TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.36K videos
198 files
3.63K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በአዳማ ከተማ 1 በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው ተገኘ!

በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አንድ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ ሰው መገኘቱን በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የተቋቋመው ግብረ ሃይል ገለጸ፡፡

ከግለሰቡ ጋር ንክኪ የነበራቸው 24 ሰዎች ተለይተዋልም ነው የተባለው። ግብረ ሃይሉ በህብረተሰቡና በተቋማት የሚታየው ቸልተኝነት አሁንም #አሳሳቢ ነው ብሏል።

#FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር ሀገር አቀፍ መረጃዎች፦

- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሥራ እንዲውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለግሰዋል።

- ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል። በተጨማሪ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ማኔጅመንት፣ አመራር እና ሠራተኞች ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ለተመሳሳይ አላማ አበርክተዋል።

- የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 14, 000 ሰራተኞቹን በጊዚያዊነት ከስራ አሰናብቷል። ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱት በአሜሪካና በአውሮፓ ገበያዎች የምርቶቹ ዋነኛ ተቀባይ የነበሩት ድርጅቶች በኮሮና ምክንያት የገበያ ፍላጎታቸው እየተቀዛቀዘ በመምጣቱ ነው።

- መከላከያ ሰራዊት ነገ በአዲስ አበባ የቫይረሱን ስርጭትን ለመግታት የሚያግዙ መልዕክቶችን የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በሄሊኮፕተር ይበትናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በማርሽ ባንድ የታጀበ የማንቂያ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡

- አልማ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል።

#DW #etv #EliasMeseret #fbc #ena
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADDISABABA

የፐብሊክ ሰርቪስ ድርጅት ከረቡዕ ጀምሮ ተሳፋሪዎች የአፍ መሸፈኛ ጭንብል በአስገዳጅነት እንዲጠቀሙ ሊደርግ መሆኑን አስታውቋል።

ከረቡዕ ጀምሮ የአፍ መሸፈኛ ጭምብል የማይጠቀሙ ተሳፋሪዎችን እንደማይጭንም ገልጿል።

በተጨማሪ የትራንስፖርት እጥረትን ለመፍታት የመጫን አቅምን ከአስገዳጅ የአፍ መሸፈኛ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ወደ 43 የሚያድግ ይሆናል ተብሏል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

በአዲስ አበባ ከመጭው ዓርብ (ሚያዚያ 30/2012 ዓ/ም) ጀምሮ የሚኒባስ ተጠቃሚዎች የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብሎችን #በአስገዳጅነት እንዲጠቀሙ ሊደረግ መሆኑ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ባለስልጣን እንዳለው ተሳፋሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት ለመጠቀም ሲንቀሳቀሱ ጭምብሎችን መጠቀም ይኖርባቸዋል ብሏል። ባለስልጣኑ ተሳፋሪዎች ያለ አፍ መሸፈኛ ጭምብል ታክሲ መጠቀም አይችሉም ሲል ገልጿል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#FicheChambalala

ፊቼ ጫምባላላ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመከላከል በአደባባይ እንዳይከበር የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች ወስነዋል። የሲዳማ የሀገር ሽማግሌዎች/አያንቶዎች በዓሉ ግንቦት 12 እና 13 ተከብሮ እንዲውልም ቀን ቆርጠዋል።

ወረርሽኝ፣ ጦርነት እና ርሀብ እንዲሁም የታላቅ ሰው ህልፈት ሲከሰት ፊቼ ጫምበላላ በዓል በአደባባይ የማይከበር መሆኑ ታሪካዊ አመጣጥ ያለው መሆኑን የገለፁት አያንቶዎቹ በዓሉ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመከላከል ዘንድሮ አደባባይ እንዳይከበር ወስነዋል፡፡

በኮሮና ወረርሽኝ አማካኝነት ሊከሰት የሚችለውን ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባት በታላቁ (ሶሬሳ) ጉዱማሌም ሆነ በወረዳ እና በቀበሌ ደረጃ በዓሉን በአደባባይ ማክበር የማይቻል እንደሆነም የሀገር ሽማግሌዎች ገልፀዋል።

#fbc
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ATTENTION

የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ኤባ አባተ የኮሮና ቫይረስ ከተገኘባቸው 365 ሰዎች 56ቱ የውጭ ሃገር የጉዞ ታሪክም ሆነ ከበሽታው ተጠቂ ግለሰብ ጋር ንክኪ #ያልነበራቸው መሆናቸውን አሳውቀዋል።

ከእነዚህ ውስም 48 በመቶ ' በአዲስ አበባ ከተማ ' ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች በመሆናቸው ህብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባው አሳስበዋል።

#FBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19Ethiopia

በአምቦ ዩኒቨርስቲ የተቋቋመው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ማእከል ተመርቆ ስራ ጀምሯል። ይህ ላብራቶሪ በቀን እስከ 1 ሺህ ናሙናዎችን መመርመር እንደሚችል ተገልጿል።

በተጨማሪ የአርባ ምንጭ የኮቪድ-19 ምርመራ ማዕከል ምርመራ ጀምሯል። ማዕከሉ በቀን እስከ 400 የሚደርሱ ናሙናዎችን የመመርመር አቅም አለው። ማዕከሉ ለጋሞ፣ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ኮንሶ ፣ እና ከደራሼ ዞኖች፣ ቡርጂ፣ አማሮ እና አሌ ልዩ ወረዳዎች ለሚመጡ ናሙናዎች የ24 ሰዓታት የምርመራ አገልግሎት ይሰጣል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GERD

የታላቁ ህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት የግድቡን ተፈጥሯዊ የግንባታ ሂደት በጠበቀ መልኩ የሚከናወን መሆኑን የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዛሬ በሰጡት መግለጫ መናገራቸውን #FBC ዘግቧል።

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ሲሰራጭ የነበረው የውሃ ሙሌቱን የሚያሳዩ የሳተላይት ምስሎች ትክክለኛና እውነተኛ መሆናቸውንም ለሚዲያዎች አረጋግጠዋል።

ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ፣ ሱዳን እና ግብጽን ጨምሮ ሌሎች የአፍሪካ ሃገራት የተሳተፉበት የ11 ቀን ውይይት በተወሰኑ ነጥቦች ላይ በ3ቱ ሀገራት መካከል መግባባት ላይ መደረሱን አስረድተዋል።

ከዚህ ባለፈ ግን በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ በኢትዮጵያ ዘላቂ ጥቅም ላይ ተፅዕኖ የሚኖራቸው ነጥቦች ላይ ጥንቃቄ ማድረግ በማስፈለጉ ልዩነት እንደነበርም በሰጡት መግለጫ አንስተዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GERD

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ መሪዎች በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ዛሬ ይመክራሉ።

የዛሬው ውይይት ሰኔ 19 የተካሄደውን ውይይት ተከትሎ የሚካሄድ መሆኑ ነው የተገለፀው።

የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር እና የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ስሪል ራማፎሳ በቪዲዮ ኮንፈረንስ የሚካሄደውን ስብሰባ ይመሩታል ተብሎ ይጠበቃል።

በስብሰባው ላይ የቢሮው አባላት የሆኑት የዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ኬንያ እና የማሊ መሪዎች እና ተወካዮችም ይሳተፉበታል።

የአፍሪካ ህብረት ዓባላት ቢሮ በዛሬው ስብሰባው ኢትዮጵያ ፣ ሱዳንና ግብፅ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ሲያደርጉት በነበሩት የሶስትዮሽ ድርድር የደረሱበትን ደረጃ የሚመለከት ይሆናል - #FBC

@tikvahethiopiaBot @tsegabwolde
ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ዝርዝር ፦

የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከዛራ የካቲት 27 እስከ መጋቢት 30 ቀን 2013 ዓ/ም የሚቆይ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

በዚሁ መሰረት የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

- ቤንዚን በሊትር 25 ብር ከ 86 ሳንቲም፥

- ኤታኖል ድብልቅ ቤንዚን በሊትር 25 ብር ከ 36 ሳንቲም፥

- ነጭ ናፍጣ በሊትር 23 ብር ከ18 ሳንቲም፥

- ኬሮሲን በሊትር 23 ብር ከ18 ሳንቲም፥

- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 20 ብር ከ27 ሳንቲም፥

- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 19 ብር ከ78 ሳንቲም፥

- የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 38 ብር ከ65 ሳንቲም ይሆናል ብሏል ሚኒስቴሩ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የተደረገውን የዋጋ ማስተካከያ በተመለከተ በዝርዝሩ የተካተቱ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫን ለማሳወቅ የህዝብ ማስታወቂያ ዛሬ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።

በዚሁ መሰረት #በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎች በሚገኙ ማደያዎች ተግባራዊ ይደረጋል ብሏል። #FBC

@tikvahethiopia
"...ከአንድ ቤተሰብ 5 እና 6 ሰዎች የሞቱ አሉ" የጭና ነዋሪዶች

በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ "ጭና" ተብሎ በሚጠራ ቦታ የህወሓት ታጣቂዎች ከአንድ መቶ በላይ ንፁሃንን መግደላቸውን ነዋሪዎች አሳውቀዋል።

ግድያው የተፈጸመው አካባቢው በህወሓት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር በቆዩባቸው ቀናት ውስጥ ሲሆን ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ህጻናት በተፈጸመባቸው ጥቃት ተገድለዋል።

አንድ የጭና አጎራባች ቀበሌ አብጥራ፣ ነዋሪ የሆኑ አስማረ ታፈረ የተባሉ ግለሰብ ለቢቢሲ በሱጡህ ቃል ፥ ነሐሴ 12 ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ በአካባቢው የህወሓት ታጣቂዎች በመግባት ተኩስ መክፈታቸውንና ውጊያ መካሄዱን ጠቁመዋል።

ጦርነቱ እስከ ነሐሴ 29 ድረስ መካሄዱን የገለፁ ሲሆን፥ እስካሁን ድረስ ተገድለው የተገኙ 119 ሰዎች በጦርነቱ ያልተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው ብለዋል።

"ይህ ቁጥር መሞታቸው ታውቆ ለቅሶ እየተለቀሰ ያለ ነው" በማለት ይህ ቁጥር ከዚህ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ተናግረዋል።

እንደነዋሪው ገለፃ፥ ከአንድ ቤተሰብ 5 እና 6 ሰዎች ሞተዋል።

ዛሬ ደግሞ ሌሎች የአይን እማኝ ነን ያሉ ነዋሪዎች በጭና ተክለሃይማኖት ቀበሌ የተገደሉ ንፁሃ ከ200 በላይ መሆናቸውን አመልክተዋል። 193 የሚሆኑት በጭና ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን መቀበራቸውን አመልክተዋል።

ከ20 በላይ የሚሆኑት በዲያ ጊዮርጊስ መቀበራቸውን አሳውቀዋል።

አሁንም ተጨማሪ አስከሬን እየተገኘ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን የደረሱበት ያልታወቀ እንዳሉም ነው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

More : https://telegra.ph/CHEENA-09-08

Source : #Reuters #BBC #FBC

@tikvahethiopia
#መቐለ #ራያ #አክሱም #ዓዲግራት

ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ስድስት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በማቅናት ምልከታ ሊያደርግ ነው፡፡

በግጭቱ ምክንያት ሥራ ያቋረጡትን አክሱም፣ ራያ፣ አዲግራት እና መቐለ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ አገልግሎት ለመመለስ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።

እስካሁን ባለው ሁኔታ አክሱም እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ዳግም ወደ አገልግሎት በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ ንግግር መጀመሩን በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር እና መሰረተ ልማት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለፋና ተናግረዋል።

በቀጣይም ከመቐለ እና አዲግራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ግንኙነት እንደሚጀመር ኃላፊው አመላክተዋል፡፡

በአክሱም ከተማ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ተከትሎ፤ ስድስት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ከሰኞ ጀምሮ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ዋናውን ግቢ ጨምሮ አድዋ እና ሽረ ግቢዎችን በስፍራው በመገኘት ምልከታ ያደርጋል ብለዋል፡፡

ቡድኑ ተቋማቱ በሰው ኃይል፣ በመሰረተ ልማት፣ በቤተ ሙከራ፣ በኔትወርክ፣ በመኝታና መማሪያ ክፍሎች፣ በማስተማሪያ ሆስፒታል፣ በቤተ መጻሕፍት እና ሌሎች አገልግሎቶች ዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችለውን ሁኔታ ይመለከታል፡፡ #FBC

@tikvahuniversity
#ATTENTION

" በድርቅ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተ የፀጥታ ችግር ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ ተጋልጠዋል " - የአማሮ ልዩ ወረዳ

• " ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ ነው " - የቡርጂ ልዩ ወረዳ

በደቡብ ክልል አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ136 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።

#አማሮ

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የአማሮ ልዩ ወረዳን ዋቢ አድርጎ ባሰራጨው መረጃ ፤ በልዩ ወረዳው ለረጅም ጊዜ ዝናብ ባለመጣሉ በ22 ቀበሌዎች ድርቅ ተከስቷል፡፡

በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በልዩ ወረዳው ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።

በድርቁ ከ3 ሺህ 500 በላይ የቤት እንስሳት በድርቁ ምክንያት መሞታቸው ተገልጿል።

በልዩ ወረዳው የተከሰቱ የፀጥታ ችግሮች የህብረተሰቡን ተጋላጭነት እንዳባባሱት ልዩ ወረዳው አመልክቷል።

በድርቁ እና ለረጅም ጊዜ በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ በርካት ሰዎች ለአደጋ መጋለጣቸው ተገልጿል።

የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በተለያየ ጊዜ እርዳታ ቢያደርግም በልዩ ወረዳው ከከተከሰተው ጉዳት አንፃር ድጋፉ በቂ አለመሆኑን ልዩ ወረዳው አሳውቋል።

#ቡርጂ

የቡርጂ ሶያማ ልዩ ወረዳ በበኩሉ በልዩ ወረዳው በተከሰተው ድርቅ 83 ሺህ 528 ዜጎች አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አሳውቋል።

በልዩ ወረዳው ከ30 ሺህ በላይ እንስሳት መሞታቸውም ተጠቁሟል።

ከምግብ እጥረት ጋር በተያያዘ ህፃናትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ለረሀብ፣ ለበሽታ እና ለሞት እየተዳረጉ መሆኑ ተገልጿል።

ከክልሉ መንግስት በተጫማሪ የአካባቢው ተወላጆች እና ግለሰቦች እርዳታ ቢያደርጉም በልዩ ወረዳው ከተከሰተው ድርቅ አንፃር የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት በቂ አለመሆኑ ተመላክቷል።

በድርቅ የተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት እና መልሶ ለማቋቋም ረጂ ድርጅቶችን ጨምሮ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረታቸውን ወደ ልዩ ወረዳው እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።

#ኮንሶ

በኮንሶ ዞን በተከሰተ ድርቅ ከ800 ሺህ በላይ ዜጎች ለአስቸኳይ ድጋፍ መዳረጋቸውን ዞኑ አሳውቋል።

ለተከታታይ 5 ዓመት የተከሰተው የዝናብ መዘግየት እና እጥረት ባስከተለው ድርቅ ለአስቸኳይ ድጋፍ የተዳረጉት 822 ሺ 526 ዜጎቻችን ናቸው።
 
የተከሰተው ድርቅ ዜጎች ላይ አስከፊ ጉዳት ከማድረሱ በፊት በችግር ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች ድጋፍ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።

Credit : #FBC #SRTA

@tikvahethiopia
" ... መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉት 10 የከባድ ውንብድና ፍርደኛ ታራሚዎች ናቸው " - ቃሊቲ ማረሚያ ቤት

ከቃሊቲ ማረሚያ መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ነበሩ የተባሉ ታራሚዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰምቷል።

ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት  መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉር የከባድ ውንብድና ወንጀል ፍርደኛ ታራሚዎች መሆናቸው ተነግሯል።

ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጥበቃና የደኅንነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ድሪባ ሰንበታ ለኤፍ ቢ ሲ የሰጡት ቃል ፦

" ትናንት ሌሊት 10 ሰዓት ከ30 ላይ መሬት ቆፍረው ሊያመልጡ ሙከራ ያደረጉ 10 የከባድ ውንብድና ፍርደኛ ታራሚዎች ላይ ማረሚያ ቤቱ ባደረገው ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ለማምለጥ ሙከራ ካደረጉ ፍርደኞች መካከል ከዚህ በፊት #አምልጦ ከጣልያን ሀገር በኢንተርፖል ተይዞ የመጣ ታራሚ ይገኝበታል።

ሌሎችም በተደጋጋሚ ከጤና ጣቢያ ፣ከመኪና ላይ ጭምር ለማምለጥ ሞክረው የተያዙ ፍርደኞች አሉ።

ማረሚያ ቤቱ  ዛሬ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ቀጠሮ የነበራቸው ታራሚዎችን አጅቦ በማቅረብ መደበኛ ስራውን ሲሰራ ውሏል።

ታራሚዎቹ  ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠቡ ተገቢ የሆነ  የክትትልና የቁጥጥር ስራው ይቀጥላል። "

Credit : #FBC

@tikvahethiopia
Audio
#ይደመጥ

- የዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ጉዳይ እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ስጋት

- የተማሪዎች ምረቃ እና የመውጫ ፈተና መያያዝ

- የሬሜዲያ ፈተና ተፈታኞች ጉዳይ

- የትምህርት ጥራት እና ፈተና

እነዚህን እና ሌሎች ጉዳዮች የተዳሰሰበት " ፋና ቴሌቪዥን " ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር አረጋ ይርዳው ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ ከላይ በድምፅ ፋይል ተያይዟል።

ፋይሉ 13 MB ነው።

Credit - #FBC

@tikvahethiopia
Audio
#ይደመጥ

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ የ " መውጫ ፈተና " ን በተመለከተ ለፋና ቴሌቪዥን የሰጡት ዝርዝር ማብራሪያ ከላይ ተያይዟል።

በዚህ ማብራሪያ ፦

- የፈተናውን አይነት

- የውጤት አገላለፅ

- የጤና ተማሪዎች ፈተና / የሙያቸው እና የመውጫው

- እንደው ተማሪዎች ፈተናውን ባያልፉ መቼ እና የት ? እስከ ስንት ጊዜ ድረስ ድጋሚ መውሰድ እንደሚችሉ

- የፈተናው ደህንነት

- የተማሪዎች ምረቃ / ውጤት ያላመጡ ምረቃ ላይ ይሳተፋሉ በሚለው ላይ የትምህርት ሚኒስቴር አቋም ምን እንደሆነ
.
.
. ሌሎችንም ምላሽ የሚፈልጉ ጉዳዮችን በዝርዝር ለመላው ተፈታኝ ተማሪዎች፣ ለተማሪ ወላጆች፣ ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል አስረድተዋል።

ፋይሉ 28.2 MB ነው።

Credit : #FBC

@tikvahethiopia
#ExitExam

ከቀጣዩ አመት ጀምሮ በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ የሚተገበረው አስገዳጅ መመሪያ ምን ይላል ?

(የትምህርት እና ስልጠና ባለስልጣን)

" ከቀጣዩ ዓመት 2016 ዓ/ም ጀምሮ እያንዳንዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለመውጫ ፈተና ከሚያስቀምጣቸው ተማሪዎች በየትምህርት መስኩ ቢያንስ 25 በመቶዎቹ ማለፍ ይጠበቅባቸዋል።

የግል ተቋማቱ 25 በመቶ ተፈታኞቻቸውን ማሳለፍ ካልቻሉ የትምህርት ፕሮግራሙ #ይሰረዛል

በተጨማሪም የትምህርት ተቋማቱ ለማስተማር የሚመዘግቧቸውን ተማሪዎች የማሳወቅ ግዴታ አለባቸው። "

NB. ዘንድሮ በተሰጠው የዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተናውን ከወሰዱ 72 ሺህ ተማሪዎች ውስጥ የማለፊያ ውጤት ያመጡት 12,422 ወይም 17.2 በመቶ ብቻ ናቸው።

Credit : #FBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ከ 'አፍሪካ ህብረት' የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ በ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር የምዝበራ ሙከራ የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ የጠየቁት ዋስትና ውድቅ ተደርጓል። ጥያቄውን ውድቅ ያደረገው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው። ከምዝበራ መኩራው ጋር በተያያዘ የተከሰሱት ፦ 1ኛ. ቀሲስ በላይ መኮንን፣ 2ኛ. በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ…
#Update

እነ ቀሲስ በላይ ማረሚያ እንዲወርዱ ታዘዘ።

ከአፍሪካ ሕብረት ሒሳብ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር የምዝበራ ሙከራ ጋር ተያይዞ የተከሰሱት እነ ቀሲስ በላይ መኮንን ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ ፍርድ ቤት አዟል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ተከሳሾች ማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ አዟል።

ዛሬ ፦
1ኛ ቄስ በላይ መኮንን፣
2ኛ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው ኢያሱ እንዳለ ወ/መስቀል፣
3ኛ በኮሚሽን ሥራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ ጃፋር ችሎት ቀርበው ነበር።

4ኛ አለምገና ሳሙኤል ዲንሳ
5ኛ የኒሞና ንግድ ሥራ ኃላ.የተ.የግል ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አበራ መርጋ ተስፋዬ ዛሬም ፍርድ ችሎት #አልቀረቡም

ችሎት የቀረቡ ከ1ኛ - 3ኛ ተከሳሾች የወንጀል ድርጊት መፈጸማቸውንና አለመፈጸማቸውን የማረጋገጫ ጥያቄ በፍ/ ቤት ተጠይቀው " ወንጀሉን አልፈጸምንም " ሲሉ የዕምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።

ዐቃቤ ሕግ ምስክሮች እንዲሰሙለት ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ፍ/ቤቱ የምስክሮችን ቃል ለመስማት ለሰኔ 26 እና 27/2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ፖሊስ ፦
° 4ኛ ተከሳሽ ይኖሩበታል የተባለው ቦታ የፀጥታ ችግር እንዳለ ገልጾ፤
° 5ኛ ተከሳሽ በአድራሻቸው አለመገኘታቸውን ገልጾ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው በጽሑፍ ጠይቋል።

ፍርድ ቤትም ፖሊስ 4ኛው ተከሳሽ ያሉበት ቦታ የፀጥታ ችግር ስለመኖሩ ማረጋገጫ እንዲያቀርብ አዟል።

5ኛው ተከሳሽ የወረዳው ነዋሪ መሆናቸው ወይም አለመሆናቸውን ከወረዳው ማረጋጋጫ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

#FBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቤት ኪራይ ? የአከራይ ተከራይ አዋጅ ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የቤት ተከራዮች " ኪራይ ጨምሩ ካለዚያ ለቃችሁ ውጡ " እየተባሉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በተለይ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩና ቃላቸውን የሰጡን ተከራዮች ፥ አከራዮቻቸው በአንድ ጊዜ ከፍተኛ የኪራይ ብር እንዲጨምሩ ያን የማያደርጉ ከሆነ አስወጥተዋቸው ለሌላ ሰው እንደሚያከራዩ እንደነገሯቸው ገልጸዋል።…
#AddisAbaba

" ... የቤት አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ ነው " - ቤቶች ልማትና አስተዳደር

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ቢሮው ከሰኔ 1/2016 ዓ/ም ጀምሮ በ120 ወረዳዎች ምዝገባ እየተከናወነ እንደሆነ ገልጿል።

በቀሪ የ15 ቀናት ጊዜ ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ወረዳዎች በማቅናት ምዝገባ እንዲያካሂዱ አሳስቧል።

አከራዮች የውል ስምምነቱን ሳይፈጽሙ እስከ 3 ወር ድረስ ከቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ ይደረጋል ተብሏል።

ይህንን ስራ ብቻ የሚያከናውን ቡድን መቋቋሙንም ቢሮው ገልጿል።

የውል ምዝገባው ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ በምሽት ጭምር እየተሰጠ እንደሆነ ያመለከተው ቢሮው ፥ " የተሰጠው የምዝገባ ጊዜ በቂ በመሆኑ የቀን ጭማሪ ላይኖር ይችላል " ሲል አሳውቋል።

ቢሮው በመግለጫው ከመጋቢት 24 ጀምሮ የሚደረግ የቤት ኪራይ ጭማሪ እና ውል ማቋረጥ ክልክል እንደሆነ እና ተቀባይነትም እንደሌለው አመልክቷል።

መንግስት ጥናት በማድረግ በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ እንደሚሆን አስገንዝቧል።

#FBC
#AddisAbaba #HousingDevelopmentandAdministration
#AddisAbaba

@tikvahethiopia