TIKVAH-ETHIOPIA
1.42M subscribers
55.2K photos
1.38K videos
199 files
3.7K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አጫጭር ሀገር አቀፍ መረጃዎች፦

- የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ሥራ እንዲውል የአንድ ወር ደመወዛቸውን ለግሰዋል።

- ሼህ ሁሴን አሊ አላሙዲ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝን ለመግታት የ120 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገዋል። በተጨማሪ የሚድሮክ ቴክኖሎጂ ግሩፕ ማኔጅመንት፣ አመራር እና ሠራተኞች ከ10 ሚልዮን ብር በላይ ለተመሳሳይ አላማ አበርክተዋል።

- የሀዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ 14, 000 ሰራተኞቹን በጊዚያዊነት ከስራ አሰናብቷል። ሰራተኞቹ ከስራ የተሰናበቱት በአሜሪካና በአውሮፓ ገበያዎች የምርቶቹ ዋነኛ ተቀባይ የነበሩት ድርጅቶች በኮሮና ምክንያት የገበያ ፍላጎታቸው እየተቀዛቀዘ በመምጣቱ ነው።

- መከላከያ ሰራዊት ነገ በአዲስ አበባ የቫይረሱን ስርጭትን ለመግታት የሚያግዙ መልዕክቶችን የያዙ በራሪ ወረቀቶችን በሄሊኮፕተር ይበትናል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ በማርሽ ባንድ የታጀበ የማንቂያ ቅስቀሳ ያደርጋል፡፡

- አልማ የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስታውቋል።

#DW #etv #EliasMeseret #fbc #ena
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከ7,600 በላይ ታራሚዎች እንዲፈቱ ተወስኗል!

የአማራ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ስርጭትን ለመከላከል በሚል ከ7,600 በላይ ታራሚዎችን በይቅርታ እንዲፈቱ ወስኗል።

ከእስር በይቅርታ እንዲፈቱ የተወሰነላቸው፦

- የሚያጠቡ እናቶች፣
- የአመክሮ ጊዜያቸው አንድ ዓመት የቀራቸው፣
- ቀላል ወንጀል ፈፅመው ጊዜያቸው አንድ ዐመት የቀራቸው፣
- የሌላ አገር እስረኛ ዜጎች ናቸው።

#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#RUSSIA

ሩሲያ በአንድ ቀን ብቻ 9,623 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ። አብዛኞቹ በዋና ከተማዋ #ሞስኮ የሚኖሩ ናቸው። ይህ ቁጥር ወረርሽኙ ሩሲያ ከደረሰ በኋላ ከተመዘገቡት ሁሉ ከፍተኛው ነው።

በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት 57 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በመላ አገሪቱ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 1,222 ማሻቀቡን ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተቋቋመው ኮሚቴ አስታውቋል።

የሞስኮ ከተማ ከንቲባ የሆኑት ሰርጌይ ሶብያኒን የከተማው ነዋሪዎች ራሳቸውን በመኖሪያ ቤታቸው ለይተው እንዲያቆዩ ተማፅነዋል።

በኮሮና ቫይረስ በጽኑ የታመሙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባው እጅግ የከፋ ደረጃ አለመድረሱን ገልጸዋል። ሁኔታው ከከፋ በሞስኮ ከተማ ለመንቀሳቀስ የሚሰጥ ፈቃድ ሊቀነስ እንደሚችልም ከንቲባው ገልጸዋል።

በሞስኮ ከተማ ነዋሪዎች ከመንግሥት ልዩ ፈቃድ ካላገኙ በቀር ከቤታቸው መውጣት የሚችሉት ዕቃ ለመሸመት፣ ውሾቻቸውን ለማንሸራሸር እና ቆሻሻ ለመጣል ብቻ ነው።

#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopi
አጫጭር መረጃዎች ፦

- ዋይት ሐውስ፤ የአሜሪካ መንግሥት ጤና አማካሪ የሆኑት ዶክተር አንቶኒ ፋውቺ ምክር ቤት ቀርበው እንዳይመሰክሩ አግዷል። ዶክተር ፋውቺ፤ ትራምፕ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን የመከቱበት መንገድ ትክክል ነው ወይስ አይደለም በሚለው ላይ ነበር እንዲመሰክሩ የታሰበው - #BBC

- በትናንትናው ዕለት የሩሲያ የግንባታ ሚኒስትር ብላድሚር ያኩሼቭ በኮሮና ተይዘው በሆስፒታል ሕክምና መከታተል መጀመራቸውን አረጋግጠዋል። ምክትላቸው ዲሚትሪ ፎልኮቭም በኮሮና መያዛቸውን መስሪያ ቤታቸው አረጋግጧል - #DW

- በደቡብ ኮሪያ ባለፉት 24 ሰዓት 6 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ስድስቱም (6) ከውጭ የገቡ ናቸው።

- በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት 802 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል ፤ ዛሬ ሪፖርት የተደረገው ኬዝ ከየካቲት 30 በኃላ የተመዘገበ ዝቅተኛው ቁጥር ነው።

- በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት የ276 ሰዎች ሞት ሲመዘገበ 2,588 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሪፖርት ተደርጓል።

- በቻይና ባለፉት 24 ሰዓት 1 ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙን ሪፖርት አድርጋለች። ዛሬ በሀገሪቱ ሞት ሳይመዘገብ አምስተኛ ቀኑን ይዟል።

- FDA ለኢቦላ በሽታ የሚውለውን ሬምዴሲቬር የተባለውን መድኃኒት ለአስቸኳይ ጊዜ የኮቪድ-19 ህክምና እንዲውል ፈቅዷል። ይህ ጸረ ቫይረስ የሆነው መድኃኒት በኮቪድ-19 በጽኑ ታመው ሆስፒታል የሚገኙ ሰዎችን ለማከም ይውላል። የአሜሪካ ምግብና መድኃኒት አስተዳደር ኮሚሽነር የሆኑት ስቴፈን ሃን 'ይህ የኮቪድ-19ን ለማከም ዕውቅና የተሰጠው የመጀመሪያው መድኃኒት ነው' ብለዋል - #BBC

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝ ሳቢያ 15 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ዕርዳታ ጠባቂ ሊሆኑ እንደሚችሉ የፋይናንስ ሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ መናገራቸው DW ዘግቧል።

ሚኒስትሩ እንዳሉት በዚህ ሳቢያ በአገሪቱ ዕርዳታ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን ቁጥር በአጠቃላይ ወደ 30 ሚሊዮን ያሻቅባል።

መንግስት የኮሮና ወረሽኝን ለመከላከል ያቋቋመው የምኒስትሮች ኮሚቴ በትናንትናው ዕለት ባደረገው እና ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በመሩት ውይይት ለዚህ ብቻ ኢትዮጵያ 1.4 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልጋት ገልጸዋል።

የኮሮና ወረርሽኝን ለመቋቋም ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ፣ ከዓለም የገንዘብ ድርጅት፣ ከአውሮፓ ኅብረት፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ብሪታኒያ እና ቻይና 2.1 ቢሊዮን ዶላር ዕገዛ መጠየቋን አቶ አሕመድ ተናግረዋል። ከዚህ ውስጥ አንድ ቢሊዮን ዶላር በቅርቡ ለኢትዮጵያ ሊሰጥ እንደሚችል ጠቁመዋል።

በትናንትናው ዕለት የዓለም የገንዘብ ድርጅት (IMF) ኢትዮጵያ የኮሮና ወረርሽኝን ጫና ለመቋቋም የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ የ411 ሚሊዮን ዶላር ዕርዳታ አጽድቋል። የዓለም ባንክ በበኩሉ 750 ሚሊዮን ዶላር የበጀት ድጋፍ ሊሰጥ እንደሚችል የፋይናንስ ሚኒስትሩ አስረድተዋል - #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#CHINA

ቻይና የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መነሻን የሚመረምሩ ዓለም አቀፍ አጥኚዎችን አሁን ወደ ሀገርዋ እንደማትጋብዝ አስታውቃለች።

በጄኔቫ የቻይና አምባሳደር እንዳሉት ቻይና አጥኚዎቹን የምትጋብዘው ቻይና በኮሮና ቫይረስ ላይ ድል ከተቀዳጀች በኋላ ነው ብለዋል።

አምባሳደር ቼን ሹ ሀገራቸው አሁን ቅድሚያ የምትሰጠው ወረርሽኙን ማሸነፍ እና የቫይረሱን ጉዳይ ፖለቲካዊ ለማድረግ የሚሰነዘሩ ትርጉም የሌላቸው ውንጀላዎችን መቋቋም ላይ መሆኑን አስረድተዋል።

የዓለም የጤና ድርጅት በበኩሉ የቫይረሱን ምንጭ ለማጣራት በሚካሄደው ምርመራ ላይ ለመሳተፍ የቻይናን #ግብዣ እየተጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።

ቻይና ግብዣውን መቼ ልታቀርብ እንደምትችል የተጠየቁት ሊቼን ሹ በአሁኑ ወቅት ቅድሚያ ሊሰጣቸው በሚችሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ተናግረው ፤ ይህን ለማድረግ ደግሞ ትክክለኛውን ድባብ እንፈልጋለን ብለዋል - #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#AtoAknawKawza

በደቡብ ክልል እስከ 12 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች በኮቪድ - 19 ቫይረስ ሊጠቁ ይችላሉ ሲል የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ #አስጠንቅቋል

የቢሮው ሃላፊ አቶ አቅናው ካውዛ እንዳሉት የከፋ የተጋላጭ ሁኔታ አመልካች እንደሚያሳየው አሁን በበሽታው ዙሪያ የሚያታየውን 'የጥንቃቄ ጉድለት' መቅረፍ ካልተቻለ በክልሉ 60 በመቶ የሚሆነው ነዋሪ በቫይረሱ ሊጠቃ ይችላል።

📹#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ማሳሰቢያ!

የሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በሲዳማ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በነገው እለት የሚከበረውን ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል በዓል በየቤታቸው አንዲያከብሩ የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አሳሰበ።

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር መሳፍንት ሙሉጌታ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በአገራችን በተለይም በሀዋሳ ከተማ በተህዋሲው የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመር በመምጣቱ ህብረተሰቡ ንክኪ ሊያስከትል ከሚችል መሰባሰብ ሊቆጠብ ይገባል ብለዋል።

በነገው እለት (ሐምሌ 19) የሚከበረው ዓመታዊ የቅዱስ ገብርኤል በዓልም የእምነቱ ተከታዮች በየቤታቸው አንዲያከብሩት ከእምነቱ የሃይማኖት አባቶች ጋር ከስምምነት ላይ መደረሱን ኮሚሽነር መሳፍንት ተናግረዋል።

አገሪቱ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ ትገኛለች ያሉት ኮሚሽነሩ ህብረተሰቡ የወጣውን አዋጅ በማክበር ራሱን ፣ ቤተሰቡንና ማህበረሰቡን ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል - #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopiaOfficial
ችሎት!

ዛሬ ፍርድ ቤት የኢ/ር ይልቃል ጌትነትን ጉዳይ ተመልክቷል።

የዛሬው ቀጠሮ መርማሪ ፖሊስ ባለፈው በነበረው ቀጠሮ ተጠርጣሪዎችን ከወንጀሉ ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለብቻ ነጥሎ ለማቅረብና የደረሰበትን አጠቃላይ ሁኔታ ለፍርድ ቤት ለማሳወቅ ነው።

መርማሪ ፖሊስ ሰራዋቸው ያለው ስራ ፦

- ተጨማሪ ምስክሮችን ሰምቻለሁ፣ከወንጀሉ ጋር የተያዙ እቃዎቻቸውን ለምርመራ ለፌደራል ፖሊስና ለብሄራዊ ደህንነት ልኪያለሁ ውጤት እየጠበኩ ነው ብሏል።

- የንብረት ግምት እንዲላክ ፣ የአስክሬን ምርመራ ሪፖርት እንዲላክልኝ ለሚመለከታቸው አካላት ልኪያለሁ ብሏል ፤ እነዚህ ስራዎች ስለሚቀሩኝ 14 ቀን ይሰጠኝ ብሏል።

የኢንጂነር ይልቃል ጠበቃ አዲሱ ጌታነህ ፦

ኢንጂነር ይልቃል ከወንጀል ጋር ያላቸው ግንኙነት ፣ በምን ሁኔታ፣ እንዴትና መቼ እንደተፈፀመ ፖሊስ እንዲያቀርብ ነበር የታዘዘው።

የ14 ሰው ህይወት አልፏል ለዛም ውጤት እጠብቃለሁ ፣ ንብረት ወድሟል ከማለት ያለፈ ተለይቶ የተሳትፎ ደረጃቸው ስላልተገለፀ ለ27 ቀናት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ ሲያደርግ ነበር ተጨማሪ ጊዜ አያስፈልግም መዝገቡ ተዘግቶ #በነፃ ይለቀቁ ብለዋል።

ፍርድ ቤት ፦

- የተጠርጣሪ ጠበቃን አቤቱታ ሰምቶ ፣ መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን ጥያቄ ተመልክቶ ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ አስፈላጊነው ፣ አይደለም የሚለውን ለመወሰን ለሐምሌ 24 ቀጠሮ ሰጥቷል #DW

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TIGRAY

"...አሁን የመጣው የአንበጣ መንጋ ታይቶም አይታወቅም" - አቶ ክንደያ ግደይ (የትግራይ አርሶ አደር)

የበረሀ አንበጣ መንጋ በትግራይ ክልል ካሉት 7 ዞኖች 4ቱን ወሯል።

በ29ኝ ወረዳዎች 79ኝ ቀበሌዎች የሚገኝ ሰብልና የተፈጥሮ ሀብት በአንበጣው ጉዳት ደርሶበታል።

አስተያየታቸው ለDW ከሰጡ ገበሬዎች መካከል የ70 ዓመት እድሜ ያላቸው አቶ ክንደያ ግደይ ለDW ተከታዩን ብለዋል ፦

"ልጅ እያለሁ መኮኒ ፣ ማይጨው እና ወጅራት በአጠቃላይ የሸፈነ ትልቅ የአንበጣ መንጋ መጥቶ አስታውሳለሁ ፤ ይህ 60 ዓመታት ያለፈው ታሪክ ነው ፤ እንደኔ እንደኔ አሁን የመጣው ግን ታይቶም አይታወቅም።"

ከትግራይ ክልል ግብርና ቢሮ በተገኘው መረጃ በክልሉ ካለ አጠቃላይ በሰብል የተሸፈነ መሬት 77,000 ሄክታር የሚሆነው በአንበጣ መንጋ ተወሯል።

በተለይም በዚህ ሁለት ሳምንት የአንበጣ መንጋው በስፋት እየተስፋፋ ይገኛል።

አምና በአንድ ዓመት ውስጥ ወደ ትግራይ የገባው የአንበጣ መንጋ ብዛት 18 ሲሆን ዘንድሮ ግን ከመስከረም ወዲህ ባሉ ቀናት ብቻ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አንበጦች የያዘ 21 መንጋ ወደ ክልሉ ገብቷል።

አንበጣው እስካሁን በትግራይ ውስጥ አጠቃላይ በቁጥር ተለይቶ ያልታወቀ ጉዳት በግብርና ምርት ላይ ማድረሱን ከ #DW ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GERD

ለ7 ሳምንታት ተቋርጦ የቆየው በኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን መካከል የሚደረገው የታላቁ ህዳሴ ግድብ ድርድር ነገ እንደሚቀጥል የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ዛሬ አሳውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ፥ “በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ሥር የሚደረገው ድርድር መቀጠል የ3ቱ አገሮች መሪዎች በታላቁ የኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ ከሰላማዊ እና አግባቢ መፍትሔ ለመድረስ ያላቸውን ቁርጠኝነት ይጠቁማል" ብለዋል። #DW

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ኦነግ በምርጫ 2013 ይሳተፋል ?

ትላንት በተጠናቀቀው የመጀመሪያው ዙር የእጩዎች ምዝገባ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) አንድም እጩ አላስመዘገበም።

የኦነግ ጊዜያዊ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ በቴ ኡርጌሳ ፥ ኦነግ ምንም የእጩ ምዝገባ አለማድረጉ በምርጫው ላለመሳተፉ ጉልህ ማሳያ ነው ብለዋል።

አቶ በቴ፥ "... በእኛ በኩል በተደጋጋሚ ስንገልፅ እንደነበረው ቢሮዎቻችን ፣ ዋና ፅ/ቤቶቻችን ጨምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መሆኑ ፣ ነፃ እንቅስቃሴ እንደድርጅት መታገዱ ፣ አመራርና አባሎቻችን ያለህግ አግባብ መታሰራቸው ምርጫ ላይ በምናደርገው ተሳትፎ ላይ ትልቅ ተፅእኖ አላቸውና እነዚህ ችግሮች ሳይፈቱ መሳተፍ እንደማንችል ስንገልፅ ነበር ፤ በዚህ ሁኔታ እጩ ማስመዝገብ አልቻልንም ስለዚህ በምርጫ ሂደቱ ተሳታፊ አይደለንም" ብለዋል።

በኦሮሞ ነፃነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ እስከ ቀጣዩ ጠቅላላ ጉባኤ ከኃላፊነታቸው እንደተነሱ ከዚህ ቀደም የተነገረላቸው አቶ ቀጄላ መርዳሳ (የኦነግ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ) በበኩላቸው ፓርቲው ለ7 እና 8 ወር ችግር ላይ ስለነበር እጩ ለማቅረብ አስቸጋሪ እንደበር ገልፀዋል።

አቶ ቀጄላ ፥ ፓርቲው በጠቅላላ ጉባኤ የውስጥ ችግሮቹን ፈቶ በወጥ አመራር በምርጫ 2013 ለመሳተፍ እጬዎችን ለማስመዝገብ በተለየ ሁኔታ ጊዜ እንዲራዘምለት ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቅርበው ምላሽ እየተጠባበቁ መሆኑን አሳውቀዋል።

#EthiopiaElection2013 #DW #OLF
https://telegra.ph/Oromo-Liberation-FrontABO-03-05
#AGOA : ኢትዮጵያ በ "AGOA" በኩል ያላት ተጠቃሚነት ላይ አሜሪካ በቅርቡ ውሳኔ ላይ እንደምትደርስ ካትሪን ታይ (የንግድ ተወካይ) ተናግረዋል።

ኃላፊዋ በይፋዊ መንገድ እና በግብረሰናይ ድርጅቶች በኩል የሚደርሱን መረጃዎች አበረታች አይደሉም፤ በኢትዮጵያ እየታየ ያለው ሰብዓዊ ቀውስ ነው ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

የጠ/ሚ ፅ/ቤት ፕሬስ ሴክሬተሪያ ቢልለኔ ስዩም፥ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች የተፈጠረውን ሰብዓዊ ቀውስ በአፋጣኝ መፍትሄ እንዲያገኝ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።

ቢልለኔ፥ " ሰብዓዊ ቀውስ AGOA እድል ከፈጠረላቸው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ሴቶች የስራ እድል በመንጠቅ አይገታም እንደውም ያባብሰዋል" ብለዋል።

ባለፈው ነሃሴ ወር ላይ አሜሪካ፥ በኢትዮጵያ እየተፈፀሙ ነው ያለችው የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች መፍትሄ የማያገኙ ከሆነ በAGOA ያለቀረጥ ምርቶቿን ለአሜሪካ ገበያ የማቅረብ እድሏን እንደምታጣ ገልፃ ነበር።

ሮይተርስ ኢትዮጵያ በ2020 (እኤአ) 237 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጡ ሸቀጦችን ያለቀረጥ በAGOA በኩል ለአሜሪካ ገበያ ማቅረቧን የሀገሪቱ መንግስት መረጃ ያሳያል ብሏል።

የጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ ከፍተኛ አማካሪ እና የኢትዮጵያ የንግድ ተደራዳሪ የሆኑት ማሞ ምህረቱ ኢትዮጵያን በAGOA በኩል ያላትን እድል ማሳጣት ማለት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ሰራተኞች እንደሚጎዳ ለፎርየን ፖሊሲ በፃፉት የግል አስተያየት ላይ ገልፀዋል።

AGOA ምንድነው?

African Growth and Opportunity Act (AGOA) የግብይት ስርዓት ነው፤ ይህ የግብይት ስርዓት የተወሰኑ የብቃት መስፈርቶችን የሚያሟሉ ከሳሃራ በታች የሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ሸቀጦችን ያለቀረጥ ለአሜሪካ ገበያ እንዲሸጡ የሚፈቅድ ነው። #DW

@tikvahethiopia
#ኤርትራ

ኤርትራ የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ቤርቦክን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረን አውሮፕላንን ከአየር ክልሏ ማስወጣቷ ተነግሯል።

የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌላ ባየርቦክ ትላንት እንዳስታወቁት፤ ወደ ጂቡቲ ሲጓዝ የነበረው የጀርመን መንግስት አውሮፕላን ያለ እቅድ ሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዱን ገልጸለዋል።

ይህ የሆነ በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማለፍ ፍቃድ ባለማግኘቱ እንደሆነም አስታውቀዋል።

ሚኒስትሯ በ3 የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ለ3 ቀናት ጉብኝት ለማድረግ በጉዞ ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ጉብኝታቸውም ጂቡቲ ነበረች።

ሚኒስትሯ ፤ ያለ እቅድ በሳዑዲ አረቢያ ለማረፍ መገደዳቸው በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ያለውን አለመረጋጋት ያመለክታል ብለዋል።

ትላንት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ሄደው ለማደር የተገደዱት ሚኒስትሯ ዛሬ በጅቡቲ ጉብኝታቸውን ጀምረዋል።

የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ " አውሮፕላኑን በኤርትራ የአየር ክልል ላይ ለማብረር ፈቃድ እንዳልተሰጠው ያወቅነው ትናንት ጠዋት ከበረራው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ ነበር " ብሏል።

አውሮፕላኑ #በበረራ_ላይ_እያለ ፈቃዱን ያገኛል ተብሎ በመወሰኑ ወደዚያ መሄዱንም ገልጿል።

ከቤርቦክ ጋር የተጓዙት ልዑካን ፤ አውሮፕላኑ እየበረረ ፈቃድ ማግኘት እንግዳ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

ቤርቦክን ፤ የሱዳን ጦርነት ጉዳይ እና የቀይ ባህር የመርከብ መንገድ ጉዳይ ትኩረት አድርጓል የተባለው የምሥራቅ አፍሪቃ ጉብኝታቸውን ነገ በደቡብ ሱዳን ያጠናቅቃሉ ተብሏል።

#AlAinNews #DW

@tikvahethiopia
🇪🇹 #NationalDialogue 🇪🇹

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ የምክክር ምዕራፉን ይጀምራል።

ለ7 ቀናት ያህል በሚቆየው የአዲስ አበባው ምክክር ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከ2 ሺህ በላይ ሰዎች እንደሚሳተፉ ኮሚሽኑ ገልጿል።

በምክክሩ የውይይት የአጀንዳ ሀሳቦችን የሚያመጡ ለምክክሩ የሚቀርቡ ተሳታፊዎች ሲሆኑ ፤ እነዚሁ ተሳታፊዎች በተስማሙባቸው የጋራ አጀንዳዎች ላይ የመፍትሔ ሀሳቦችን እንደሚያቀርቡ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመልክቷል። #DW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Africa #Kenya " በሙስና የተዘፈቀውን ካቢኔዎትን ይበትኑ ! " - የኬንያ አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ምክር ቤት ምንም እንኳን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጁን ቢሰርዙም ተቃውሞው ቀጥሏል። የኬንያ አብያተ ክርስትያናት ፕሬዜዳንቱ ካቢያናቸውን እንዲበትኑ ጠይቀዋል። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና በርከታ ኬንያውያን ሩቶ በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና እንዲያጸዱ ጥሪ እያቀረቡ…
#Kenya #Update

ሩቶ ካቢኔያቸውን በተኑ።

ለሳምንታት በህዝብ ተቃውሞ ስትናጥ የከረመችው ኬንያ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ የካቢኔ ሚኒስትሮቻቸውን በተኑ።

ሩቶ ዛሬ ነው ይህን እርምጃ የወሰዱት።

የፕሬዜዳንቱ እርምጃ በመላው ሀገሪቱ ለተነሳው የፀረ መንግሥት ተቃውሞ እንደምላሽ ነው የተወሰደው።

ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ፥ የካቢኔያቸው ተቀዳሚ ዋና ጸሐፊ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ እንዲሁም ምክትል ፕሬዝደንት ራጋቲ ጋቻጉ ሲቀሩ ሌሎቹን ሚኒስትሮቻቸውን በሙሉ ማሰናበታቸውን ተናግረዋል።

ፕሬዝደንቱ እርምጃውን የወሰዱት የሕዝባቸውን ድምፅ በመስማት መሆኑን ተናግረዋል።

#DW
#CitizenTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አዲስ እና ሰፋ ያለ መንግሥት ለመመሥረት ከሕዝቤ ጋር ውይይት አደርጋለሁ ! " - ሩቶ የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ካቢኔያቸውን በመበተን ሚኒስትሮቻቸውን ከስልጣን ያባረሩት ሕዝቡ ያነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ መሆኑን አሳውቀዋል። ሩቶ ፥ " ኬንያውያንን በመስማት ካቢኒዬን መርምሬ ነው የወሰንኩት " ብለዋል። " አዲስ እና ሰፋ ያለ መንግሥት ለመመሥረት ከሕዝቤ ጋር ውይይት አደርጋለሁ " ሲሉም አሳውቀዋል።…
የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥራቸውን ለቀቁ።

በሀገሪቱ በተቀጣጠለው ፀረ መንግሥት ተቃውሞ በርካቶች መሞታቸውን ተከትሎ ጠንካራ ትችት የተሰነዘረባቸው የፖሊስ አዛዥ ጃፌት ኮሜ በዛሬው ዕለት የስንብት ደብዳቤ አስገብተዋል።

የኬንያ ፕሬዝደንት ጽሕፈት ቤትም የኮሜን የስንብት ደብዳቤ ፕሬዝደንት ዊልያል ሩቶ መቀበላቸውን አረጋግጧል።

ጽሕፈት ቤቱ አክሎም በቦታቸው ምክትል የኬንያ ፖሊስ አዛዥ የነበሩት ዳግላስ ካንጃ መተካታቸውን አስታውቋል።

በሀገሪቱ ላይ የተካሄደውን ፀረ መንግሥት ተቃውሞ ያደራጀው ጀነሬሽን Z በአጭሩ ጄን Z የተሰኘው የኬንያ ወጣቶች ስብስብ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የኃይል እርምጃ ወስዷል ያሉት የኬንያ ፖሊስ አዛዥ ሥልጣናቸውን እንዲቀቁ ግፊት ሲያደርግ ነበር።

ሕዝባዊ ተቃውሞ የበረታባቸው የሀገሪቱ ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ትላንት ካቢኒያቸውን መበተናቸው ይታወሳል።

#DW
#Kenya

@tikvahethiopia
#Sudan

" በ2 ሳምንት ውስጥ ለቃችሁ ውጡ " - የሱዳን ጸጥታ ኃይሎች

የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች የውጪ ዜጎች ከዋና ከተማዋ ካርቱም እና በዙሪያ ካሉ አካባቢዎች እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጡ።

ፖሊስ ባወጣው ማሳሰቢያ ፥ የውጪ ዜጎች ከተባሉት የሱዳን አካባቢዎች ለመውጣት የ2 ሳምንት ጊዜ ብቻ ነው የተሰጣቸው።

የሱዳን በመንግሥት ወታደሮች እና የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ከገቡ በርካታ ወራት አልፈዋል።

ውጊያ አሁን ድረስ ተጠናክሮ በመቀጠሉ የውጪ ዜጎች ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ አካባቢውን ለቀው መውጣት እንዳለባቸው ነው ፖሊስ ያሳሰበው።

በሌላ በኩል ፥ ' በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ውስጥ የሌላ ሀገር ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አሉ ' በሚል በመገናኛ ብዙሃን መዘገቡን ተከትሎ በተለይ ከሌሎች የአፍሪቃ ሃገራት በመጡ የውጪ ዜጎች ላይ ጥላቻ ይስተዋላል።

ከቀናት በፊት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ከ150 በላይ የውጪ ዜጎች መታሰራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

#DW
#Reuters
#SudanMilitary
#RSF

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቪድዮ : የቀድሞ የአሜሪካ ፕ/ት ዶናልድ ትራምፕ የግድያው ሙከራ በተደረገባቸው ወቅት እሳቸው ቅስቀሳ ከሚያደርጉበት ስፍራ በቅርብ ርቀት በሚገኝ ጣሪያ ላይ የነበሩ የ " ሴክሬት ሰርቪስ " የስናይፐር ተኳሾች የግድያ ሙከራውን ባደረገው ሰው ላይ ምላሽ ሲሰጡ ታይተዋል። አንድ ተቀርጾ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨ ቪድዮ ሁለት የሴክሬት ሰርቪስ ስናይፐር ተኳሾች በፍጥነት ኢላማ አድርገው የግድያ ሙከራ ባደረገው…
#USA

የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የሪፐብሊካን ፓርቲ እጩነታቸው ትላንት ተቀብለዋል።

ከቅዳሜው የግድያ ሙከራ በኋላ ሪፐብሊካኖች ለዶናልድ ትራምፕ ጠንካራ ድጋፋቸውን ከምን ጊዜውም በላይ አሳይተዋል። 

" የሁሉም አሜሪካውያን ፕሬዝዳንት እሆናለሁ " ያሉት ዶናልድ ትራምፕ ፦

- በሀገር ውስጥ ሕገወጥ ስደተኞችን ማባረር፣

- ኢኮኖሚውን ማሳደግ

- ግብር መቀነስን በዋና ግብነት አስቀምጠዋል።


በውጪ ግንኙነታቸውም የጋዛና የዩክሬይንን ግጭት መፍትኄ ከመስጠት ጀምረው ዓለምን ካጣችው ሰላም ጋር እንደሚያስታርቋት ቃል ገብተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳሉ የዴሞክራቶች ፓርቲን በመወከል ተወዳድረው የአሜሪካ የቀድሞ ፕሬዚደንት የነበሩት ባራክ ዖባማ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን እጩ የኋይት ሐውስ ተወዳዳሪ መሆናቸው እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል።

ባራክ ኦባማ ሁሉ የቀድሞዋ የምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ናንሲ ፔሎሲም ሥጋታቸውን ገልጠዋል። #DW

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የ6 ሰዎችን ማግኘት አልተቻለም  "- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን፣ ገዜ ጎፋ ወረዳ ኪንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ የደረሰዉን የመሬት መንሸራተት አደጋ በተመለከተ ክልሉ ዛሬ ወቅታዊ መረጃ ሰጥቶ ነበር። በዚህም መግለጫ " የቀበሌዉን ማህበረሰብ ቁጥር ለመለየት በተደረገ የቤት ለቤት ቆጠራ ስድስት ሰዎች አልተገኙም " ብሏል። አሁንም አስክሬን ፍለጋዉን እንደቀጠለ ጠቁሟል። በሌላ በኩል ፤ እስካሁን…
#Update

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የቀሪ ሰዎችን አስክሬን የማፈላለጉ ሥራ ማብቃቱን ዛሬ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት አሳውቋል።

ያልተገኙ ሟቾችን የመፈለጉ ሥራ ያበቃው አደጋው ከተከሰተበት ከባለፈው ሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ እስከ ትናንት ድረስ የቁፋሮ ሥራው ሲካሄድ ከቆየ በኋላ እንደሆነ ጠቁሟል።

በፍለጋው የ243 ሰዎች አስክሬን በማግኘት በክብር እንዲያርፍ ሲደረግ፤ የ6 ሰዎች እስክሬን ግን እስከ ትናንት ተፈልጎ አለመገኘቱን አሳውቋል።
#DW

@tikvahethiopia