TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"....ወደ ኋላ እየተመለከቱ ወደፊት መጓዝ አይቻልም እንደሚባለው ሁሉ፤ እኛም የሚመጣውን ብሩህ እና ያማረ ጊዜ በማሰብ ሀገራችንን ከክፋት፣ ከችጋር፣ ከድንቁርና እና ከልመና ለማሻገር ባለመታከት መስራት ብቻ ሳይሆን መትጋት ግዴታችን ነው፡፡ የእኛ ትውልድ #በንግግር የሚያምን፤ በውይይት የሚግባባ፣ ራሱንም ሆነ ወንድሙን የሚያዳምጥ፣ ማዳመጥ ብቻ ሳይሆን በጋራ መፍትሄ የሚፈልግ ትንታግ ትውልድ እንጂ በጥላቻ እርስ በርሱ የሚገፋፋ የሚከፋፈል ከፍ ሲልም የሚገዳደል አይደለም፡፡" #አማኑኤል_ኢቲቻ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AmharaRegion #Gojjam ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋርዱላና ኧሌ ዞኖች ተነስተው ለደን ምንጣሮ ስራ ወደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እያመሩ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ጎዛምን አካባቢ በ " ፋኖ ታጣቂዎች " የተያዙ የቀን ሰራተኞችን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረገ መሆኑን የምልመላና የቅጥር ሂደቱን የፈፀመው " ኒኮቲካ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር አሳውቋል። የታገቱት ሰራተኞች ብዛታ 272…
#Update

" 4 ሚሊዮን ብር ለማስለቀቂያ ከፍለናል ሰነዱ በእጄ አለ፤ ከለቀቋቸው በኃላ ድጋሜ በመያዝ 6 ሚሊዮን ብር ጠይቀዋል " - ቀጣሪ ድርጅቱ

ወደ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለደን ምንጣሮ ስራ በግል ድርጅት ተመልምለው ወደ ስፍራው በአማራ ክልል፣ በምስቅው ጎጃም ፣ ጎዛመን በኩል አቋርጠው ሲጓዙ የካቲት 18/2016 ዓ/ም " በፋኖ ታጣቂዎች " ታገቱ የተባሉ ሠራተኞች እስካሁን ከእገታ አልተለቀቁም ሲል ቀጣሪው ድርጅት ገለጸ።

የቀጣሪው ድርጅት ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሙልጌታ አለነ ፤ ላለፉት 24 ቀናት ታግተው የሚገኙትን 272 #የቀን_ሰራተኞች ጉዳት ሳያገኛቸው ለማስለቀቅ መጋቢት 1 ቀን 2016 ዓ/ም 4 ሚሊዮን ብር በተለያዩ 3 ሰዎች አማካኝነት ክፍያ ፈፅመናል ብለዋል።

አቶ ሙልጌታ ፤ " ገንዘቡን #ተቀበሉን ከዛም ለቀቋቸው ከለቀቋቸው በኃላ እንደገና ጎዛመን የሚባል ቦታ ላይ ለዋናው አስፓልት 5 ኪ/ሜ ሲቀር እንደገና ሌላ ኃይል መልሶ ያዛቸው። ... የውሸት የውሸት ፖለቲካ የእውነት አምላክ ይፍረድልን ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረድልን " ሲሉ ተናግረዋል።

" 4,000,000 ብር (4 ሚሊዮን) ነው #የከፈልናቸው " ያሉት አቶ ሙልጌታ ፤ " የከፈልኩበት ሰነድ በእጄ አለ ፤ በ3 ሰው ስም ነው የገባው። ' አስገባ ' ተባልኩኝ አስገባሁ ተለቀቁ እንደገና ከተለቀቁ በኃላ ሌላ ቡድን ያዛቸውና ለእያንዳንዱ መኪና አሁን 1,500,000 ብር ተጠይቋል ፤ ልጆቹን ለቀይ መስቀል ነው አሳልፈን የምንሰጠው ብለውን እየጠበቅን ነው " ብለዋል።

መጋቢት 1 ተለቀው እና ድጋሚ ተይዘው ከሆነ ከቀናት በፊት ቃለ ምልልስ በሰጡበት ወቅት ይህን ገንዘብ ለአጋቾቹ #መክፈላቸውንና ተለቀው መያዛቸውን ለምን እንዳልተናገሩ ተጠየቀው ፤ " አንደኛ የነበርኩት እዛው አካባቢ ነው ለደህንነቴ አስቸጋሪ ነበር። ሁለተኛ ደግሞ ልጆቹን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረኩ ነበር በዛ የተነሳ ነው " ሲሉ መልሰዋል።

ስራ አስኪያጁ ፤ ሰራተኞቹ #ከእገታው_ተለቀው መሄድ ከጀመሩ በኃላ በድጋሚ በቡድኑ ሌላ ክንፍ የተያዙት እዛው በምስራቅ ጎጃም ፣ ማቻከል ወረዳ አማኑኤል አካባቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ሲጓዙበት የነበረ 4 ተሽከርካሪ ቁልፍም በታጣቂዎች መወሰዱን ገልጸዋል።

6 ሚሊዮን ብር ማስለቀቂያ መጠየቁን አመልክተዋል።

' የአማራ ፋኖ የጎጃም ቃል አቀባይ ' እንደሆኑ የገለጹት ፋኖ ማርሸት ፀሀይ ግን ምንም አይነት የገንዘብ ጥያቄ አላቀረብንም ፤ ገንዘብም አልተቀበልንም ፣ ድርጅቱ ስም ማጥፋት ነው የያዘው ብለዋል።

ፋኖ ማርሸት " ይሄ ኒኮቲካ የሚባለው የኮንስትራክሽን ድርጅት የፋኖን ስም በዓላማ እያጠፋ ያለ ተቋም ነው። ምርኮኞች የተያዙት በ4ኛው ክ/ጦር በሚያስተዳድረው ቀጠና ነው። ክፍለ ጦራችን #አማኑኤል / ማቸከል፣ ጎዛመን እስከ ደ/ማርቆስ እና ልጆቹ አሁን ያሉበትን በረሃ ያጠቃልላል። ስለዚህ በዚህ ቀጠና እስካሉ የኛ ሙርከኞች ናቸው " ብለዋል።

" #ገንዘብ_የጠየቀ_አካል_የለም። ተጭነውባቸው ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም የመጡባቸው የአውቶብሶቹ ባለቤቶች (4 አውቶብሶች) ' አውቶብሶቻችን ስጡን ' ሲሉ  አንሰጥም የሚል መልስ ሲሰጣቸው ' ለፋኖ ገንዘብ እንስጥና ድጋፍ አድርገን አውቶብሶቻችን ይመለሱ ' አሉ እኛ የገንዘብ ችግር የለብንም ፤ ገንዘብ አንጠይቅም አውቶብሶቹ ግን ቀይ መስቀል መጥቶ ልጆቹን ሲረከብ ተጭነው የሚሄዱባቸው ናቸው ብለን አቆይተናል " ብለዋል።

ልጆቹ ከነበሩበትም #እንዳልተንቀሳቀሱ ፣ ኒኮቲካም ሊቀበል እንዳልመጣ ገልጸው ድርጅቱ " የፋኖን ስም እያጠፋነው " ሲሉ ከሰዋል።

" እነዚህ ልጆች ታጋቾች ሳይሆኑ #ምርኮኞች ናቸው። ምርኮኞቹን ደግሞ ለቀይ መስቀል የምናስተላልፍበት ምክንያት ፦
1. እኛ ተንቀሳቃሽ ኃይል ስለሆንን፣
2. ለነሱ የምንመግበውን ምግብ ለወታደራችን ማዋል ስላለብን ፣
3. ዓለም አቀፍ የጦርነት ህግን አክብረን የምንዋጋ የነፃነት ታዋጊዎች / ኃይሎች መሆናቸውን ለማረጋገጥ ነው " ብለዋል።

እስካሁን ቀይ መስቀል እንዳልመጣ በአካል ከመጡ እናስረክባለን ሲሉ ተናግረዋል።

የተያዙት ደግሞ ድርጅቱ እንዳለው " 272 " ሳይሆኑን 246 ብቻ ናቸው ብለዋል።

ኒኮቲካ ኮንስትራክሽን አሁን ጉዳዩ ከእኛ ከአቅማችን በላይ ነው ሲል አሳውቋል።

አቶ ሙልጌታ አለነ ፤ " ለሚመለከተው ሁሉ ስራውን ለሚያሰራን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልም በፅሁፍ አሳውቀናል ምንም መፍትሄ የለም #የድሃ_ልጅ ነው እየተሰቃየ የሚገኘው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የአማራ ህዝብ እውነቱን ብቻ አይቶ ይዳኘን ፣ እነዚህ ወንድም ህዝቦች ናቸው የመጡት ለስራ ነው " ብለዋል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የሰራተኞቹን ጉዳይ እንደሚያውቅ ፣ ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ጋር በመሆን እየሰራበት እንደሆነ ገልጾ ለጊዜው ለታጋቾች ደህንነት ሲባል ከዚህ በላይ አስተያየት እንደማይሰጥ ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከቪኦኤ ሬድዮ /ጋዜጠኛ ዮናታን ዘብዲዮስ ማግኘቱን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia