TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ያለሙትን አሳክተው እፎይ የሚሉበትን የተሻለ አማራጭ ይዘን እየመጣን ነው‼️
በቅርብ ቀን ይጠብቁን …
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተራዘሟል በአዲስ አበባ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባ  እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ። ምዝገባው ሰኔ 30 ያበቃል መባሉ ይታወሳል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር  ቢሮ ይፋ ባደረገው መረጃ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ 248,469 የኪራይ ውል ምዝገባ ተከናውኗል። አሁንም ምዝገባው እንደቀጠለ ይገኛል ብሏል። ነገር ግን ፦ - በርካታ ተመዝጋቢ በመኖሩ…
#AddisAbaba

" ለሁለተኛ ዙር አይራዘምም " - የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ፤ የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት ምዝገባ  ለሁለተኛ ጊዜ የማይራዘም መሆኑ አሳውቋል።

ቢሮው በመጀመርያው የምዝገባ ወቅት የነበረው መጨናነቅ እንዳይደገም ነዋሪዎች ከወዲሁ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት በነዋሪዎች ጥያቄ መሰረት መራዘሙን ያስታወሰው ቢሮው " ነገር ግን አሁንም መዘናጋት እንደሚታይ " ገልጿል።

ባለፍነው ሰኔ 1 ጀምሮ ሰኔ 30 ይጠናቃቀል ተብሎ በነበረው ስምምነት በመጀመርያዎቹ ምዝገባ ቀናት ከፍተኛ የሆነ መቀዛቀዝ እንደነበር  ፤ ነገር ግን በወሩ መጨረሻ አካባቢ ከፍተኛ ቁጥር የነበረው ተዋዋይ መገኘቱን አመልክቷል።

በዚህም በቀን ከ30,000 በላይ ነዋሪ ይመዘገብ እንደነበር ተጠቁሟል።

በነዋሪዎች ጥያቄ የውል ስምምነቱ እስከ ሐምሌ 24/2016 ዓ/ም ቢራዘምም አሁንም መዘናጋት እንደሚታይ ተጠቁሟል።

የአከራይ ተከራይ ውል ስምምነት ለሁለተኛ ጊዜ የማይራዘም በመሆኑና በመጀመርያው የምዝገባ ወቅት የነበረው መጨናነቅ እንዳይደገም ነዋሪዎች ከወዲሁ እንዲመዘገቡ ቢሮው ጥሪ ቀርቧል።

#AddisAbabaHousingDevelopmentandAdministrationBureau

@tikvahethiopia
🔈#የሰራተኞችድምጽ

° " ሰበብ እየተፈለገ ከስራ እየተባረርን ነው " - የደቡብ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ሰራተኞች

° " ከህግና ስርአት ውጭ የተሰናበተ አንድም ሰራተኛ የለም " - የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ


" የደቡብ ክልል መንግሥት ፈርሶ ሰራተኛዉ ሲበተን ደቡብ ኢትዮጵያ ቢደርሰንም እንደ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛ መብታችን ተከብሮ መስራት አልቻልንም " ሲሉ የደቡብ ኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቢሮ ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

" ቢሮው መቀመጫውን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ሶዶ ከተማ  ካደረገና ስራ ከጀመርን ጀምሮ በርካታ ግፍ እየተፈጸመብን ነው "  የሚሉት ከቢሮው የተባረሩ እና ያለጥፋታችን በከባድ ማስጠንቀቂያ ውስጥ ነን ያሉ  ሰራተኞች " ቅጣቶች እና ክሶች ያለህግና ስርአት የቢሮው ዲስፕሊን ኮሚቴ እንኳን በማያዉቀዉ መልኩ እየተተገበሩ ናቸው " ሲሉ ከሰዋል።

" በዚህ አመት ብቻ ስራ ከጀመርነዉ ዉስጥ ወደ 5 ሰራተኞች ያለማስጠንቀቂያ እና ህጋዊ ስርአት ከቢሮዉ ተገፍትረን ተባረናል " በማለት ገልጸዋል።

" ከቢሮ ተገፍትረን ከተባርንና ደሞዝ ከተቋረጠብን በኋላ ከስራ ገበታ መቅረታችን የሚገልጽ ደብዳቤ ይለጠፍብናል " የሚሉት ሰራተኞቹ  ጉዳዩን ለክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስ  ብናሳውቁም መፍትሄ አላገኘነም ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰራተኞችን ቅሬት ይዞን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊን ዶክተር ኦንጋዮ ኦዳን አነጋግሯል።

እሳቸው ፥ " ከህግ እና ስርአት ውጭ አንድም ሰራተኛ አልተሰናበተም " ብለዋል።

" በደል ደርሶብኛል የሚል ካለም ለመነጋገርና ስህተት ተሰርቶ ከሆነ ለመጠየቅ ዝግጁ ነን " ሲሉ ቃል ገብተዋል።

" በብዛት ከቢሮዉ የለቀቁ ሰራተኞች ፦
- ከስራ በተደጋጋሚ የሚቀሩ
- መቀመጫቸውን ሀዋሳ ያደረጉ
- ተመላልሶ መስራትን ካለመፈለግ ነው " የሚሉት ኃላፊው " ቢሮ ሳይቀመጡ ስራ መስራት ደግሞ አግባብ አይደለም " ብለዋል።

ከዚህ ውጭ ችግሮች እንዳይፈጠሩ ብዙ ጥረቶች ሲያደርጉ መቆየታቸውንም ገልጸዉ አብዛኞቹ ሰራተኞች ከስራ መቅረታቸውን ተከትሎ ህጋዊ ደብዳቤ መጻፉን ገልጸዋል።

በሌላ በኩል ሰራተኞች " ተበድለናል " ብለዉ ለቢው አቤቱታ ሲያስገቡ ምላሽ ለምን አለተሰጣቸውም ? ብለን ጠየቀናል።

ቢሮው ፥ ምንም እንኳን ተበዳዮች ማመልከቻ አስገብተናል ቢሉንም " በጉዳዩ ላይ መረጃዉ የለኝም " ሲል ምላሽ ሰጥቶናል።

ይሁንና እንዲህ አይነት ችግሮች ያሉባቸዉ ሰራተኞች ጥያቄና አቤቱታ ይዘዉ ከመጡ እንደሚያስተናግድና ለዚህም በአካል ወላይታ ሶዶ በሚገኘዉ ቢሮዉ ሊቀርቡ እንደሚገባ ገልጿል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Addis Ababa University- Cisco Networking Academy,
@CiscoExams www.netacad.com www.cisco.com

Online Live class - Cisco CCNA Professional Networking Course Training & Certification Preparation.

Registration Date: May 20,2024 to July 26, 2024
Class start date: July 27, 2024.

Course Recognitions: CCNA trainees will receive 3 Certificate of Completion, 3 Letter of Merit, 3 Digital Badge that recognized and accepted in USA, Canada, and Europe, and you will award 58% CCNA certification exam discount voucher.

Mobile #: 0945-039478/0902-340070/ 0935-602563/
Office : 011-1-260194

Follow our telegram channel: @CiscoExams
#TeleTV

በድርጊት እና በአስፈሪ ዘውግ የተሞሉ የሃገራችን ድንቅ ፊልሞች "6 ሰአት ከለሊቱ" እና "ትዝታ" በቴሌቲቪ መተግበሪያ ብቻ!!

ዛሬዉኑ የቴሌቲቪን መተግበሪያ ከ Playstore ወይም ከ Appstore https://teletv.et/download በማውረድ አልያም በ ድህረ-ገጽ https://www.teletv.et  ላይ በመግባት መመዝገብ ይችላል።

👉ቴሊቲቪ ላይ የሚገኙ ፊልሞችን መመልከት የሚቻለው መተግበሪያው ላይ ብቻ ነው!!

ቴሌቲቪ! ሲኒማ በስልክዎ !

#TeleTV #Tizita and #KeLelitu6Seat  #Tiztamovie #6seatkelelit #Staytuned #Launch #ExclusiveMovies #Newethiopianmovie #ethiopianmovie #NewBeginnings #Teletv #Excitement #BigReveal #EthiopianCinema #OnlineCinema #NewPlatform #StayTuned
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

የ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና የማለፊያ ነጥብ 50 ሲሆን ለአካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ደግሞ 45 እንደሆን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

በከተማዋ በሚገኙ የመንግሥት እና የግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ መርሐግብር ትምህርታቸውን ተከታትለው፥ በ2016 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 85,046 ተማሪዎች መካከል 80,198 ተማሪዎች ወይም 94.3 በመቶዎቹ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡

የተማሪ ወላጆች ተማሪዎች ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጫን የመለያ ቁጥር እና ስም በማስገባት ውጤት መመልከት ይችላሉ። ወይም ከስር የተቀመጠውን የቴሌግራም ቦት ይጠቀሙ፡፡

ውጤት ለማየት፦ https://aa6.ministry.et/#/result

በቴሌግራም ቦት፦ @emacs_ministry_result_qmt_bot

@tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ተጠርጣሪዎችን የመያዝ ኦፕሬሽን መጀመሩ ተሰማ።   በተለያዩ ህጋዊ ያልሆኑ ተግባራት የተሳተፉ አካላት እና ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩን ጊዚያዊ አስተዳደሩ አሳውቋል። በትግራይ ከጊዜ ወደ ጊዜ ለመንግስት እና ለህዝብም ድህንነት አስጊ የሆኑ ኢ-ህጋዊ ተግባራት እየተበራከቱ መምጣታቸውን አስተዳደሩ አመልክቷል። ይህን ለመቆጣጠር ኮሚቴዎችን አቋቁሞ በማጣራት…
#Tigray

