህ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃዩ ነው ” - ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ

• “ እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል ” - የታጋች ተማሪ ወንድም


ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ከታገቱ 10 ቀናት አስቆጥረዋል።

ስለታጋቾቹ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ገንዘብ ከፍሎ ከእገታው የተለቀቀ ተማሪ እና የታጋች ቤተሰቦችን ስለጉዳዩ ጠይቋል።

አንድ ስሙ እንዲገለጽ ያልፈቀደ ከእገታው የተለቀቀ ተማሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል፣ “ እኔ 50 ሺህ ፣ ጓደኛዬ 300 ሺ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃሉ ነው ” ብሏል።

ከታጋቾች መካከል 36 የሚሆኑት ከኦሮሚያ  ሲሆኑ 28ቱ በነጻ ሲለቀቁ ሌሎች 9ኙ ግን እዛው እደታገቱ ናቸው ፤ ከአማራ እና ደቡብ የሆኑም እንዳልተለቀቁ ገልጿል።

‘ ታጋቾች ተለቀዋል፣ 7 ታጋቾች ናቸው ያልተለቀቁት ’ የሚባለው ዜና ውሸት መሆኑን ገልጾ፣ ከገርበ ጉራቻ በእግር የ1 ሰዓት የእግር መንገድ ከሚወስድ ጫካ አሁንም ከ60 በላይ ታጋቾች እንዳሉ መመልከቱን ተናግሯል።

የአይን እማኙ፥ “ ያሳለፍኩትን ከባድ መከራ በቃላት አልገልጸውም ” ያለ ሲሆን ታጋቾቹ በምግብ እጦትና በብርድ እየተሰቃዩ በመሆናቸው መንግስትም እንዲደርስላቸው አሳስቧል።

“ ቤተሰቦቼ ድሃ ናቸው ብዬ አልቅሼ ነው የለቀቁኝ ። ጓደኛዬ 300 ሺህ ብር ባይከፍል ግን አይለቁኝም ነበር ” ብሏል።

አንድ የታጋች ወንድም በሰጡት ቃል ደግሞ ፥ “ ' ልጆች ተለቀዋል ' ይባላል ፤ በርካታ ወላጆች ግን ልጆቻቸው በእገታ ላይ ናቸው። ደውለን እየጠየቅን ነው። እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል። ግን ገንዘብ የለንም !! ” ብለዋል።

ሌላኛዋ የታጋች እህት በበኩሏ ፣ ታጋች እህቷ እስከ 3 ቀናት 40ዐ ሺህ ብር ላኪ እንደተባለች፣ ከ10 ሺህ ብር በላይ ግን ማግኘት እንዳልቻለ ገልጻላች።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚሁ ጉዳዩ ላይ ምላሽ ለማግኘት ወደ ኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን፣ ሰላምና ጸጥታ ቢሮዎች ያደረገው ሙከራ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ምላሻቸውን ማካተት አልተቻለም። 

በተጨማሪም፣ የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ ምን እየተሰራ እንደሆነ ጥያቄ አቅርበናል።

የአገልግሎት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ከበደ ደሲሳ ፥ " በጉዳዩ ላይ የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከሰጠው ወጪ የተለየ ነገር የለኝም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ቢሮ ፣ ከቀናት በፊት በሰጠው መግለጫ በ ' ሸኔ ቡድን ታግተው ተወሰዱ ' ካላቸው 167 ታጋቾች መካከል የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ መለቀቃቸውን 7 ታጋቾች ብቻ እንደቀሩ አሳውቆ ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የኢትዮጵያ_ቃለ_ሕይወት_ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታ ላይ በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት እየተወሰደ ነው ያለችው ሕገወጥ እርምጃ እንዲቆም የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ጥሪ አቅርባለች። ቤተክርስቲያኗ በዛሬው ዕለት ስለጉዳዩ ሰፋ ያለ ዝርዝር መግለጫ ልካልናለች። ከመግለጫው መካከል ፦ " በቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ እየተካሄደ…
#Update

“ ሃያ (20) ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” - ቤተክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘ በጉልበት ሊወስደው ነው ’ ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል።

ጉዳዩ ከምን ደረሰ ?

ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው ቃል ፣ “ 20 ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችን እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” ብላለች።

“ ዛሬ (ሰኞ ሐምሌ 8 ቀን 2016 ዓ/ም) ግቢ ውስጥ ገብተው በጉልበት አጥረውታል። መሳሪያ በያዙ ሰዎች እያስጠበቁት ነው ያሉት ” ስትል ገልጻለች።

ይህንን ያሉት አንድ የቤተ ክርስቲያኗ አካል ፣ “ እኛም ዛሬ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩም፣ ለኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ አመራሮችም ደብዳቤ እየላክን ነው ” ብለዋል።

“ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ጠዋት ነው የላከነው፣ ለአቶ ሽመልስ አብዲሳም ልከናል። ገና ምንም የሰጡት ምላሽ የለም ” ሲሉ አክለዋል።

“ 40 በመቶ ገደማ ይዞታችን ነው ይወሰዳል የተባለው ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “ አሁን ግማሹን አጥረዋል። ለሁለት ግለሰቦች ነው ይሰጣል የተባለው ” ነው ያሉት።

በተጨማሪ ፣ በፍርድ ቤትም እግድ እንዲያወርድላቸው እንደጠየቁ፣ የሚጠብቁት ያስገቡትን ደብዳቤ ምላሽ እየጠበቁ እንደሆነ ገልጸዋል።

“ አስቸኳይ ምላሽ የማይሰጠን ከሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ወደ መጥራት የምናመራ ይሆናል። በሰላማዊ መንገድ ድምፃችንን እናሰማለን። ሁል ጊዜ ቤተ ክርስቲያን የምትቆመው ከሰላም ጎን ነው። የመረበሽ የማስረበሽ ዓላማ የላትም ” ብለዋል።

ቅሬታ የቀረበበት የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም። ሆኖም በቀጣይ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ምላሹን የምናቀርብ ይሆናል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ ሃያ (20) ሄክታሩን አጥረውታል። መጋዘኖችንም እያፈረሷቸው ነው። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንገደዳለን ” - ቤተክርስቲያኗ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን፣ 40 በመቶ የሚሆን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ‘ በጉልበት ሊወስደው ነው ’ ስትል ከሰሞኑን በተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል። ጉዳዩ ከምን ደረሰ ? ቤተ ክርስቲያኗ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠችው…
#Update

“ መሬቱ ከዚህ በፊት በNGO እጅ የነበረ ነው ” - የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር 

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን “ 20 ሄክታር ” የሚሆነውን የኮሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር “ በጉልበት አጥሮታል ” ስትል ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሏን ሰጥታ ነበር።

ለጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፣ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ደብዳቤ እንዳስገባችም ገልጻ፣ ምላሽ ካልተሰጣት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንደምትገደድ ነው የገለጸችው።

ቤተ ክርስቲያኗ፣ ይህን ቃል ከመስጠቷ በቀደሙት ቀናት ውስጥም ከተማ አስተዳደሩ 40 በመቶ የሚሆነውን ይዞታዋን “ በጉልበት ሊወስደው ነው ” ስትል ተደጋጋሚ መግለጫ መስጠቷ ይታወቃል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ለቤተ ክርስቲያኗ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጥ የጠየቀው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ምላሹን ሰጥቷል።

አስተዳደሩ ፤ “ መሬቱ ከዚህ በፊት በNGO እጅ የነበረ ነው። በበጎ አድራጎት እጅ ነው የነበረው ” ብሏል።

አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈቀዱ የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር አካል፣ “ በኢትዮጵያ ሲቪክ ማኀበራት በኩል NGO ስራውን ጨርሶ መሬቱን ለመንግስት አስረክቦ ሂዷል ” ብለዋል።

“ በቤተ ክርስትያኗ ጥያቄ ለአምልኮ ወይም ለቀብር ቦታ ተብሎ የተሰጠ መሬት አይደለም ” ያሉት እኝሁ አካል፣ “ NGO ለበጎ አድራጎት ስራ ወስዶ ሲሰራበት የነበረ፣ በኋላ ፍቃዱን መልሶ የወጣበት የNGO መሬት መሆኑን ነው የማውቀው ” ሲሉ ተናግረዋል።

“ ያለው ሂደት ደግሞ በህግ በኩል ነው ተይዞ ያለው። ስለዚህ ‘ በአስተዳደሩ ተወሰደብን፣ ወከባ ተፈጠረብን ’ ለሚለው ነገር አስተዳደሩ የፈጠረው ወከባ የለም ” ብለዋል።

“ ለቤተ ክርስትያን መሬቱ ሲሰጥና ሲቀበሉ ውል አልነበረም፤ እነዚህ ሦስተኛ አካል ናቸው ማለት ነው ”  ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፥
- ቤተ ክርስቲያኗ እኮ መሬቱ ይዞታዋ ስለመሆኑ ማረጋገጫ እንዳላት፣
- ከግቢው ውስጥ የነበራት መጋዘን ትላንት እንደፈረሰ፣
- ሃያ (20) ሄክታሩ ይዞታዋ እንደታጠረ ነው የገለጸችው ለዚህ ምላሽዎ ምንድን ነው ? ሲል በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።

የአስተዳደሩ አካል ፥ “ መሬቱ በእጃቸው ላይ የነበረ አይደለም። በNGO እጅ የነበረ ነው። ስለዚህ ይህን በተመለከተ ይህንን ነው ማድረግ የሚቻለው ” ብለዋል።

“ 12 ሚሊዮን የቃለ ህይወት እምነት ተከታዮች ወይም 35 ሚሊዮን ወንጌላዊያን ተከታዮችን ጠቅሰው እያስኬዱት ያሉትም ስህተት ነው ” ሲሉ አክለዋል።

“ ምክንያቱም ቢመለከትም የቢሾፍቱ ቃለ ሕይወትን ነው እንጂ በአጠቃላይ የወንጌላዊያን ጥያቄና የመብት ጥሰት አድርገው በማቅረባቸው እኛም ትንሽ ከፍቶናል ” ነው ያሉት።

“ የሚመጣውን ስሞታ እንደ መንግስት ተቀብለን እናስተናግዳለን ” ያለው አስተዳደሩ፣ “ ባለመብት ከሆኑ ሚዲያ መጥራትና ሰላም እንዲጠፋ መቀስቀሱ ተገቢ አይደለም ” ሲል ወቅሷል።

ስለዚህ ይዞታው የቤተክርስቲያን አይደለም ብላችሁ ነው የምታምኑት ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ፣ “ በNGO እጅ ነው የነበረው። NGO ደግሞ የወሰደው ለበጎ አድራጎት ስራ ነው። ለአምልኮት፣ ለመቃብር አይደለም ” የሚል ምላሽ ነው የሰጡት።

መጨረሻም፣ “ የህግን መንገድ መከተሉ የተሻለ ነው የሚሆነው። አዲስ ጥያቄ ከሆነ ከእነርሱ ተቀብለን እናስተናግዳለን ” ሲሉ ተናግረዋል።

#TilvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ መሬቱ ከዚህ በፊት በNGO እጅ የነበረ ነው ” - የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር  የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን “ 20 ሄክታር ” የሚሆነውን የኮሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር “ በጉልበት አጥሮታል ” ስትል ትላንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሏን ሰጥታ ነበር። ለጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ፣ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ደብዳቤ እንዳስገባችም…
#Update!

