TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#NGAT

ትምህርት ሚኒስቴር ያዘጋጀው ጊዚያዊ የድኅረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና መርሐግብር፥ ሀገር አቀፍ ፈተናው ነሐሴ 23 እና 24 /2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ያሳያል።

ዘንድሮ ለድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች መግቢያ ስድስት የተለያዩ የፈተና ዓይነቶች እንደሚሰጥ ተሰምቷል።

ፈተናው በሁለት ክፍሎች ተደራጅቶ የሚዘጋጅ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ክፍል የጠቅላላ ዕውቀትን የሚለኩና ሁሉም ተፈታኞች የሚወስዱት ሲሆን፤ ሁለተኛው ክፍል ደግሞ የሙያ ዘርፍን ታሳቢ በማድረግ በስድስት መስኮች የሚዘጋጅ ይሆናል።

ጠቅላላ ዕውቀትን የሚለኩ ጥያቄዎች 70% የሚሸፍኑና የሙያ መስክ ታሳቢ ያደረጉ ጥያቄዎች 30% የሚይዙ መሆናቸውን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ያገኘው መረጃ ያሳያል።

የድኅረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና የአመልካቾች ምዝገባ ከሐምሌ 24 እስከ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም መከናወኑ ይታወቃል።

የተፈታኞች Username እና Password በቀጣይ ቀናት እንደሚገለፅ ይጠበቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
የNGAT ፈተና መቼ ይሰጣል ? ትምህርት ሚኒስቴር ፥ የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እና የፈተና ቀንን አሳውቋል። በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸው እና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣቸው አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል…
#NGAT : የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጥበት ቀን እና ሰዓት ይፋ ተደርጓል።

ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነውን የትምህርት መስኮችና የመግቢያ ፈተና የሚሰጥባቸውን መርሐግብር ከላይ ይመልከቱ።

ፈተናው ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#NGAT : የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጥበት ቀን እና ሰዓት ይፋ ተደርጓል። ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነውን የትምህርት መስኮችና የመግቢያ ፈተና የሚሰጥባቸውን መርሐግብር ከላይ ይመልከቱ። ፈተናው ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። Via @tikvahuniversity
NGAT_EXAM_SCHEDULE_FFF1.xls
33.5 KB
#NGAT : ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1 / 2016 ዓ.ም የሚሰጠው የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የሚሰጥበት ቀንና ሰዓት፣ የመፈተኛ ማዕከላት እና የትምህርት መስኮች

ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘ የመጨረሻ መርሐግብር ከላይ ተያይዟል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
NGAT_EXAM_SCHEDULE_FFF1.xls
#NGAT

የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ለመውሰድ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከልነት የመረጡ ተፈታኞች ብቻ የፈተናው ጊዜ የተለወጠ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን ወደፊት እንደሚያሳውቅ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

በሌሎች የፈተና ጣቢያዎች (ዩኒቨርሲቲዎች) ፈተናውን ለመውሰድ ያመለከቱ በሙሉ፣ ፈተናው በተያዘው ዕቅድ መሰረት ነሐሴ 30/2016 ዓ.ም ከ8:00 ሰዓት ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል፡፡

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
NGAT_EXAM_SCHEDULE_FFF1.xls
#NGAT

የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የማለፊያ ነጥብ 50% እና ከዚያ በላይ እንደሆነ ተገልጿል።

የፈተናው ውጤት ዛሬ ይፋ ሆኗል።

በ2017 ዓ.ም የድኅረ ምረቃ ፕሮግራሞች ለሚማሩ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም መሰጠቱ ይታወሳል።

የተፈታኞች ውጤት ዛሬ ይፉ የሆነ ሲሆን ተፈታኞች የምዝገባ ቁጥር / Username በማስገባት ውጤታቸው በተከታዩ ሊንክ መመልከት እንደሚችሉ ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ውጤት መመልከቻ - https://result.ethernet.edu.et/ngat_result

Via @tikvahuniversity