" ለረጅም ግዜ ታግሰናል። ከዚህ በኋላ ግን ሁሉም ነገር በህግና ስርዓት መልክ እንዲይዝ እናደርጋለን " - የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰላምና የፀጥታ ቢሮ   

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የሰላምና የፀጥታ ቢሮ ፤ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

" በአሁኑ ሰዓት የክልሉ የፀጥታ ሃይል በተናበበና በተቀናጀ  አኳሃን በመስራት በቅርቡ ከሌላው ጊዜ የተሻለ የፀጥታ ሁኔታ እንዲኖር በመስራት ላይ እንገኛለን " ብሏል።

የህግ ልዕልና ማረጋገጥ እንዳለ ሆኖ በተለይ  ከብረታ ብረት ስርቆት ጋር ተያይዞ የተጀመረው ህግ የማስከበር ዘመቻ እንደ መነሻ በመውሰድ በወርቅ ፣ ማዕድንና መሬት ዘረፋና እገታ እንዲሁም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ስርዓት የማስያዝ ስራዎችና እርምጃዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብሏል።

" የተጀመረው ህግ የማስከበር እንቅስቃሴ ያስደነገጣቸው ህገ-ወጥ  አካላት ጉዳዩ ፓለቲካዊ መልክ ሊያስይዙት እየሞከሩ ነው " ያለው ቢሮው " በማህበራዊ የትስስር ገፆች በሚነዛው በሬ ወለደ ውዥንብር ሳንደናገጥ ስራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን " ሲል አሳውቋል።

" ለረጅም ግዜ ታግሰናል ፤ ከዚህ በኋላ ግን ሁሉም ነገር በህግና ስርዓት መልክ እንዲይዝ እናደርጋለን " ሲል አረጋግጧል።

እስካሁን በተለያዩ ህገ-ወጥ ተግባሮች ተሳተፉ  ናቸው የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተሰምቷል።

እነማን እንደሆኑ በስም የተጠቀሰ ነገር የለም።

ሳምንቱን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ከትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን 3 ከፍተኛ አመራሮች ከሃላፊነት ተነስተው በሌሎች መተካታቸው ሲዘዋወር ነበር።

ከብረታ ብረት ስርቆትና ሌሎች ህገ-ወጥ ተግባራት ጋር በተያያዘም በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ቢነገርም መረጃውን የጊዚያዊ አስተዳደሩና የፀጥታና ሰላም ቢሮ ማረጋገጫ ሊሰጥበት አልቻለም።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia 
Safaricom Ethiopia !

የዛሬው ሜኗችን ላይ ያሉን ስፔሻሎች እነዚህ ናቸው ፤ እስካሁን አላዘዛችሁም?

አሁንም ሳያመልጠን M-PESA Safaricom appን እናውርድ 500ሜ.ባ ኢንተርኔት ዳታ ፓኬጅ እናግኝ!

M-PESA ላይ እንመዝገብ፣ በM-PESA እንገበያይ!

🔗የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያን በዚህ ሊንክ እናውርድ ፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

የቴሌግራም ቻናላችንን እዚህ እንቀላቀል 👉https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC

ስለ አገልግሎታችን ማንኛውንም ጥያቄ ወይም መረጃ  በቴሌግራም   ቻናላችን https://t.me/Safaricom_Ethiopia_PLC 24/7 ማግኘት ይቻላል!

#MPESASafaricom  #FurtherAheadTogether
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (No.7) • “ እኔ 50 ሺህ፣ ጓደኛዬ 30ዐ ሺህ ብር ከፍለን ተለቀናል። በርካታ ተማሪዎች እየተሰቃዩ ነው ” - ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ • “ እኛም 700 ሺህ ላኩ ተብለናል ” - የታጋች ተማሪ ወንድም ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በታጣቂዎች ከታገቱ 10 ቀናት አስቆጥረዋል። ስለታጋቾቹ ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ? ቲክቫህ…
#Update (No.8)

" ባነር አሰርተን ልመና ወጥተናል ገንዘብ ግን እየተገኘ አይደለም " - የታጋች ተማሪ ቤተሰብ

ትምህርት አጠናቀው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ዓመት የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች “ ገብረ ጉራቻ ” የሚባል ቦታ ሲደርሱ መታገታቸው አይዘነጋም።

ተማሪዎቹ የታገቱት ሰኔ 26/2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ገደማ ሲሆን፣ ብዛታቸው በትክክል ባይታወቅም ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ከእገታው ያመለጡ ተማሪዎች በሁለት ታታ አውቶብስ የነበሩ መሆናቸውን በወቅቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ከታጋቾቹ መካከል አንዳንዶቹ ከፍተኛ ብር ከፍለው መለቀቃቸውን መግለጻቸውም ይታወሳል።

የታጋቾቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

የታጋቾቹ ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው የታጋች ቤተሰቦቸ፣ ልጆቻቸው ባለመለቀቃቸው ጭንቀት ላይ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቃሏን ለቲክቫህ የሰጠች አንድ የታጋች እህት አጋቾቹ የጠየቁትን ግማሽ ሚሊዮን ብር ካልተላከላቸው ታጋቾቹን ‘ አንለቅም ’ ማለታቸውን ገልጻ፣ “ ባነር አሰርተን ልመና ወጥተናል ገንዘብ ግን እየተገኘ አይደለም ” ብላለች።

በተጨማሪም እህቷ ፤ ያሉት ታጋች ተማሪዎች ምግብ በወቅቱ እንደማያገኙና ልብስም ስለሌላቸው በብርድ እየተሰቃዩ እንደሆነ እንደገለጸችላት ተናግራለች።

" አጋቾቹ 700 ሺህ ጠይቀውናል " ያለ ሌላኛው የአንዲት ታጋች ተማሪ ወንድም፣ ታጋቿ በስቃይ ውስጥ እንዳለች ቤተሰብ ገንዘቡን ለመላክ አቅም እንዳላገኘ ገልጿል።

" ቤተሰቡ በከባድ ሀዘን ላይ ነው። በተወለድንበት ሀገር ለዛውም ንጹሐን ተማሪ ታግተው ሲሰቃዩ መንግስት ምን እየሰራ ነው ? " ሲል ጠይቋል።

ታጋቾቹን ለማስቀቅ ምን እየሰራ ነው ? ሲል ቲክቫህ የጠየቀው የኦሮሚያ ክልል ስላምና ጸጥታ ቢሮ፣ የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ከዚህ ቀደም የሰጠው መግለጫ እንዳለ ከመጥቀስ ውጪ በጸጥታ ቢሮው በኩል ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም።

ሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማትም ለጉዳዩ ምላሽ ለመስጠተ ፈቃደኛ አልሆኑም።

የኦሮሚያ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ከዚህ ቀደም በሰጡት መግለጫ፣ በ 'ሸኔ ቡድን ታግተው ተወሰዱ' ካላቸው 167 ታጋቾች መካከል የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀው፣ 7 ታጋቾች ብቻ እንደቀሩ አሳውቆ ነበር።

አንድ ከቀናት በፊት ገንዘብ ከፍሎ ከእገታ የተለቀቀ ተማሪ ግን እርሱ ከነበረበት የእገታ ቦታ ብቻ ከ60 በላይ ታጋቾች እንዳሉ ለቲክቫህ ተናግሮ ነበር።

ሌላኛዋ በእገታው ላይ ያለች ተማሪ ባለችበት ጫካ ፣ በርካታ ታጋች ተማሪዎች እንዳሉ እንደተናገረች ቤተሰቦቿ ለቲክቫህ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
" ችግሩ ከአቅማችን በላይ ነው " - መሰቦ ሲሚንቶ

የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ ፤ ለጊዜው ስሚንቶ ማምረት ማቆሙን አሳውቋል።

ፋብሪካው የሲሚንቶ ማምረት ስራ ያቆመው አጋጠመኝ ባለው " የጥሬ እቃ አቅርቦት እጥረት " ነው።

መሰቦ ፥ " ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ሲሚንቶ ለማምረት የምንጠቀምባቸው ጥሬ እቃዎች በተለያዩ ጊዚያት በአግባቡና በወቅቱ ለማግኘት አልቻልንም " ብሏል።

" የተለያዩ ጥሬ እቃዎች ሚገኙባቸው ቦታዎች ከሚኖር ማህበረሰብ ጋር የተፈጠረው ችግር በጊዚያዊነት እና በዘላቂነት ለመፍታት ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላትና የአከባቢው ነዋሪዎች በተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም እስከ አሁን መፍታት አልተቻለም " ብሏል ፋብሪካው፡፡ 

እነዚህ ችግሮች ምን ምን እንደሆኑ በይፋ ከመናገር ተቆጥቧል።

" የተፈጠረው ችግር ከእኔ አቅም በላይ ነው " ያለው መሰቦ ሲሚንቶ ፋብሪካ ችግሩን የሚመለከተው አካል ትኩረት ሰጥቶ መፍትሄ እስኪሰጠው ድረስ ለጊዜው ሙሉ በሙሉ ሲሚንቶ ማምረት አቁሞ በጥገና ስራ እንደሚገኝ አሳውቋል።

#Tigray #Messebo

@tikvahethiopia            
 
#CentralEthiopia

የ11 ዓመት እድሜ ያላትን የገዛ ልጁን የደፈረው አባት 16 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት ተፈርዶበታል።

ድርጊቱ የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል፣ በጉራጌ ዞን፣ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ነው።

ተከሳሽ ሙሂዲን ወራቄ ይባላል።

የግል ተበዳይ (ልጁ) ያለ እድሜዋ በአዲስ አበባ ከተማ በሰራተኝነት ተቀጥራ ትሰራ ነበር።

በኃላም ፤ በቤተሰቡ መበተን ምክንያት በብቸኝነት የሚኖረዉን አባቷ ለመደገፍ ወደ ከዊሶ ወደ ተባለው መንደር ትመለሳለች።

ተከሳሽ ጋብቻ እየመሰረተ ሲፈታ ከሶስት ጊዜ በላይ ትዳር መስርቶ ፍቺ የፈፀመ ሲሆን የደረሱ ልጆቹንም ድሮ የልጅ ልጅ ለማየት በቅቷልም ነዉ የተባለዉ።

" አባቴን ትቼ  የትም አልሄድም " ስትል ከወላጅ አባቷ መኖር የጀመረችዉ ታዳጊ በተደጋጋሚ በገዛ አባቷ ተደፍራለች።

አንድ ቀን በወላጅ አባቷ ጭካኔና የነዉረኝነት ባህሪ የደረሰባትን በደል ሁሉ ለወላጅ እናቷ ትናገራለች።

አንጀቷ የበገነው እናትም ወደ ወረዳዉ ሴቶች ጉዳይ ጽህፈት ቤት አቅንታ ሰዉየዉ ለፍርድ ይቀርብ ዘንድ እገዛ እንዲደረግልኝ ስትል አቤቱታ በማሰማቷ ክስ ሊመሰረት ችሏል።

የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ መከላከል ባለመቻሉ ጥፋተኛ በማለት በ16 ዓመት ከ6 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

መረጃው ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ነው የተገኘው።

Via @tikvahethmagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
#OnlineScam ባለፈው ወር ላይ የላኦ እና የቻይና ፖሊስ በሰሜን ላኦስ ጎልደን ትሪያንግል ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በህገወጥ የጥሪ ማእከል የኦንላይን ማጭበርበር (Online Scam) ተግባር ላይ ተሰማርተዋል ያሏቸውን 280 ቻይናውያንን በቁጥጥር ስር አውለዋል። ግለሰቦቹም ወደ ቻይና ዲፖርት ተደርገዋል። ፖሊስ ግለሰቦቹን በያዘበት ወቅት 460 ኮምፒዩተሮች እና 1,345 ስልኮችን ይዟል። እንዚህ አካላት…
#Update

ሕንድ በማይናማር እንዲሁም ካምቦዲያ በሳይበር ወንጀል / የኦንላይን የማጭበርበሪያ ማዕከላት (Online Scam Centers) ውስጥ ያሉ ዜጎቿን አስወጣች።

ሀገሪቱ በማይንማር፣ ማያዋዲ ' ሽዌ ኮ ኮ '  በሚገኝ የኦንላይን ማጭበርበሪያ ማዕከል ውስጥ የሚገኙ 11 ተጎጂ ዜጎቿን እንዳስወጣች ገልጻለች።

ሕንዳዊያኑ ከማዕከሉ እንዲወጡ የተደረገው በማይናማር ባለስልጣናት እና በአካባቢው ወጣቶችን ከቦታው እንዲወጡ በሚረዱ ሰዎች ርብርብ ነው።

አሁን ላይ እነዚህ ሕንዳዊያን ዜጎች ወደ ሀገራቸው ሕንድ እንዲመለሱ እየተሰራ እንደሆነ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአካባቢው ያገኘው መረጃ ያሳያል።

ከዚህ በተጨማሪ የሕንድ መንግሥት ከካምቦዲያ ባለስልጣናት ጋር በመተባበር በሳይበር ወንጀል / ኦንላይን ማጭበርበር ማዕከላት ውስጥ እንዲሰሩ ሲደረጉ የነበሩ 14 የሕንድ ዜጎችን አስወጥቷል።

በፍጥነት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እየተሰራ ስለመሆኑም ሰምተናል።

ሕንድ በርካታ ወጣቶቿ በማጭበርበሪያ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙባት ሀገር ስትሆን ከዚህ ቀደም መሰል ዜጎቿን የማስወጣት እርምጃ የወሰደች ሲሆን አሁንም ቀጥላለች።

ሌሎች ሀገራት በተመሳሳይ ተጠቂ ናቸው ያሏቸው ዜጎቻቸውን የማስወጣት እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።

በማይናማር፣ ላኦስ፣ ካምቦዲያ ፣ ቻይና ታይላንድ ድንበር፣ ታይላንድ ማይናማር ድንበር ባሉ የማጭበርበሪያ ማዕከላት እጅግ በርካታ የኢትዮጵያ ዜጎችን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ይገኛሉ።

አንዳንድ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ከ300 ሺህ በላይ ሰዎች አሉ (ከተለያዩ ሀገራት)።

በስፍራው የሚገኙት ብዙሃኑ ወጣቶች ናቸው።

ወደዚህ ተግባር የገቡት እራሳቸው ተጭበርበረው ነው / ይህ ማለት እራሳቸውም ተጎጂዎች (ሰለባ) ናቸው።

ደላሎችና ኤጀንሲዎች ወጣቶች 'ወደ ታይላንድ / ወደ ሌላ ሀገር' ለ፦
- ሴልስ
- የማርኬቲንግ
- ለሆቴል እንግዳ ተቀባይ
- ለተቋማት ደንበኞችን ማነጋገር በሚል ነው የሚልኳቸው።

በኃላም ወደ ጎረቤት ሀገራት በመውሰድ የተደረጀ የኦንላይ ማጭበርበር ስራ ላይ እንዲሰማሩ ነው የሚደረገው።

ወጣቶቹ ከሚሰማሩባቸው ተግባራት ዋነኛው ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት በመክፈት ሰዎችን በተለይ ሴትን በወንድ / ወንድ በሴት አስመስለው በማነጋገር ገንዘብ ማጭበርበር ነው።

የታዘዙትን አድርገው ገንዘብ ካላመጡም የከፋ ቅጣት ሊጠብቃቸው ይችላል።

ወጣቶችን እንዲያጭበረብሩ የሚያሰሩ ማፊያዎቹ በቀጠናው እጃቸው ረጅም የሆነ ሰዎች ናቸው።

እጃቸው በረዘመ ማፊያዎች በሚመራው የሳይበር ወንጀል / የኦንላይን ማጭበርበር / ተግባር በየአመቱ እስከ 43.8 ቢሊዮን ዶላር ይዘረፋል።

ስለ ማጭበርበሪያ ስልቶቹ / ሰዎችን በምን መንገድ እንደሚያጭበረብሩ በዚህ ያንብቡ ፦ https://t.me/tikvahethiopia/88986

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#DStvEthiopia

ሁሉንም ታላላቅ ሊጎች ለሁላችንም!

ሁሉንም ወሳኝ ጨዋታዎች ፣ ደማቅ ግጥሚያዎች ፣ የዋንጫ ፍልሚያዎች በዲኤስቲቪ!

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ፣ ቻምፒዮንስ ሊግ ፣ ላሊጋ ፣ ሴሪአን ጨምሮ ከጨዋታ እስከ ትንታኔ ከተጫዋች ብቃት እስከ ቡድን ወኔ ... ሁሉም በዲኤስቲቪ!

እንደየምርጫዎ በሁሉም ፓኬጅ ላይ ኳስ ያለው ዲኤስቲቪ!

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
👇
https://bit.ly/3RFtEvh

#ሁሉምያለውእኛጋርነው
#DStvSelfServiceET
#CHAPA

⚠️በዚህ ዲጂታል ዘመን በረቀቁ ስልቶች በመጠቀም የክፍያ መጭበርበር በተደጋጋሚ እየተከሰተ ነው!
ቻፓ ንግድዎን ከአጭበርባሪዎች በመከላከል ለደንበኛዎችዎ በጣም ምቹ እና ደህንነቱ የተጠበቀ የክፍያ ስርአት ያቀርባል።
➡️ ዘመናዊ የደህንነት ስርዓታችን አጭበርባሪዎችን አስቀድሞ በመያዝ የለፉበት ገንዘብ እንዳይሰረቅ ይከላከላል።
➡️ ፈጣን እና ቀላል የክፍያ ስርዐታችን ያለምንም ተጨማሪ መዘግየቶች ፈጣን እና ውጣውረድ የሌለው ክፍያ ለማድረግ ያስችላል።
እርስዎ ንግድዎ ላይ ያተኩሩ ፣ ቻፓ ክፍያዎችዎን ይቆጣጠራል። ንግድዎን ዛሬውኑ ቻፓ ላይ በማስመዝገብ ክፍያዎትን ያዘምኑ!

🌐ለበለጠ መረጃ ድህረ ገጻችንን ይጎብኙ፡ https://chapa.co/ ወይንም ዛሬውኑ በ 8911 ይደውሉልን።

Website | Instagram | Facebook |LinkedIn |X
የመምህራንና ትምህርት አመራሮች ልዩ የክረምት ስልጠና መቼ ይሰጣል ?

ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ክረምት ይሰጣል የተባለውን ልዩ የመምህራንና ትምህርት አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ጊዜ ይፋ አድርጓል።

በዚህም የመምህራንና ትምህርት አመራሮች ልዩ የክረምት ስልጠና ከሐምሌ 22-ነሐሴ 16/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ታውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር ልዩ ስልጠናው የሚመራበት የአፈጻጸም መምሪያ ለሁሉም አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች ልኳል፡፡

በዚህም መሰረት፦

ሁሉም ሰልጣኝ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም እስከ ቀኑ 6፡00 በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲዎች ይገባሉ፡፡

የትምህርት ቤት አመራሮች ነሐሴ 4/2016 ዓ.ም እንዲሁም መምህራን ነሐሴ 16/2016 ዓ.ም ስልጠና አጠናቀው ከዩኒቨርሲቲዎቹ ይወጣሉ፡፡

ስለሆነም ሁሉም የትምህርት ቢሮዎች በተጠቀሰው መርሐግብር መሰረት ለሰልጣኝ መምህራንና የትምህርት ቤት አመራሮች ጥሪ እንዲያደርጉ ሚኒስቴሩ ለክልል/ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች በላከው ሰርኩላር አሳስቧል።

Via @tikvahuniversity
#US #Egypt

የዴሞክራት ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ ተቀብለው በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የግብፅን አጀንዳ በማራመድና በሌሎች ክሶች ሐምሌ ጥፋተኛ ተባሉ። 

በሴናተሩ ላይ የቀረቡትን ክሶች የተመለከተው የኒውዮርክ ፍ/ቤት በመጪው ጥቅምት ወር የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀጠሮ መያዙ ታውቋል። 

ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ በነበሩበት ወቅት፣ ለዓመታት የግብፅን አጀንዳ በሴኔት ውስጥ ሲያራምዱ እንደነበር ለዚህም ከግብፅ መንግሥት ክፍያ ማግኘታቸውን ዓቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ አረጋግጧል።

የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ  እ.ኤ.አ. በማርች 2020 ገደማ ባለቤቷ ሴናተር ሜኔንዴዝ ከአንድ የግብፅ ጦር ጄኔራል ጋር እንዲገናኙ ፕሮግራም ማዘጋጀቷንና በፕሮግራሙ ላይም ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር ተገናኝተው በወቅቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በግብፅ፣ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ይካሄድ ስለነበረው ድርድር መወያየታቸውን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በወቅቱም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዋነኛ የትኩረት አጀንዳ ተደርጎ ይወሰድ እንደነበር የምርመራ ሰነዱ ይገልጻል።

ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር በተገናኙ በቀጣዩ ወር ውስጥ (በኤፕሪል 2020 ወይም ገደማ)፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ላይ ለሚሳተፉት ለወቅቱ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ፀሐፊና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደብዳቤ መጻፋቸውን ያትታል።

በደብዳቤያቸው መግቢያ ላይም፣ " እኔ ይህንን ደብዳቤ የምጽፈው ግብፅ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን በግድቡ ዙሪያ ያደርጉት የነበረው ድርድር መቋረጥ እንዳሳሰበኝ ለመግለጽ ነው " ማለታቸውን ያስረዳል።

በማከልም፣ " የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በግድቡ ድርድር ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ እጠይቃለሁ "ማለታቸውን የምርመራ መዝገቡ ይጠቅሳል።

እ.ኤ.አ. በ2021 መገባደጃ ላይ የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ አዘውትራ ከምትገናኘው ከግብፅ ጄኔራል ጋር በመነጋገር እሷና ባለቤቷ ሜኔንዴዝ ወደ ግብፅ እንዲጓዙ ፕሮግራም ማመቻቸቷንና ጉዞውም በጥቅምት 2021 መደረጉን ያስረዳል። 

በመጀመሪያ ጉዞው መደበኛ ያልሆነ ወይም ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቁጥጥር ውጭ እንዲካሄድ የታቀደ መሆኑን የሚያለክተው የምርመራ መዝገቡ፣ በኋላ ላይ አንድ የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ባልደረባ በካይሮ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ በማነጋገር ጉዞው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅናና ቁጥጥር የሚደረግበት መደበኛ የኮንግረንስ ልዑክ የሥራ ጉብኝት እንዲሆን ማነጋገሩን ይጠቅሳል።

ነገር ግን ይህ ጥያቄ መቅረቡን ያወቀው የግብፅ ባለሥልጣን እንደዚያ ሊሆን እንደማይችል የሚገልጽ መልዕክት ለናዲን ሜኔንዴዝ መላኩንና ናዲን ሜኔንዴዝም ምልዕክቱን ለሴናተር ሜኔንዴዝ መላኳን በዚህም ምክንያት ሴናተሩና ባለቤታቸው ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅና ውጪ እንደተካሄደ በምርመራ መዝገቡ ተጠቅሷል።

ሜኔንዴዝና ባለቤታቸው ወደ ግብፅ ከተጓዙ በኋላም በካይሮ ከበርካታ የግብፅ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተውና በአንድ ከፍተኛ የግብፅ የስለላ መሥሪያ ቤት ባለሥልጣን የግል መኖሪያ ቤት እራት መብላታቸውን ያስረዳል።

በእነዚህ ወቅቶችም ልዩ መለያ ቁጥር የተከተበባቸው ባለ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 22 የወርቅ ባሮችን (አሞሌዎችን) ከግብፅ መንግሥት በክፍያ (በጉቦ) መልክ ማግኘታቸውን፣ በዚያ ወቅት የገበያ ዋጋ መሠረት አንዱ ወቄት የወርቅ ባር 1,800 ዶላር እንደነበርና ክስ ከተመሠረተ በኋላ በወጣ የፍርድ ቤት የብርበራ ማዘዣ ሁለት የወርቅ አሞሌዎች በመኖሪያ ቤታቸው መገኘቱን የምርምራ መዝገቡ ያስረዳል።

የአሜሪካ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንደገለጸው፣ ሴናተር ሜኔንዴዝ በተለያዩ ጊዜያት ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር መገናኘታቸውን፣ ከእነዚህም መካከል በአሜሪካ የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ሚስጥራዊ ክትትል በተደረገበት በሞርተን ሬስቶራንት ውስጥ ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እራት በመብላት ለግብፅ መረጃ አሳልፈው መስጠታቸውን እንዲሁም ለግብፅ ምቹ ወታደራዊ የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለማስገኘት ማሴራቸውን ይገልጻል።

ሜኔንዴዝ ለግብፅ መንግሥት ራሳቸው ደብዳቤ አዘጋጅተው ከሰጡ በኋላ ይህንኑ ደብዳቤ በመጠቀም በግብፅ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ሌሎች የኮንግረስ አባላት ያላቸውን ሥጋት ለማግባባት እንደተጠቀሙበት የአሜሪካ ፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የክስ ሰነድ ያስረዳል።

በጥቅሉ የአሜሪካ የምርመራ ቢሮ እ.ኤ.አ. በጁን 16 ቀን 2022 ከሜኔንዴዝ ቤት በድምሩ 486,461 ዶላር፣ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 11 የወርቅ አሞሌዎችንና አንድ ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ሁለት የወርቅ አሞሌዎችን በቁጥጥር ሥር አውሏል።

በአጠቃላይ የኒው ጀርሲው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የውጭ መንግሥት ፍላጎትን ለመፈጸም ሥልጣናቸውን መጠቀም፣ ጉቦ መቀበል፣ ማጭበርበር፣ ፍትሕን ማደናቀፍን ጨምሮ በ16 የወንጀል ድርጊቶች የተከሰሱ ሲሆን፣ ባለፈው ማክሰኞ በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ተብለው ተበይኖባቸዋል።

የቅጣት ውሳኔውን ለማስተላለፍ ለመጪው ጥቅም ወር 2017 ዓ.ም. ቀጠሮ የተያዘ ሲሆን፣ ሴናተሩ በትንሹ ከ20 ዓመት በላይ እስር ሊፈረድባቸው እንደሚችል ሲኤንኤንን ጨምሮ የተለያዩ የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

Credit - Reporter Newspaper

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ክብሯት እና ክብሯን የዩክሬን ፕሬዝዳንት ፑቲን ! " - ጆ ባይደን በቀጣዩ የአሜሪካ ምርጫ ዴሞክራት ፓርቲያቸውን ወክለው ይወዳደራሉ ተብለው የሚጠበቁት ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን የጤናቸው ነገር አሳሳቢ ነው እየተባለ ነው። " እርጅናም ተጫጭኗቸዋል፣ በትልልቅ መድረኮች የሚነገሯቸውን ነገሮች እየሳቱ ነው ፤ ስለዚህ ምክትላቸው ይተኳቸውና ከዶናልድ ትራምፕ ጋር ይፎካከሩ " የሚል አስተያየት የሚሰነዝሩ የፓርቲው…
#USA

" ካማላ ሃሪስ ዕጩ ሆነው እንዲቀርቡ ድጋፍ እሰጣለሁ " - ባይደን

ፕሬዜዳንት ጆ ባይደም ከአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ራሳቸውን ማግለላቸውን በይፋ አሳውቀዋል።

ባይደን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እራሳቸውን ከምርጫው እንዲያገሉ ጫና ሲደረግባቸው እንደነበእ ይታወሳል።

ዛሬ ምሽት " ለፓርቲዬ እና ለሀገሬ ጥቅም ሲባል ራሴን ከ2024 ፕሬዝዳንተዊ የምርጫ ፉክክር አውጥቻለው " ሲሉ በይፋ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ባይደን፤ ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ የዴሞክራቶች ዕጩ ሆነው በፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ እንዲቀርቡ ድጋፍ ሰጥተል።

" እኔን ተክተው ካማላ ሃሪስ ለፕሬዝዳንት እንዲወዳደሩ እፈልጋለሁ " ብለዋል።

ከቀናት በፊት የቀድሞው የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ ዕጩነታቸውን በይፋ መቀበላቸው አይዘነጋም

@tikvahethiopia