TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኢትዮጵያን አታዋርዷት‼️

#የዩኒቨርሲቲ_ተማሪዎች እናተ ከሌላው የተሻላችሁ ናችሁ፤ ቦታው ይገባችኃላ ተብላችሁ ነው አሁን ያላችሁበት ቦታ የሄዳችሁት። ዩኒቨርሲቲ የገባችሁት ተምሮ ሀገር ለመቀየር እንጂ እርስ በርስ እየተከፋፈላችሁ እንድትጣሉ አይደለም። ዱላ፣ መሰዳደብ፣ መበሻሸቅ፣ መጠላላት ለማን ይጠቅማል?? ነገ የተሻለ ህይወት እንዲኖራችሁ አትመኙም?? ነገ የድሀውን ቤተሰባችሁን ኑሮ መቀየር አትመኙም?? ነገ ያሻችሁ አማርጣችሁ በልታችሁ፤ ያሻችሁን ገዝታችሁ ለብሳችሁ ዘንጣችሁ መኖር አትፈልጉም?? ልክ እንደ ውጪዎቹ በወጣትነታችሁ መኪና መያዝ፤ ሀገር ማገልገል፤ መሸለም፤ በህዝብ ዘንድ መወደድ አትፈልጉም??

እባካችሁ ፌሮውን፣ ዱላውን #ጣሉት! ይህ ዘመን ችግሮቻችን #በንግግር መፍታት የምንችልበት ነው።

በፈጣሪ እስከመቼ ወደኃላ እንጓዛለን?? ቢያንስ ለትንንሾቹ ልጆች አርአያ ሁኑ እንጂ!

ኢትዮጵያን በአለም ህዝብ ፊት አታዋርዷት!
ዱላውን፣ ፌሮውን ጥላችሁ እስክርቢቶ እና ወረቀት አንሱ፤ ሀገር የሚቀይር ሀሳብ አፍልቁ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
"....ወደ ኋላ እየተመለከቱ ወደፊት መጓዝ አይቻልም እንደሚባለው ሁሉ፤ እኛም የሚመጣውን ብሩህ እና ያማረ ጊዜ በማሰብ ሀገራችንን ከክፋት፣ ከችጋር፣ ከድንቁርና እና ከልመና ለማሻገር ባለመታከት መስራት ብቻ ሳይሆን መትጋት ግዴታችን ነው፡፡

የእኛ ትውልድ #በንግግር የሚያምን፤ በውይይት የሚግባባ፣ ራሱንም ሆነ ወንድሙን የሚያዳምጥ፣ ማዳመጥ ብቻ ሳይሆን በጋራ መፍትሄ የሚፈልግ ትንታግ ትውልድ እንጂ በጥላቻ እርስ በርሱ የሚገፋፋ የሚከፋፈል ከፍ ሲልም የሚገዳደል አይደለም፡፡

እኛ የዛሬ ተመራቂዎች ይህንን ታሪካዊ አደራ በሚገባ ተረድተን በመተባበር ፣ በመደጋገፍ ፣ ራሳችንን በእውቀት በማሳደግ ሀገራችንን በቅንነት ለማሻገር ከሚተጉት ጋር ሁሉ ወኔና ጉልበት በመሆን አደራችንን እንድንወጣ እየለመንኩ ፤ በሄዳችሁበት ቦታ ሁሉ መልካም ነገር የግጠማችሁ በማለት ንግግሬን በዚሁ እቋጫለሁ፡፡" አማኑኤል ኢቲቻ/የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ፕሬዘዳንትና የዘንድሮ ተመራቂ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"....ወደ ኋላ እየተመለከቱ ወደፊት መጓዝ አይቻልም እንደሚባለው ሁሉ፤ እኛም የሚመጣውን ብሩህ እና ያማረ ጊዜ በማሰብ ሀገራችንን ከክፋት፣ ከችጋር፣ ከድንቁርና እና ከልመና ለማሻገር ባለመታከት መስራት ብቻ ሳይሆን መትጋት ግዴታችን ነው፡፡ የእኛ ትውልድ #በንግግር የሚያምን፤ በውይይት የሚግባባ፣ ራሱንም ሆነ ወንድሙን የሚያዳምጥ፣ ማዳመጥ ብቻ ሳይሆን በጋራ መፍትሄ የሚፈልግ ትንታግ ትውልድ እንጂ በጥላቻ እርስ በርሱ የሚገፋፋ የሚከፋፈል ከፍ ሲልም የሚገዳደል አይደለም፡፡" #አማኑኤል_ኢቲቻ

@tsegabwolde @tikvahethiopia