" መሬቱ ጭራሽ በNGO እጅ ገብቶ አያውቅም ከመጀመሪያው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኗ እጅ የነበረ ነው " - ቤተ ክርስቲያኗ

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን 40 በመቶ የሚሆነው የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር " በጉልበት ሊወስደው ነው " ስትል በተደጋጋሚ መግለጿ ይታወቃል።

ለቤተ ክርስቲያኗ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጥ ቲክቫህ ትላንት የጠየቅነው የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ደግሞ፣ "መሬቱ በNGO እጅ የነበረ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

ቤተ ክርስቲያኗ ምን አለች ?

የከተማ አስተዳደሩ የሰጠውን ምላሽ በተመለከተ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሏን የሰጠችው ቤተ ክርስቲያኗ፣ " ቦታው በNGO እጅ ጭራሹኑ ያልነበረ ከመጀመሪያው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኗ እጅ የነበረ ነው " ብላለች።

" ' መሬቱ ከዚህ በፊት በNGO እጅ የነበረ ነው። በቤተ ክርስቲያን ጥያቄ ለአምልኮ ወይም ለመቃብር ቦታ የተሰጠ አይደለም' " የሚለው የከተማ አስተዳደሩ ምላሽ " የተሳሳተ መረጃ ነው " ነው ያለችው።

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ፀሐፊ ስምኦን ሙላቱ (ዶ/ር)፣ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ " ይሄ መሬት የተሰጠው ከመጀመሪያ ከ1981 ዓ/ም ጀምሮ ለኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" መሬቱ በNGO እጅ ገብቶ አያውቅም።  እሳቸው (የከተማ አስተዳደሩ አካል ማለታቸው ነው) የሚያወሩት ስለምን መሬት እንደሆነ አውቃለሁ። ሌላ ጉዳይ ነው ፤ የሌላ ቤተ እምነት ነው " ብለዋል።

" በደርግ መንግሥት ጊዜ በህፃናት ኮሚሽን በተፃፈ ደብዳቤ መቼ እንደተረከብነው፤ Every detail በመጀመሪያው መግለጫ ተሰጥቷል " ነው ያሉት።

" ስለዚህ እሳቸው (ከከተማ አስተዳደሩ ምላሽ የሰጡትን አካል ማለታቸው ነው) የሰጡት መልስ ስለሌላ ቦታ እንጂ ስለኩሪፍቱ የቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን አይደለም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ፣ ከተማ አስተዳደሩ ምላሽ የሰጠው ቤተክርስቲያኗ ' ሊወሰድብኝ ነው ' ስላለችው ኩሪፍቱ ማዕከል ነው፤ እርስዎ ምላሽ ተሰጠበት ያሉት የትኛው ቦታ ነው ታዲያ ? ሲል ጥያቄ አቅርቧል።

ዋና ፀሐፊው፣ " የሌላ ቤተ እምነት ነውና አሁን ስለሌላ ቤተ እምነት ማውራት ለእኔ ጥሩ ስላልሆነ ነው። የዚህ ነው የዛ ነው ባልልም እነርሱ ያውቁታል በትክክል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

" ምክንያቱም በሁለቱም ጉዳዮች ከንቲባ ጽሕፈት ቤትም ስንመላለስ ነበር፤ ያኛው ሌላ ጉዳይ ነው " ሲሉ አክለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ጉዳዩ የሚመለከታት የቢሾፍቱ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን እያለች የ35 ሚሊዮን ወንጌላዊያን የመብት ጥሰት አድርጎ ማቅረብ ልክ እንዳልሆነ ስለሰጠው ምላሽ ቤተክርስቲያኗ፣ ጉዳዩ የሁሉም የቃለ ሕይወት አማኞች እንደሆነ አጸፋ ሰጥታለች።

" 20 ሄክታሩን ወስደዋል፤ የቀረውን 20 ሄክታሩንም 'በላዩ ላይ አፍርሱ፣ የቀረውን ደግሞ ወደ መሬት ሊዝ ይግባ' እየተባለ ብዙ ነገር እየገፋ ነው ያለው " ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የነዋሪዎችድምጽ " የምንኖረው በኮንሶና አካባቢው ነው። የመብራት ለቀናት መጥፋት እና መቆራረጥ ከፍተኛ ችግር በስራችን እና በህይወታችን ላይ እያደረሰ ነው። ለቀናት ሲጠፋ ችግሩን ለመንግስት እንዳንናገር ድንገት ይመጣል መጣ ስንል ደግሞ በአንድ ሰአት ውስጥ ሁለት ሶስቴ ይቆራረጣል። አሁን ላይ ስራ መስራት አስቸጋሪ ሆኗል። በመብራት የሚሰሩ ስራዎች በተለይም ጸጉር ቤቶች ፣ ብየዳና የማሽነሪ ስራዎች…
#Update

" ለኮንሶና አካባቢው የመብራት ችግር አርባምንጭ ላይ ተጨማሪ የመብራት ማስተላለፊያ ሰብስቴሽን ይገነባል " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርእሰመስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ

" ለኮንሶ ዞን የራሱ የሆነ ሀይል ማሰራጫ ነው የሚያስፈልገው " -  የኮንሶና አካባቢው ወጣቶች

ከሰሞኑ የኮንሶና አካባቢዉ ማህበረሰብ በመብራት ኃይል መቆራረጥና መጥፋት ስራ እስከመዝጋት መድረሳቸዉን ገልጸዉ  መንግስት መፍትሄ እንዲሰጣቸዉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማሰማታቸው ይታወሳል።

ከሰሞኑ በተካኬደው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ስብሰባ ወቅት ጉዳዩን ያነሱት የክልሉ ርእሰመስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ " ለኮንሶና አካባቢው የመብራት ችግር አርባምንጭ ላይ ተጨማሪ የመብራት ማስተላለፊያ ሰብስቴሽን ይገነባል " ማለታቸው ተሰምቷል።

" በርእሰ መስተዳድሩ ንግግር ቅር ተሰኝተናል " ያሉ ግለሰቦች " በኮንሶና አካባቢዉ ሰላማዊ ሰልፍ እናካሂዳለን " በማለት በሶሻል ሚዲያ ቅስቀሳ ሲያደርጉ ተስተውለዋል።

ወጣቶቹ ለቅሬታቸዉ ምንጭ የሆነው የርእሰመስተዳድሩ ንግግር መሆኑን ጠቅሰዉ " ለኮንሶና አካባቢው ከባድ የመብራት ኃይል ችግር መፍትሄው ኮንሶ ላይ እንጅ አረባምንጭ ላይ ተጨማሪ ሰብስቴሽን መገንባት አይደለም "  ብለዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸዉ የኮንሶ ዞን መንግስት ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተሩ አቶ ሰራዊት ቲቶ ፥ " የርእሰመስተዳድሩን ንግግር ተከትሎ የሶሻል ሚዲያ እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም ከተማዋ ፍጹም ሰላማዊ መሆኑን ገልጸው ሁኔታውን በመጠቀም ችግር ለመፍጠር የሚያሴሩ እንዳሉ እናውቃለን " ብለዋል።

ኃላፊዉ አክለውም የመብራት ችግሩን ለመቅረፍ ከሚመለከታቸው የክልል አመራሮችና ከፍተኛ የመብራት ኃይል  ባለስልጣናት ጋር ዉይይት እንደተካሄደ በመጥቀስ የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ በማውጣት በአጭር ጊዜ ቅስጥ መፍትሄ ለመስጠት ተወስኖ እንቅስቃሴ መጀመሩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (No.7) • “ እኔ 50 ሺህ፣ ጓደኛዬ 30ዐ ሺህ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃዩ ነው ” - ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ • “ እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል ” - የታጋች ተማሪ ወንድም ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ከታገቱ 10 ቀናት አስቆጥረዋል። ስለታጋቾቹ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ? ቲክቫህ…
#Update (No.8)

" ባነር አሰርተን ልመና ወጥተናል ገንዘብ ግን እየተገኘ አይደለም " - የታጋች ተማሪ ቤተሰብ

ትምህርት አጠናቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች “ ገብረ ጉራቻ ” የሚባል ቦታ ሲደርሱ መታገታቸው አይዘነጋም።

ተማሪዎቹ የታገቱት ሰኔ 26/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ብዛታቸው በትክክል ባይታወቅም ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከእገታው ያመለጡ ተማሪዎች በሁለት ታታ አውቶብስ የነበሩ መሆናቸውን በወቅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ከታጋቾቹ መካከል አንዳንዶቹ ከፍተኛ ብር ከፍለው መለቀቃቸውን መግለጻቸውም ይታወሳል።

የታጋቾቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የታጋቾቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የታጋች ቤተሰቦቸ፣ ልጆቻቸው ባለመለቀቃቸው ጭንቀት ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቃሏን ለቲክቫህ የሰጠች አንድ የታጋች እህት አጋቾቹ የጠየቁትን ግማሽ ሚሊዮን ብር ካልተላከላቸው ታጋቾቹን ‘ አንለቅም ’ ማለታቸውን ገልጻ፣ “ ባነር አሰርተን ልመና ወጥተናል ገንዘብ ግን እየተገኘ አይደለም ” ብላለች።

በተጨማሪም እህቷ ፤ ያሉት ታጋች ተማሪዎች ምግብ በወቅቱ እንደማያገኙና ልብስም ስለሌላቸው በብርድ እየተሰቃዩ እንደሆነ እንደገለጸችላት ተናግራለች።

" አጋቾቹ 700 ሺህ ጠይቀውናል " ያለ ሌላኛው የአንዲት ታጋች ተማሪ ወንድም፣ ታጋቿ በስቃይ ውስጥ እንዳለች ቤተሰብ ገንዘቡን ለመላክ አቅም እንዳላገኘ ገልጿል።

" ቤተሰቡ በከባድ ሀዘን ላይ ነው። በተወለድንበት ሀገር ለዛውም ንጹሐን ተማሪ ታግተው ሲሰቃዩ መንግስት ምን እየሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።

ታጋቾቹን ለማስቀቅ ምን እየሰራ ነው ? ሲል ቲክቫህ የጠየቀው የኦሮሚያ ክልል ስላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከዚህ ቀደም የሰጠው መግለጫ እንዳለ ከመጥቀስ ውጪ በጸጥታ ቢሮው በኩል ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።

ሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማትም ለጉዳዩ ምላሽ ለመስጠተ ፈቃደኛ አልሆኑም።

የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ከዚህ ቀደም በሰጡት መግለጫ፣ በ 'ሸኔ ቡድን ታግተው ተወሰዱ' ካላቸው 167 ታጋቾች መካከል የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀው፣ 7 ታጋቾች ብቻ እንደቀሩ አሳውቆ ነበር።

አንድ ከቀናት በፊት ገንዘብ ከፍሎ ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ ግን እርሱ ከነበረበት የእገታ ቦታ ብቻ ከ60 በላይ ታጋቾች እንዳሉ ለቲክቫህ ተናግሮ ነበር።

ሌላኛዋ በእገታው ላይ ያለች ተማሪ ባለችበት ጫካ ፣ በርካታ ታጋች ተማሪዎች እንዳሉ እንደተናገረች ቤተሰቦቿ ለቲክቫህ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OnlineScam ባለፈው ወር ላይ የላኦ እና የቻይና ፖሊስ በሰሜን ላኦስ ጎልደን ትሪያንግል ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በህገወጥ የጥሪ ማእከል የኦንላይን ማጭበርበር (Online Scam) ተግባር ላይ ተሰማርተዋል ያሏቸውን 280 ቻይናውያንን በቁጥጥር ስር አውለዋል። ግለሰቦቹም ወደ ቻይና ዲፖርት ተደርገዋል። ፖሊስ ግለሰቦቹን በያዘበት ወቅት 460 ኮምፒዩተሮች እና 1,345 ስልኮችን ይዟል። እንዚህ አካላት…
#Update

ሕንድ በማይናማር እንዲሁም ካምቦዲያ በሳይበር ወንጀል / የኦንላይን የማጭበርበሪያ ማዕከላት (Online Scam Centers) ውስጥ ያሉ ዜጎቿን አስወጣች።

ሀገሪቱ በማይንማር፣ ማያዋዲ ' ሽዌ ኮ ኮ '  በሚገኝ የኦንላይን ማጭበርበሪያ ማዕከል ውስጥ የሚገኙ 11 ተጎጂ ዜጎቿን እንዳስወጣች ገልጻለች።

ሕንዳዊያኑ ከማዕከሉ እንዲወጡ የተደረገው በማይናማር ባለስልጣናት እና በአካባቢው ወጣቶችን ከቦታው እንዲወጡ በሚረዱ ሰዎች ርብርብ ነው።

አሁን ላይ እነዚህ ሕንዳዊያን ዜጎች ወደ ሀገራቸው ሕንድ እንዲመለሱ እየተሰራ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአካባቢው ያገኘው መረጃ ያሳያል።

ከዚህ በተጨማሪ የሕንድ መንግሥት ከካምቦዲያ ባለስልጣናት ጋር በመተባበር በሳይበር ወንጀል / ኦንላይን ማጭበርበር ማዕከላት ውስጥ እንዲሰሩ ሲደረጉ የነበሩ 14 የሕንድ ዜጎችን አስወጥቷል።

በፍጥነት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እየተሰራ ስለመሆኑም ሰምተናል።

ሕንድ በርካታ ወጣቶቿ በማጭበርበሪያ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙባት ሀገር ስትሆን ከዚህ ቀደም መሰል ዜጎቿን የማስወጣት እርምጃ የወሰደች ሲሆን አሁንም ቀጥላለች።

ሌሎች ሀገራት በተመሳሳይ ተጠቂ ናቸው ያሏቸው ዜጎቻቸውን የማስወጣት እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።

በማይናማር፣ ላኦስ፣ ካምቦዲያ ፣ ቻይና ታይላንድ ድንበር፣ ታይላንድ ማይናማር ድንበር ባሉ የማጭበርበሪያ ማዕከላት እጅግ በርካታ የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ይገኛሉ።

አንዳንድ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች አሉ (ከተለያዩ ሀገራት)።

በስፍራው የሚገኙት ብዙሃኑ ወጣቶች ናቸው።

ወደዚህ ተግባር የገቡት እራሳቸው ተጭበርበረው ነው / ይህ ማለት እራሳቸውም ተጎጂዎች (ሰለባ) ናቸው።

ደላሎችና ኤጀንሲዎች ወጣቶች 'ወደ ታይላንድ / ወደ ሌላ ሀገር' ለ፦
- ሴልስ
- የማርኬቲንግ
- ለሆቴል እንግዳ ተቀባይ
- ለተቋማት ደንበኞችን ማነጋገር በሚል ነው የሚልኳቸው።

በኃላም ወደ ጎረቤት ሀገራት በመውሰድ የተደረጀ የኦንላይ ማጭበርበር ስራ ላይ እንዲሰማሩ ነው የሚደረገው።

ወጣቶቹ ከሚሰማሩባቸው ተግባራት ዋነኛው ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት በመክፈት ሰዎችን በተለይ ሴትን በወንድ / ወንድ በሴት አስመስለው በማነጋገር ገንዘብ ማጭበርበር ነው።

የታዘዙትን አድርገው ገንዘብ ካላመጡም የከፋ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይችላል።

ወጣቶችን እንዲያጭበረብሩ የሚያሰሩ ማፊያዎቹ በቀጠናው እጃቸው ረጅም የሆነ ሰዎች ናቸው።

እጃቸው በረዘመ ማፊያዎች በሚመራው የሳይበር ወንጀል / የኦንላይን ማጭበርበር / ተግባር በየአመቱ እስከ 43.8 ቢሊዮን ዶላር ይዘረፋል።

ስለ ማጭበርበሪያ ስልቶቹ / ሰዎችን በምን መንገድ እንደሚያጭበረብሩ በዚህ ያንብቡ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/88986

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሚዲያ ዘመቻችሁን እንድታቆሙ እንጠይቃለን " - የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር ፥ " በሕገ-ወጥ መንገድ ረዘም ላለ ጊዜ ሳይለማ የቆየ 280,000 ካሬ ሜትር ለልማት እንዲውል ማድረግ ሕገ- መንግስትን ማስከበር እና ማክበር እንጂ የሚያስወቅስ ጉዳይ አይደለም " አለ። ይህን ያለው ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ ነው። አስተዳደሩ ፥ " ሕግ እና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን ማስከበር የአንድ…
#Update

“ ሁለቱንም አካላት ፊት ለፊት ለማገናኘት የጋራ መድረክ ይዘናል ” - የኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ

የኢትዮጵያ ቃለ ህይወት ቤተክርስቲያን የኩሪፍቱ ማዕከል ይዞታዋን የቢሾፍቱ ከተማ አስተዳደር “በጉልበት ሊወስደው ነው” ስትል በተደጋጋሚ ቅሬታ ማቅረቧ ይታወሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቅሬታው ምላሽ የጠየቀው የከተማ አሰተዳደሩ በበኩሉ፣ “ መሬቱ በNGO እጅ የነበረ ነው ” የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር።

ይህንኑ የከተማ አስተዳደሩን ምላሽ የተመለከተችው ቤተክርስቲያኗ፣ “ መሬቱ በጭራሽ በNGO እጅ ገብቶ አያውቅም ከመጀመሪያው ጀምሮ የቤተ ክርስቲያኗ እጅ የነበረ ነው ” የሚል አጸፋ መሰጠቷ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ስለጉዳዩ ምን አለ ?

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሁለቱም አካላት በጋራ ተወያይተው ችግራቸውን እንዲፈቱ በተናጠል እንዳነጋገራቸው ገልጿል።

የጉባዔው ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ሁለቱንም አካላት ፊት ለፊት ለማገናኘት የጋራ መድረክ ይዘናል ” ብለዋል።

“ ህዝቡ ወዴት ይሄዳል ? ሰው ሲያኮርፍ ወዴት ያመራል ? የሚሉ ጉዳዮች ይኖሬሉ ” ያሉት ዋና ፀሐፊው፣ “ ስለዚህ ይህንን ቁጭ ብሎ Manage ማድረግ ያስፈልጋል ” ሲሉ ተናግረዋል።

ሁለቱም አካላት በጋራ ለመነጋገር ፈቃደኞች እንደሆኑ ነገር ግን ጉዳዩ ገና በሂደት ላይ እንደሆነ፣ ወደ ስምምነት እንዲመጡ ለማድረግ ጉባዔው የጋራ መድረክ እንዳዘጋጀ አስረድተዋል።

የከተማ አስተዳደሩን በተናጠል እንዳወያዩ፣ ቤተ ክርስቲያኗን ለማወያዬት በሂደት ላይ እንደሆኑ የገለጹት ዋና ፀሐፊው፣ “ አንድ ሳምንት ሊፈጅብን ይችላል ጨፌ ስብሰባ ስለገቡ ዋናዎቹ። የጋራ ፕሮግራም ይዘናል እንወስናለን ” ብለዋል።

ጉባዔው ሁለቱም አካላት የቃላት ውርዋሮ አቁመው ወደ ስምምነት እንዲመጡ የማግባባት ሥራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🔈#የሰራተኞችድምጽ " የደመወዝ ጥያቄ እንዳንጠይቅ በፖሊስ መደብደባችንን እና መታሰራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን !! " - የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች እና ሰራተኞች " ከግንቦት ወር ጀምሮ ደመወዝ አልተከፈለንም " ያሉ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዎችና ሰራተኞች ያሉበትን ችግር እና ቅሬታቸውን ለመግለጽ ወደዞን መምሪያ በመሄድ ላይ ሳሉ በፖሊስ ተደብድበው መመለሳቸውን…
#Update

° " የተቆራረጠ ደሞዝ አንወስድም ምክኒያቱም ካሁን በፊትም እንዲሁ ተደርገናል " - የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች

° " የተፈጠረው የካሽ እጥረት በመሆኑ ወደስራ ተመለሱ " - የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ


የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች " ከግንቦት ወር ጀምሮ ደሞዝ አልተከፈለንም " በሚል ስራ አቁመው ወደ ዞኑ ጤና መምሪያ ጥያቄ ለማቅረብ ለመሄድ ሲሞክሩ በሀድያ ዞን ፖሊስ ተደብድበው ወደ ሆሳዕና ከተማ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።

ጉዳዩን ከምን ደረሰ ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላችሁ ሰራተኞቹ አሁንም ስራ እንዳቆሙ መሆኑን በመግለጽ የተፈቀደውን የአንድ ወር ደሞዝ እንዳይወስዱ በ2015 ዓ/ም በዚህ መልኩ እንደተቃጠለው ገንዘባቸው እንዳይሆን ስጋት እንደገባቸው ገልጸዋል።

ሰራተኞቹ አሁን ላይ ውይይት አድርገዉ አንዳች ውሳኔ ላይ ለመድረስ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን በመግለጽ በቅርቡ አቋማቸውን እንደሚገልጹ ነግረዉናል።

የሰራተኞቹን ስራ ማቆም ተከትሎ በስራ ላይ  ችግር አልተፈጠረም ወይ ? ስንል ጥያቄ ያቀረብንላቸው የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ  አብርሀም ሎምቤ ፥ " ስራ ያላቆሙ ሰራተኞች በጫና ውስጥ ሆነው እየሰሩ ቢሆንም ስራ ያቆሙ ሰራተኞች ወደስራ ገበታቸው ተመልሰው ብንነጋገር የተሻለ ነው " ብለዋል።

ለምን የሰሩበትን ክፍያ አትሰጧቸውም ? በሚል ላነሳነው ጥያቄ " የካሽ እጥረት ነው የተፈጠረው ፤ የካሽ እጥረት እንደሀገር የሚገጥም በመሆኑ ክፍያቸው አይቀርባቸውም " ሲሉ መልሰዋል።

በሌላ በኩል ስራቸውን ያቆሙ ሰራተኞች ወደስራ መመለሳቸውን በደብዳቤ እየገለጹ የአንድ ወር ደሞዝ ይውሰዱ ስለተባለው ጉዳይ የጠየቅናቸው አቶ አብርሀም " ዋናው ወደስራ መመለሳቸው በመሆኑ በቃልም ቢሆን ከሰው ሀብት ጋር ተነጋግረን ስራ መጀመር ይችላሉ " ብለዋል።

ሰራተኞች ግን ባለሙያ ሆስፒታል ውስጥ እንደሌለ እየታወቀ ማስታወቂያው የተነገረው ብለዋል።

" ሲጀመር የሰኔዉ ላይ ለመወያየት ቀድሞ የግንቦት የት ነዉ ያለዉ ስላልን ነዉ ይሄ ሁሉ በደል የደረሰብን። " ሲሉ ገልጸዋል።

" አሁንም የግንቦት ላባችን እንዳይበላ ሁሉም ይወቅልን " ብለዋል።

ሰራተኞቹ አስገዳጅ ሁኔታ ተፈጥሮ የሰኔ ላይ እንዲፈርሙ ከተደረጉ በኃላ የግንቦቱ ክፍያቸው ተበልቶ ሊቀር ይችላል ሚል ስጋት እንዳላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
#Update

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ሀዘናቸውን ገለጹ።

ጠ/ሚኒስትሩ ፥ " በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ  ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካታ  ዜጎቻችንን ሕይወት ቀጥፏል " ብለዋል።

" በደረሰው አስከፊ ጉዳት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እገልጻለሁ " ብለዋል።

" አደጋውን ተከትሎ የፌዴራል የአደጋ መከላከል ግብረ-ሀይል በአካባቢው ተሰማርቶ የአደጋውን ጉዳት ለመቀነስ ርብርብ እያደረገ ነው " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Tassa Tassa Tassa 😭 “ ማሽን መግባት የማይችልበት ተዳፋት ቦታ ስለሆነ በሰው ኃይል ቁፋሮ እየተደረገ እየተፈለገ ነው ያለው ” - ዞኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ ትላንት በደረሰው የመሬት ናዳ የሞቱት አብዛኛዎቹ ነፍስ ለማዳን የገቡ እንዲሁም ችግሩን ለማዬት የተሰበሰቡ ሰዎች መሆናቸውን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽንና ሚዲያ ዳይሬክቶሬት…
#Update

የሟቾች ቁጥር 229 ደረሰ።

በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ በመሬት ናዳ ሳቢያ የሞቱ ወገኖች ቁጥር 229 ደርሷል።

ከወረዳው አስተዳዳር በተገኘ መረጃ የሟቾች ቁጥር ወንድ 148 ሴት 81 በድምሩ 229 መድረሱ ተሰምቷል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበል ትላንት ከረፋዱ 4 ሰዓት አካባቢ ድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ መድረሱ ይታወሳል።

አስክሬን የማፈላለጉ ስራ አሁንም ቀጥሏል።

የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊያሻቅብ ይችላል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
 #Update #TPLF

" ' ስልጣን ልቀቅ አልለቅም ' በሚሉ የሁለት ቡድን ፍላጎት የህዝባችን ስቃይ እንዲራዘም አንሻም " - የህወሓት ማእከላዊ  የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት

የህወሓት ማእከላዊ  የቁጥጥር ኮሚሽን አባላት ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

የኮሚሽኑ አባላት በጋራ በሰጡት መግለጫ " ትናንት ህዝባችን ላይ ያደረስነው ጉዳት በመረዳት ዛሬ መፀፀትና ለደህንነቱ መትጋት ይገባናል " ብሏል። 

" በኛ ጦስ ምክንያት በህዝባችን ላይ ሊከተል የሚችለው መከራ ከወዲሁ በመገንዘብ ሊካሄድ ከታሰበ ጉባኤ ራሳችንን አግልለናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

" በህወሓት አቋም የሚባል ጠፍቶ ቦታውን ኔትወርክና መቦዳደን ተክቶታል " ሲሉም ገልጸዋል።

" ግልፅነት ፣ አሳታፊ አሰራር እና ዴሞክራሲ ጠፍቶ ስልጣንን አለአግባብ መጠቀም አይለዋል " ያሉት የኮሚሽን አባላቱ ፥ " 9 አባላት ያሉት የጉባኤ አዘጋጅ ኮሚቴ ለይስሙላ ቢቋቋምም ይህንን ወደ ጎን በመተው ስራውን የሚያከናውነው ሃይል የበላይነት አለኝ የሚል አካል ነው " በማለት ድርጊቱ አውግዘዋል።

" ' ስልጣን ልቀቅ አልለቅም ' በሚሉ የሁለት ቡድን ፍላጎት የህዝባችን ስቃይ እንዲራዘም አንሻም ፤ ከመተማመን መግባባትና ዴሞክራሲያዊ መንገድ ውጪ የሚካሄድ ህዝባዊ ጠቀሜታ ስለሌለው የዚሁ ተግባር አካልና ተባባሪ መሆን አንፈልግም " ብለዋል።

የኮሚሽኑ አባላት ፥ " አካሄዳችሁ አስተካክሉ ላለ አካልና ግለሰብ የሌለ ስም እየሰጡ ማጥላላት የትም አያደርስም " ያሉ ሲሆን " ከኔትወርክ እና መጠላለፍ ያልፀዳ ጉባኤ ማካሄድ ህዝብን ይጎዳል እኛም የዘህ ጉዳት ተባባሪ ላለመሆን ይካሄዳል ከሚባለው ጉባኤ ራሳችን አግልለናል " ሲሉ አሳውቀዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMK

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጎፋ 🕯️ “ ህብረተሰቡ እየተረባረበ አስከሬኖችን በቻሉት ልክ እያወጡ ነው። ቁፋሮው እንደቀጠለ ነው ” - ጎፋ ዞን በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ከቀናት በፊት በተከሰተው የመሬት ናዳ አደጋ የሟቾችን አስክሬን በቁፋሮ የማውጣቱ ስራው እንደቀጠለ መሆኑን ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጿል። ቃላቸውን የሰጡት የዞኑ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽንና ሚዲያ ዳይሬክቶሬት አቶ ገነነ እንዳሻው፣ ቁፋሮው እንደቀጠለ መሆኑን…
#Update

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ ተገኝተዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ፣ ከቀድሞ ጠ/ሚ አቶ ኃለማርያም ደሳለኝ ፣ ከፌዴራል ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በማሆን በገዜ ጎፋ ወረዳ ተገኝተው በመሬት ናዳ የተጎዱ ወገኖችን እያጽናኑ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንትና ወደ ስፍራው ሊያቀኑ የነበረ ቢሆንም አጋጣሚ አየሩ ዳመናማና ለጉዞ አመቺ ባለመሆኑ ምክንያት እንደቀሩ ዞኑ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጹ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

° " የከተማዉ ከንቲባ ሙሉ ደሞዛችን በሂደት እንደሚከፈለን ቃል ገብተው ወደስራ ብንመለስም ፈርማችሁ ስራ ጀምሩ መባላችን አስፈርቶናል " - ሰራተኞች

° " ህጋዊ ደብዳቤ አስገብተው እንደወጡ ህጋዊ ደብዳቤ  አስገብተው ሊመለሱ ይገባል " - የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ


ከሰሞኑ " የሶስት ወር ደሞዝ ዘግይቶብናል " ያሉ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ስራ ማቆማቸውን ይህን ለማሳወቅም ወደዞኑ ዋና ከተማ ሲያቀኑ ፖሊስ " ሆሳዕና አትገቡም " ብሎ ከከተማው መግቢያ እንዳስመለሳቸው መዘገባችን ይታወሳል።

ሰራተኞቹ ምንም እንኳን ወደዞኑ አመራሮች ቀርበው አቤቱታቸውን ባያቀርቡም ስራ አቁመው መሰንበታቸዉን ተከትሎ የሾኔ ከተማ ከንቲባና ሌሎች ባለስልጣናት አወያይተዋቸው ነበር።

በውይይቱም የአንድ ወር ደሞዛቸዉን ማለትም የሰኔን ቅድሚያ  እንዲወስዱና ቀሪውን የግንቦት ወር ደግሞ በሂደት እንደሚያገኙ ከንቲባው ቃል ገብተውላቸው ወደስራ ቢመለሱም እስካሁን ስራ በማቋረጣችሁ የይቅርታ ደብዳቤ አስገቡ መባሉን ተከትሎ ስራውን መጀመር አለመቻላቸውንና መፈረም የሚለዉ ሀሳብ እንዳስፈራቸው ገልጸዉልናል።

ጉዳዩን በተመለከተ ከቀናት በፊት ወደስራ ከገቡ በቃል ሪፖርት አድርገው ስራቸዉን መጀመር ይችላሉ ያሉን የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ አብርሀም ሎምቤ ምን ሀሳባችሁን ቀየራችሁ ? ስንል ላቀረብንላቸዉ ጥያቄ " ሀሳብ መቀየር ሳይሆን የድርጅቱ አሰራር ስለሆነ ነው " ሲሉ መልሰውልናል።

" ሰራተኞቹ ፍርሀት ሊሰማቸው አይገባም " ያሉት ስራ አስኪያጁ " ህጋዊ ደብዳቤ አስገብተዉ እንደወጡ ሁሉ ህጋዊ ደብዳቤ  አስገብተው ሊመለሱ ይገባል ይህ ደግሞ ሊያስፈራቸዉ አይገባም ብ ጉዳዩ ችግር የለውም ብለን አስረድተናቸዋል " ሲሉም ገልጸዉልናል።

አሁን ላይ የተወሰኑ ሰራተኞች ፈርመዉ ስራ ሲጀምሩ  የተወሰኑት ፊርማዉን ባለመፈረማቸው ምክኒያት ወደስራ አለመመለሳቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ሰራተኞቹ ያለፈው የደከሙበት ደመወዛቸውን ተብልቶ ይቀራል የሚል ስጋት እንዳላቸውም ሳይናገሩ አላለፉም።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#IMF : የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ኢትዮጵያ በጠየቀችው ብድር ላይ ለመወያየት ነገ ሰኞ ሐምሌ 22 / 2016 ይሰበሰባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ብሎምበርግ ድረገጽ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የመረጃ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ ጋር የምታደርገው ድርድር ከተሳካ በቀጣይ አመታት 10.5 ቢሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል…
#Update

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) አስፈጻሚ ቦርድ ለኢትዮጵያ የሚሆንና መጠኑ 2.556 ቢሊዮን SDR (የኮታው 850% ወይም ወደ 3.4 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ) የሆነ የ4 ዓመት የተራዘመ የብድር አገልግሎት አቅርቦት ዛሬ አጽድቋል።

ይህ የ4 ዓመት ፓኬጅ፦
- የማክሮ ኢኮኖሚ ሚዛን መፋለስን መፍታትን
- በግል ዘርፉ ለሚመራ እድገት መሠረት መጣልን
- የመንግሥትን የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ አፈጻጸምን የሚደግፍ ነው ተብሏል።

ውሳኔው ኢትዮጵያ ከባላንስ ኦፍ ፓይመንት ጋር የተያያዙ ፍላጎቶቿን እንድታሟላ ይረዳታት ተብሏል።

በተጨማሪ በጀቷን የሚደግፈውን የ766.75 ሚሊዮን SDR ወይም 1 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ የሚሆን ገንዘብ ክፍያ ወዲያውኑ እንዲለቀቅ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል።

(ዝርዝር መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia