TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.36K videos
198 files
3.63K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ሲሰራጭ በነበረው ቪድዮ ዙርያ ነገ መግለጫ ይሰጣል ተብሏል።

Via #EliasMeseret
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚር አብይ ነገ ጠዋት🛫እስራኤል ያመራሉ!

የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጋዜጠኞች በላከው መረጃ የኢትዮጵያው መሪ ከእስራኤሉ ጠ/ሚር ቤንጃሚን ኔታናያሁ እና ከፕሬዝደንቱ ሬኡቨን ሬቭሊን ጋር ሰኞ ይገናኛሉ።

Via #EliasMeseret
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የሀሳብ ማዕድ" #EliasMeseret #AddisAbeba

PHOTO: TIKVAH FAMILY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EliasMeseret Tikvah Eth family!

የምናከብረው እና የምንወደው የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ ለቤተሰባችን የተመረጡ መረጃዎችን ማቅረብ ይጀምራል።

ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት የተመረጡ መረጃዎችን ለቤተሰባችን ከማቅረብ በተጨማሪ ወጣቶች፣ ተማሪዎች፣ መላው የማህበረሰቡ በሀሰተኛ ዜናዎች እንዳይደናገር እና እንዳይታለል አሁን እያደረገ ካለው በተጨማሪ ጊዜውን መሥዕዋት በማድረግ የአቅሙን አስተዋፆ ያደርጋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ "የሀሰተኛ ዜናዎች መድሃኒት" የሆነው ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት በማህበራዊ ሚዲያዎች በትዊተር፣ ፌስቡክ፣ ቴሌግራም ላይ ባሉት ትክክለኛ የግል ገፆቹ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል። በሀሰተኛ መረጃዎች እንዳይታለሉ ለበርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች፣ ለቴሌቪዥን እና ሬድዮ ጣቢያዎች፣ ለጋዜጠኞች ባለውለታም ጭምር ነው።

ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ አክቲቪስቶችን እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን በማሰባሰብ ለውይይት በአንድ ጠረጴዛ እንዲቀመጡ ለማድረግ እያደረገ ያለውን ስራም በመላው የቤተሰባችን አባላት የሚታወቅ ነው።

ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ የቤተሰባችን አባል በመሆኑ ትልቅ ደስታ ይሰማናል፤ ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ ደግሞ የመረጣቸውን መረጃዎች ለቤተሰባችን ከመፃፍ በተጨማሪ፣ ማህበረሰቡን እንዲሁም እዚህ ለተሰባሰብነው ከ442,000 በላይ ለምንሆነው የቲክቫህ ቤተሰቦች ስለማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራም ይሰራል።

Tikvah Eth family!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EliasMeseret #TikvahFamily

የሀሰተኛ ዜናዎች መድሃኒት "ኤልያስ"!

የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰባችን አባል የሆነው ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ነገ ከምሽቱ 12:00-1:00 ለናተ ለውድ ቤተሰቦቻችን የተመረጡ መረጃዎችን ያደርሳችኃል።

STOP FAKE NEWS!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EliasMeseret #TikvahFamily

የቲክቫህ ቤተሰብ አባልና ዓለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ዛሬ ከምሽቱ 12:00-1:00 ድረስ የተመረጡ መረጃዎችን ለናተ ለውድ ቤተሰቦቻችን ያደርሳል!

መልካም ምሽት!

@tikvahethiopiaBot👈አስተያየት መቀበያ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EthioTelecom #EliasMeseret

ዛሬ ለበርካታ ደቂቃዎች ኢንተርኔት የተቋረጠበትን ምክንያት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ለAssociated Press ጋዜጠኛው ኤልያስ መሰረት ተናግረዋል፦

"በመጀመርያ ለኢንተርኔት መቋረጡ ይቅርታ እንጠይቃለን። እኛ ሁል ግዜ የኔትወርክ ለውጥ የምናደርገው ብዙ ሰው ኢንተርኔት በማይጠቀምበት ሰአት ለሊት ላይ ነው። ዛሬ ላይ የተከሰተው የኢንተርኔት መቋረጥ ግን በእኛ ቁጥጥር ስር የነበረ አይደለም፣ አቅደነውም የነበረ አይደለም። በፋይናንስ ተቋሞቻችን ላይ ሊደርስ የነበረ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል INSA ኔትወርኩን ለማቋረጥ ተገድዶ ነበር። እኛም መቋረጡን ለደንበኞቻችን ለመንገር ግዜ አልነበረንም፣ ጉዳዩ ጊዜ የሚሰጥ አልነበረም። ለጥቂት ደቂቃ በማቋረጥ ጥቃቱን ለመከላከል ይቻላል ተብሎ የተወሰደ እርምጃ ነው። ከ INSA ጋር እየተነጋገርን ነው የምንሰራው። ዛሬ ግን ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ችግር አጋጥሟቸው የነበረ ይመስለኛል። አሁን ጉዳዩ ላይ እየተነጋገርን ነው።"

@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣ...

በ ሀገር ዓቀፍ ደረጃ በተደረገ ቅኝት አድራሻቸው የማይታወቁና ተጭበርብረው የተሰሩ 27 የምግብ ዓይነቶች ገበያ ላይ እየዋሉ መሆኑን ተገልጿል። የአምራች አድራሻቸው የማይታወቁና ተጭበርብረው ገበያ ላይ ከሚገኙ የምግብ አይነቶች ውስጥ፡-

የምግብ ዘይት ዝርዝር፦
-ንጹህ የኑግ ዘይት፣
-ኢዛና ዘይት፣
-ጣና ዘይት፣
-ኦሊያድ ዘይት፣
-ስኬት የተጣራ ዘይት፣
-በቅሳ የምግብ ዘይት፣
-አሚን የምግብ ዘይት፣
-ቀመር የምግብ ዘይት፣
-ሎዛ የምግብ ዘይት፣
-ዘመን የኑግ እና የለዉዝ ዘይት፣
-ዘቢብ ቃህ የምግብ ዘይት፣

የለውዝ ቂቤ ዝርዝር፦
-ማኢዳ የለዉዝ ቅቤ፣
-ሮዛ ክሬሚ ለዉዝ ቅቤ፣

ቪምቶ ዝርዝር፦
-ዳና ቪንቶ
-ቪንቶ

የምግብ ጨው ዝርዝር፦
-አዋሽ የገበታ ጨዉ፣
-ሳራ እና ኑስራ ጨዉ፣
-ሴፍ የገበታ ጨዉ (በተለያየ እሽግ)፣
-ሽናጉ የገበታ ጨዉ፣
-ወዛቴ አዮዳይዝድ ጨዉ፣
-ቃና የገበታ ጨዉ፣
-አስሊ የገበታ ጨዉ፣

ማር ዝርዝር፦
-ሲሳይ ንጹህ ማር እና ቅቤ አቅራቢ፣
-ወለላ ማር፣

የከረሜላ ዝርዝር፦
-ካርቶንስ ካንዲ ፍሩትስ፣
-ሊዛ ሎሊፖፕ፣
-ክሬሚ ሎሊፖፕ፣

(የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣ)

#ሼር #share

#EliasMeseret
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
አሳዛኙ የአዲስ አበባ ቆሬ አካባቢ አደጋ፦

[ከሸገር ኤፍ ኤም 102.1]

- አደጋው የደረሰው 5:30 አካባቢ ከብስራተ ገብርኤል ወደ ጀሞ ሲሄድ የነበረና አጠና የጫነ IVECO ግልባጭ መኪና ቆሬ ዓለም ሰላም ድልድይ ውስጥ ባሉ ቤቶች ላይ ወድቆ ነው።

- በአደጋው የሶስት ሰዎች ህይወታቸው አልፏፋ። በአንድ ሰው ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል። ከሟቾች ውስጥ የ11 ወር ህፃንና ንፍሰጡር ሴትም ይገኛሉ። ነፍሰጡር ሴቷ የ25 ዓመት ወጣት እና የህፃኑ አክስት እንደሆነች ተገልጿል።

- የ28 ዓመት ወጣት የሆነው አሽከርካሪም በአደጋው ህይወቱ አልፏል።

- የአደጋው መንስኤ እየተጣራ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

#ShegerFM #EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ቢሾፍቱ ውስጥ ኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የያዘው ሰው ተገኝቷል በሚል በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ከኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ተሰምቷል።

የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ሊያ ታደሰ ለጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት በሰጡት መረጃ ከቻይና ከተመለሰች 12 ቀን የሆናት እና የቫይረሱን የሚመስሉ ምልክቶች ያሳየች አንድ ግለሰብ ቢሾፍቱ ውስጥ ተገኝታ እንደነበር አንስተው ግለሰቧ ወደ ለይቶ ማቆያ ተወስዳ፣ ምርመራ ሲደረግላት ነፃ ሆና ተገኝታለች ብለዋል።

#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለሚመለከተው አካል፦

ይህ አዲስ አበባ ከተማ ወሎ ሰፈር አደባባዩ ላይ ያለዉ የድልድይ አካል ቢወድቅ ከስር ባሉ በተላላፊዎች ላይ ጉዳት ስለሚያስከትል ይታሰብበት!

#DrivinginAddis #EliasMeseret

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
42ኛው የካራማራ የድል በዓል የመታሠቢያ ቀን!

የዛሬ 42 አመት ተስፋፊው የመሀመድ ዚያድባሬ ኃይል ካራማራ ላይ አከርካሪው ተሠበረ። በውጤቱም በምስራቅ 700 ኪ.ሜ እንዲሁም በደቡብ 300 ኪ.ሜ ዘልቆ በወረራ ይዞት ከነበረው የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ተጠራርጎ ወጣ ።

ወድቃ የነበረችው ሰንደቃችንም ዳግም ተነስታ በክብር ከፍ አለች።

ይህን በአባቶቻችን ደምና አጥንት እና በእናቶቻችን ደጀንነት ያገኘነውን የመላ ኢትዮጵያውያን የጋራ ደማቅ የድል ታሪክ ለማክበር ድሉ በተገኘበት ዛሬ የካቲት 26 ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በኢትዮ ኩባ ወዳጅነት ፓርክ (በትግላችን ሐውልት) ላይ ለማክበር ዝግጅት ተጠናቋል።

በዝግጅቱ ላይ፦

- በጦርነቱ ወቅት በአመራር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች (ጀኔራሎችን ጨምሮ ) ሌሎች መስመራዊ መኮንኖች

- ለድሉ መገኘት ቁልፍ ሚና የተወጡ የጀግናው አየር ኃይላችን አብራሪዎች

- በጦርነቱ የተሳተፉ ባለሌላ ማዕረግተኛ ወታደሮች (የጀብድ ሜዳይ የተሸለሙ ጭምር )

- በጦርነቱ ቤተሠቦቻቸውን ያጡ የኩባ ተማሪዎችና የህፃናት አንባ ልጆች

- ለኢትዮጵያ ድጋፍ በመስጠት በጦርነቱ የተሳተፉ ሀገራት አምባሳደሮች /ተወካዮቻቸው እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ።

በመሆኑም ታሪክና ሀገር ወዳድ የሆናችሁ ዜጎች በዕለቱ በቦታው ላይ ተገኝታችሁ የመታሠቢያ በዓሉን በድምቀት እንድታከብሩ ተጋብዛችሗል።

የበዓሉ ጊዜያዊ አስተባባሪዎች፣ ኮረማሽ የጉዞ ማህበር ከማይክ መላከ የኢትዮ- ኩባ ወዳጅነት ማህበር እና በኢትዮጵያ የኩባ ኤምባሲ ጋር በመተባበር።

#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዶክተር ሊያ ታደሰ፦

"የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች [UAE] ውስጥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሁለት ኢትዮጵያውያን የኤምሬትስ ነዋሪ ሲሆኑ በዛ ሀገር ለአመታት የኖሩ እና በቅርቡም ጉዞ ያላደረጉ መሆኑን አረጋግጠናል"

#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ኢትዮጵያዊው የAP ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረትን ጨምሮ 25 የሚሆኑ ከ25 ሀገራት የተውጣጡ ጋዜጠኞች ከነገ ጀምሮ በአሜሪካ 3 ግዛቶች በመገኘት የሀገሪቱን ምርጫን እንዲዘግቡ ፕሮግራም ተይዞ የነበረ ቢሆንም "ለጥንቃቄ" ሲባል ፕሮግራሙ በስድስት ወር እንደተራዘመ ተሰምቷል።

#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፓይለቶች ማህበር አባላት የዛሬ አመት በአውሮፕላን አደጋ ህይወታቸውን ላጡ ጓደኞቻቸው የማስታወሻ ፕሮግራም አካሂደዋል።

#EliasMeseret #EliasGJ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ኢትዮጵያ፦

- በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው International Community School (ICS) ከነገ ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 11 ትምህርት ቤቱን በኮሮና ቫይረስ ስጋት ምክንያት እንደሚዘጋ አስታውቋል።

- የኮሮና ቫይረስ በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል ትክክለኛውን መረጃ በመጠቀም ረገድ ከመንግስት ተቋማትና ግል ማህበራዊ ሚዲያ አንቀሳቃሾች ጋር ውይይት ተደርጓል።

- የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በዛሬው እለት በኮሮና ቫይረስ ቅድመ ጥንቃቄ ዙሪያ ከኢትዮዽያ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አባል ቤተ እምነቶች ጋር ምክክር አድርጓል።

- የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የጤና ባለሙያዎች ለማሰልጠን፣ አስፈላጊ ቁሳቁሶችን ለሟሟላት እና ለህክምና ማዕከላት የሚውል 30 ሚሊዮን ብር አፅድቋል።

- ዛሬ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዓለም የጤና ወረርሽኝ በሆነው የኮሮና ቫይረስ ላይ ምክክር አድርጓል። ዶክተር ሊያ ታደሰ እና ዶክተር ኤባ አባተ በወቅታዊ የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ እና ኢትዮጵያ ቫይረሱ እንዳይገባ እያደረገች ባለው ቅድመ ጥንቃቄ ዙሪያ ለምክር ቤቱ አባላት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

#ጤናሚኒስቴር #አዲስፎርቹን #EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopiaBOT
ከአሉባልታዎች እና ሀሰተኛ መረጃዎች ተጠበቁ!

ይህ በቀኝ በኩል ያለ ፎቶ ለቀናት "አንድ ቻይናዊ ዱከም ያለው ኢንደስትሪ ዞን ውስጥ የኮሮና ቫይረስ ይዞት ያሳያል" እየተባለ በብዛት ሼር ሲደረግ ነበር።

ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ከኢንደስትሪ ዞኑ የኮሚኒኬሽን ክፍል መረጃ ተቀብሎ እንዳሰራጨው ከሆነ ግለሰቡ የልብ ህመም አጋጥሞት እንጂ ከቫይረሱ ጋር የተያያዘ አልነበረም። ግለሰቡ አሁን ጤና ተመልሶ በግራ በኩል ያለው ፎቶ ላይ ይታያል።

#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር ሀገር አቀፍ መረጃዎች፦

- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሥራ እንዲውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለግሰዋል።

- ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል። በተጨማሪ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ማኔጅመንት፣ አመራር እና ሠራተኞች ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ለተመሳሳይ አላማ አበርክተዋል።

- የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 14, 000 ሰራተኞቹን በጊዚያዊነት ከስራ አሰናብቷል። ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱት በአሜሪካና በአውሮፓ ገበያዎች የምርቶቹ ዋነኛ ተቀባይ የነበሩት ድርጅቶች በኮሮና ምክንያት የገበያ ፍላጎታቸው እየተቀዛቀዘ በመምጣቱ ነው።

- መከላከያ ሰራዊት ነገ በአዲስ አበባ የቫይረሱን ስርጭትን ለመግታት የሚያግዙ መልዕክቶችን የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በሄሊኮፕተር ይበትናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በማርሽ ባንድ የታጀበ የማንቂያ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡

- አልማ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል።

#DW #etv #EliasMeseret #fbc #ena
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia