TIKVAH-ETHIOPIA
1.4M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ጋምቤላ⬆️

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የተለያዩ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችን ከአንድ ተጠርጣሪ ግለሰብ ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ቾል ኩን ለኢዜአ እንደገለጹት ህገ ወጥ መሳሪያዎችን ከትናንት በስቲያ በጋምቤላ ከተማ በቁጥጥር ሥር ማዋል የተቻለው #ከላሬ ወረዳ ወደ #ጋምቤላ ከተማ ለማስገባት ሲሞክር ነው።

በፖሊስ ከተያዙት የጦር መሳሪያዎች መካከል አራት ሽጉጦች፣ አንድ ታጣፊ ክላሽ፣ አንድ ሺህ 133 የተለያዩ ዓይነት ጥይቶች ይገኙበታል።

ከህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎች ጋር ከ20 ሺህ 600 ብር በላይ #ገንዘብ ፖሊስ አብሮ በቁጥጥር ሥር መዋሉንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

በተጠርጣሪው ላይ በተደረገው ማጣራትም የጦር መሳሪያዎቹን ወደ #መሀል ሀገር የማስገባት እቅድ እንደነበረውም ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በተጠርጣሪ ግለሰቡ ላይ ማስረጃ የማሰባሰብና የማጠራት ሥራ እየተካሄደ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ “የምርመራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ይላካል” ብለዋል።

ክልሉ በተለይም ከደቡብ ሱዳን ጋር በስፋት በድንበር የሚዋሰን ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በርካታ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ወደ ክልሉ እየገባ መሆኑን የገለጹት ኮሚሽነሩ፣ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህዝቡ #ተሳተፎውን እንዲያጠናክር
ጠይቀዋል።

ህግ ወጥ የጦር መሳሪዎች በሀገሪቱ ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ችግሮች በመገንዘብ ኮሚሽነሩ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር በጋራ #ለመከላከል ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

©ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia