TIKVAH-ETHIOPIA
1.42M subscribers
55.2K photos
1.38K videos
199 files
3.7K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
5ኛው አመት የTIKVAH-ETH የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ ከነገ ነሃሴ 20 እስከ መስከረም 30 በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል!!

ላለፉት አመታት በአብዛኛውን በከተሞች አካባቢ የሰራነውን ስራ #በማጠናከር ዘንድሮ ደግሞ ከከተማ ውጭ ወደሚገኙ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ትኩረታችንን እናደርጋለን።

ምን አይነት መፅሃፍት ነው ከቤተሰባችን አባላት የምናሰባስበው?

•ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ መፅሃፍትን/Text Book/ እንዲሁም አጋዥ መፅሃፍት ብቻ

•በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ ትውልዱን ይጠቅማል፤ እውቀት ያስጨብጣል የምንላቸው መፅሃፍት።

•ትንሹ መስጠት የሚቻለው መፅሃፍ 1

•መፅሃፍቱ የሚገቡት ገጠራማ አካባቢ ለሚገኙ እና በአካል ሄደን ለምንለያቸው ቤተ መፅሃፍት

#እርሶ ምን ማድረግ ይችላሉ??

√ቢያንስ አንድ የመማሪያ መፅሃፍ ለሚወዷት ለኢትዮጵያ መለገስ ይችላሉ። እንዲሁም ከፍተኛ የመፅሃፍት ችግር ያሉባቸው ቦታዎችን በመለየት የማስተባበር ስራ ሊሰሩ ይችላሉ።

•TIKVAH-ETH በሀገሪቱ በየትኛውም አካባቢ ለምትገኙ የበጎ አድራጎት ማህበራት ይህን ሀገራዊ ስራ እንድታግዙ ጥሪውን ያቀርብላችኃል።

•የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ ትልቁን ድርሻ በመውሰድ ከተማራቹባቸው እና ስትጠቀሟቸው ከነበሩት መፅሃፍ መካከል ቢያንስ አንዱን ለመጪው ትውልድ በስጦታ አበርክቱ።

•በStopHateSpeech ጉዞ ተሳታፊ የነበራችሁ የቤተሰባችን አባላት ይህን ለሀገርና ለትውልድ የሚሰራን ስራ በሙሉ አቅማችሁ እንድታግዙ ጥሪ እናቀርባለን።

•በውጭ ሀገር የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት ጠቃሚ ናቸው የምትሏቸው መፅሃፍት በመላክ አልያም እዚህ ሀገር ባላችሁ ወዳጅና ዘመድ መፅሃፍት እንዲገዛ በማድረግ ይህን

#ኦሮሚያ
#አማራ
#ትግራይ
#ደቡብ
#ሱማሌ
#አፋር
#ሀረሪ
#ጋምቤላ
#ቤኒሻንጉል
#አ/አ ከተማ አስተዳደር
#ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር

🏷በማኛውም አይነት ቋንቋ የተዘጋጀ የመማሪያ መፅሃፍ መለገስ ይቻላል!!
-------------------------------------------------------
በአሁን ሰዓት ልየታ ከተደረገባቸው አካባቢዎች መካከል፦

#ራያ_ቆቦ በራያ ቆቦና ዙሪያዋ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት መፅሃፍት ለመለገስ እና ይህን ስራ ለማስተባበር ከቤተሰባችን አባል #ሉላይ ጋር ይገናኙ፦ +251949256094

#ድሬዳዋ በድሬዳዋ ከተማ እና አካባቢው የምትገኙ ደግሞ ከቤተሰባችን አባል መሃሪ 0915034762/መሃሪ/ ጋር መገናኘት መፅሃፍ መለገስ ትችላላችሁ።

ሌሎች አካባቢዎች ላይ እኛም ለሀገራችን መስራት እንፈልጋለን የምትሉ እውቅና ያላችሁ ማህበራት ካላችሁ መልዕክት አስቀምጡልን @tsegabwolde 0919743630

5ኛው አመት የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት የመፅሃፍ ማሰባሰብ ዘመቻ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመማሪያ መፃህፍትን ለግሱ!

#አዲስ_አበባ
👉ዮናስ ገ/መስቀል
0970514616
👉መባ
0924140293

#ሰበታ
👉ያሬድ ለማ
0932540523
👉ያብስራ ካሳ
0921421493

#መቐለ
👉ኤርሚያስ ደጀኔ
0912178520
👉ፊራኦል መስፍን
0923602445

#ራያ_ቆቦ
👉ሉላይ
+251949256094

#ድሬዳዋ
👉መሃሪ
0915034762

#አዳማ
👉ሰላም
0949377735

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመማሪያ መፃሃፍትን ለግሱ!

#አዲስ_አበባ
👉ዮናስ ገ/መስቀል
0970514616
👉መባ
0924140293

#ሰበታ
👉ያሬድ ለማ
0932540523
👉ያብስራ ካሳ
0921421493

#መቐለ
👉ኤርሚያስ ደጀኔ
0912178520
👉ፊራኦል መስፍን
0923602445

#ራያ_ቆቦ
👉ሉላይ
+251949256094

√ጅማ
👉አሰፋ
0911670454

#ድሬዳዋ
👉መሃሪ
0915034762

#አዳማ
👉ሰላም
0949377735

#ሀዋሳ
አለን ኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ማህበር
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ የመደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራት @tsegabwolde

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኑ ትውልድ እንገንባ!

ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል የመማሪያ መፅሃፍትን ይለግሱ!

#መቐለ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት በተለይም የዘንድሮ ተፈታኞች የመማሪያ መፅሃፍትን ለመለገስ የምትፈልጉ👉ኤርሚያስ ደጀኔ/0912178520/፣ ፊራኦል መስፍን/0923602445/

#ራያ_ቆቦ እና አካባቢው የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት በተለይም የዘንድሮ ተፈታኞች የመማሪያ መፅሃፍትን ለመለገስ የምትፈልጉ👉ሉላይ/+251949256094/

#ወላይታ_ሶዶና አካባቢዋ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት በተለይም የዘንድሮ ተፈታኞች የመማሪያ መፅሃፍትን ለመለገስ የምትፈልጉ👇
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/
0926172318/Gedi/
+251936455130/Bereket/
0968787670 /Zegeye/

በሁሉም ክልል፣ ዞን እና ወረዳ የሚገኙ አስተባባሪዎችን በየጊዜው ይፋ እናደርጋለን!! እርሶም የዚህ አካል በመሆን ማስተባበር ይችላሉ! @tsegabwolde 0919743630

5ኛው አመት የTIKVAH-ETH የመፅሃፍት ማሰባሰቢያ ዘመቻ!
#አምቦ #ለኩ #ጅማ #ከሚሴ #ይርጋለም #ሃዋሳ #ሶዶ

ኑ ትውልድ እንገንባ!

#አዲስ_አበባ
0970514616/ዮናስ ገ/መስቀል/
0924140293/መባ/

#ሰበታ
0932540523/ያሬድ ለማ/
0921421493/ያብስራ ካሳ/

#መቐለ
0912178520/ኤርሚያስ ደጀኔ/
0923602445/ፊራኦል መስፍን/

#ራያ_ቆቦ
+251949256094/ሉላይ/

#ጅማ
0911670454/አሰፋ/

#ድሬዳዋ
0915034762/መሃሪ/

#አዳማ
0949377735/ሰላም/

#ሀዋሳ
+251926429534/ተስፋ/
+251935932153/ብስራት/

#ለኩ
0919687777/ዳዊት እንዳለ/

#ይርጋለም
0953804369-/አሸናፊ/
0964039768-ብርሀኑ/

#ከሚሴ
0915543171/ሁሴን/

#ወላይታሶዶ
+251913776084/Aso/
0926172318/Beza/

•ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ እና አጋዥ መፅሃፍትን በመለገስ ለመጭው ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን እናውርስ!!

📚የዘንድሮው አመት ተፈታኝ ተማሪዎች እና ወላጆች በዚህ ስራ ላይ በስፋት በመሳተፍ ለመጭው ትውልድ አርዓያ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን!

5ኛው አመት የTIKVAH-ETHIOPIA የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ!

በዚህ ሀገራዊ ስራ መሳተፍ የምትፈልጉ የበጎ አድራጎት ማህበራትና ግለሰቦች @tsegabwolde

በሁሉም ከተሞች ያሉ አስተባባሪዎችን በየዕለቱ እናሳውቃለን!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#መቐለ #ራያ #አክሱም #ዓዲግራት

ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ስድስት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ወደ አክሱም ዩኒቨርሲቲ በማቅናት ምልከታ ሊያደርግ ነው፡፡

በግጭቱ ምክንያት ሥራ ያቋረጡትን አክሱም፣ ራያ፣ አዲግራት እና መቐለ ዩኒቨርሲቲዎች ወደ አገልግሎት ለመመለስ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል።

እስካሁን ባለው ሁኔታ አክሱም እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች ዳግም ወደ አገልግሎት በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ ንግግር መጀመሩን በትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደር እና መሰረተ ልማት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለፋና ተናግረዋል።

በቀጣይም ከመቐለ እና አዲግራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ግንኙነት እንደሚጀመር ኃላፊው አመላክተዋል፡፡

በአክሱም ከተማ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ ተከትሎ፤ ስድስት አባላት ያሉት የባለሙያዎች ቡድን ከሰኞ ጀምሮ የአክሱም ዩኒቨርሲቲ ዋናውን ግቢ ጨምሮ አድዋ እና ሽረ ግቢዎችን በስፍራው በመገኘት ምልከታ ያደርጋል ብለዋል፡፡

ቡድኑ ተቋማቱ በሰው ኃይል፣ በመሰረተ ልማት፣ በቤተ ሙከራ፣ በኔትወርክ፣ በመኝታና መማሪያ ክፍሎች፣ በማስተማሪያ ሆስፒታል፣ በቤተ መጻሕፍት እና ሌሎች አገልግሎቶች ዩኒቨርሲቲው የመማር ማስተማር ሥራውን ለማስጀመር የሚያስችለውን ሁኔታ ይመለከታል፡፡ #FBC

@tikvahuniversity
#ራያ

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የአሜሪካ ዲፕሎማቶች ፈፅመውታል ያሉትን ተግባር አጥብቀው ተቹ።

ምን ተፈጠረ ?

የአማራ ክልል እንዲሁም የትግራይ ክልል ጥያቄ ከሚያነሱባቸው አካባቢዎች አንዱ የራያ አካባቢ እንደሆነ ይታወቃል።

በዚህ አካባቢ ከማንነት ጥያቄ ጋር የተያያዘ የቆየ ጥያቄ ያለ ሲሆን አንዳንድ አካባቢዎች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከትግራይ አስተዳደር ወጥቶ ወደ አማራ ክልል ገብቷል።

ከትላንት በስቲያ የአሜሪካ ኤምባሲ ልዑካን ዲፕሎማቶች በራያ አለማጣ አካባቢ እንደነበሩ ተነግሯል።

ታዲያ የትግራይ አስተዳደር በ " ኃይል ተወረው ተይዘውብኛል " በሚለው አካባቢ ላይ የአሜሪካ ዲፕሎማቶች መገኘታቸው እንዳስቆጣው ተሰምቷል።

አቶ ጌታቸው ረዳ ምን አሉ ?

አቶ ጌታቸው ፤ " የአሜሪካ ኤምባሲ የዲፕሎማቶች ልዑካን ቡድን አላማጣ ነበር ፤ ምን ሲሰሩ እንደነበር ፈጣሪ ነው የሚያውቀው " ያሉ ሲሆን " ዲፕሎማቶቹ የአማራ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ በኃይል የያዙትን አካባቢ መጎብኘታቸው፣ የትግራይ ግዛቶች በጽንፈኛ ኃይሎች የኃይል ቁጥጥር ስር መሆኑን እንደመቀበል ይቆጠራል " ብለዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ የአሜሪካ ዲፕሎማቶች በአካባቢው ላይ የተገኙት በሕገወጥ አስተዳደሩ ባለሥልጣናት በተቀነባበረ ድራማ ላይ መሆኑን ፤ ይህን ግን ለምን እንዳደረጉ ገልፅ እንዳልሆነ ጠቁመው ድርጊቱ አሜሪካ ለፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ያላትን ቁርጠኝነት የሚጻረር በመሆኑ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ ተቃውመዋል።

በሌላ በኩል ፦ ከሰሞኑን የፌደራል መንግስት ለሚቀጥለው በጀት ዓመት " በራያ እና አካባቢው ለሚገኙ መዋቅሮች የሚመድበው ድጎማ " ወደ ትግራይ ክልል እንዳይተላለፍ የ145 ሺህ ሰዎች ፊርማ ያለበት ሰነድ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት መቅረቡን ከ " ኢትዮጵያ ኢሳይደር " ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ፊርማውን አሰባስቦ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ያስረከበው የ " ወሎ ራያ አማራ ማንነትና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ " ነው።

ለፌዴሬሽን ምክር ቤት በደብዳቤ የቀረበው ይህ ጥያቄ የሰሜኑ ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ስር የነበሩ አራት መዋቅሮችን የሚመለከት ሲሆን እነዚህ መዋቅሮች በትግራይ ክልል ስር በነበሩበት ወቅት " የማንነት ጥያቄ ይነሳባቸው " እንደነበር ተገልጿል።

ነገር ግን የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት ተከትሎ የአካባቢው ህዝብ " ራሱን በራሱ ለማስተዳደር " መቻሉን ኮሚቴውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ባስገባው ሰንድ ላይ ገልጿል።

የወሎ ራያ አማራ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ የአካባቢው ህዝብ " ከፌደራል መንግስቱ ሊያገኝ ይገባ የነበረው በጀት " የሚላከው " በትግራይ ክልል በኩል ነው " በመባሉ ምክንያት እስካሁን የገንዘብ ድጎማ አለማግኘታቸውን ሰነዱ አስረድቷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
 " ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ነገር ሁሉ የአማራ ክልል ሙሉውን ኃላፊነት ይወስዳል " - የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ምን አለ ? " የአማራ ክልል የትግራይ መሬት በካርታው በማስፈር የትምህርቱ ሰርዓቱ አካል በማድረግ እያስተማረበት ይገኛል " ሲል የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ከሰሰ። " ክልሉ የትግራይ መሬት በሚመለከት በስርዓተ ትምህርቱ ያሰፈረው…
ራያ ላይ ምን እየሆነ ነው ?

“ ህወሓት የፕሪቶርያውን ስምምነት በግልፅ በመጣስ ራያ ላይ ጦርነት ከፍቷል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር

የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባኛል ጥያቄ ከሚያነሱበት አንዱ በሆነው ራያ አላማጣ አካባቢ ትላንትና " ህወሓት " ተኩስ መክፈቱን፣ በዚህም በሰው ሕይወት ላይ ሞትና የአካል ጉዳት ሙድረሱን አካባቢውን ከሚያስተዳድሩ አመራሮች (ባለስልጣን) አንደኛው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ የአካባቢው አመራር (ባለስልጣን) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ራያ ላይ  አዲስ ነገር አለ። ህወሓት የፕሪቶሪያውን ስምምነት በግልፅ በመጣስ ራያ ላይ ጦርነት ከፍቷል ” ብለዋል።

“ ቀን ላይ አንድ ሰው ሕይወቱ አልፏል። ሁለት ቆስለው ወደ ደሴ ሪፈር ተብለዋል። ደንበሩን በማለፍ የራያ አላማጣ ወረዳ አዳዲስ ቀበሌዎች ተቆጣጥሯል ” ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጦርነቱ የተከፈተው በምን ሰዓት ነው ? በዬት በኩል ነው የተከፈተው ? አሁን ተኩስ አለ ? በቁጥጥር ስር የሆኑት ቀበሌዎች እነማን ናቸው ? ከሰሞኑን ለጦርነት አመላካች ጉዳዮች ነበሩ ? ሲል ለአመራሩ ጥየቄ አቅርቧል።

አመራሩም ፣ “ ጦርነቱን የጀመሩት ሰኞ ሌሊት 6:00 አከባቢ ሲሆን፣ እስከ ቀን 6:30 ድረስ ነበር። መከላከያ ለራያ ምሊሻ ‘ወደ ኋላ ተመለሱ እነርሱም ይመለሳሉ’ በማለቱ ምክንያት ጦርነቱ ቁሞ የራያ ምሊሻ ወደ ኋላ ቢልም TDF መልሶ ቦታውን ተቆጣጥሮታል ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ተኩሱ የተጀመረበትን ልዩ ቦታ በተመለተ በሰጡት ምላሽም ፣ “ የተጀመረበት ቦታው ‘ጮጓራ’ ይባላል። የራያ አላማጣ ቦታ ነው። አሁንም እሱን በማለፍ ወደ ‘ኮስም’ የሚባል አከባቢ እየተጠጉ ነው። ተጨማሪ ኃይልም እያስጠጉ ይገኛሉ ” ብለዋል።

የአካባቢው አመራር የተኩሱን መነሻ በገለጹበት አውድ ፣ “ የዚህ ዋናው መንስኤ አማራ ክልል #ወልቃይት እና #ራያ በስርዓተ ትምህርቱ ካርታ ላይ ተካተዋል በሚል በወጣው መግለጫ ነው ” ሲሉ አስረድተዋል።

“ የራያ ህዝብ የዘመናት ትግሉ በህጋዊ መንገድ ፍትህ ማግኘት እንጂ ጦርነት አይፈልግም። እነሱ እየተከተሉ ደጋግመው እያቆሰሉት ነው ” ሲሉም አክለዋል።

በህወሓት ተከፈተ ስለተባለው ተኩስ በትግራይ ክልል በኩል እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በትግራይ ያሉ አስታዳዳሪዎችን አግኝቶ የነበረ ሲሆን ስብሰባ ላይ እንደሆኑና ወደ በኃላ ማብራሪያ እንደሚሰጡን ገልጸዋል።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ካቢኔ ሰሞኑን በሰጠው መግለጫ፣ “ የአማራ ክልል የትግራይ መሬት በካርታው በማስፈር የትምህርቱ ሰርዓቱ አካል በማድረግ እያስተማረበት ይገኛል " ማለቱ አይዘነጋም።

አስተዳደሩ ፤ በአማራ ክልል መንግሥት በኩል በትግራይ ህዝብ ላይ ግፍ እና በደል ሲፈፀም እንደቆየ አሁንም እንደቀጠለ ገልጾ ክልሉ የሰላም ስምምነቱን የሚያናጋ ጠብ አጫሪ ተግባራትን እየፈፀመ እንደሆነ ከሶ ነበር።

የፌደራል መንግስት በካርታው ላይ ምንም አይነት እርማት እንዳልሰጠ ፣ የአማራ ሕዝብም ሆነ ሌለው የኢትዮጵያ ህዝብ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ጎን እንዲቆሙ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ነገር ሁሉ ግን የአማራ ክልል ሙሉውን ኃላፊነት ይወስዳል " ሲል አስጠንቅቆ ነበር።

መረጃው በአ/አ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ራይ " ግጭቱ ከ20 ደቂቃ በላይ አልፈጀም፤ በግጭቱ የሞተ ሰውም የለም  " - በትግራይ ደቡባዊ ዞን የራያ ጨርጨር አስተዳዳሪ አቶ ግደይ ካልኣዩ " የአማራ ታጣቂዎች በትግራይ ግዛት ውስጥ የፈፀሙት ትንኮሳ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት  እንዲያስቆመው ተደርጓል " - የትግራይ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ረዳኢ ሓለፎም የትግራይ እና አማራ ክልሎች የይገባናል ጥያቄ በሚያነሱበት…
#Update #ራያ

° “ ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል ” - የአላማጣና አካባቢው አመራር

° “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል ” - የተጎጂ ቤተሰብ

በአማራ እና ትግራይ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ተቀሰቀሰ የተባለውን ተኩስ በተመለከተ በአማራ ክልል በኩል ሆነው ቃላቸውን የሰጡ አንድ የአካባቢ ከፍተኛ አመራር ከትላንት ወዲህ ያለውን ሁኔታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።

እኚሁ አመራር ፤ “ ዛሬ አፍሪካ ህብረት መጥተው ማን ስምምነቱ እንደጣሰ ተመልክተዋል። አፍሪካ ህብረት እያንዳንዱን ችግር አይተውታል ” ብለዋል።

“ ዛሬ ተኩስ የለም። የያዙት ቦታ አሁንም አለቀቁም። ከያዙት ቦታ የሚገኘውን ኮስም 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ንብረቱ ዘርፈው ጭነውታል። አፍሪካ ህብረት ሁሉንም ታዝቧል። መከላከያ ያለውን እውነታ አስረድቷቸዋል ” ሲሉ አክለዋል።

“ የሞተውን ዛሬ በክብር ቀብረነዋል። ማቹ ተፈራ ፍቃዱ ይባላል። የሁልግዜ ለምለም ቀበሌ ነዋሪ ነው። ቀብሩም ከቀኑ 7፡00 በጎልአጆ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል። ሪፈር የተላኩ አልተመለሱም ” ሲሉ ተናግረዋል።

በተኩሱ ጉዳት ደርሶባቸው ሪፈር ተጽፎላቸዋል ከተባሉት ሁለት ቁስለኞች መካከል የአንዱ ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ጉዳቱ በጣም ከፍ ያለ ነው። አጥንቱ ደቋል። በአላማጣ አዋሳኝ በኩል ድንበር ላይ ቆሞ እያለ ነው በእነርሱ (በህወሓት) በኩል ጥቃት የደሰበት” ብለዋል።

“ በጣም ከፍተኛ ጉዳት አለው ሁለቱም እጆቹ ከኋላውም ቀላል ጉዳት ደርሷል። ግን ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሁለቱ እጆቹ ላይ ነው። ወደ ደሴ ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎለት እንደገና ደሙ አልቆም ሲል ወልዲያ ሆስፒታል ከትላንት ማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ (መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ/ም) 7፡00 ገብቶ ነበር። ከዚያ በኋላም ወደ ግል ክሊኒክ ገብቷል። ሁለቱም እጆቹ ላይ ስለሆነ በጣም ስቃይ አለው ” ሲሉ አክለዋል።

" በድንበራችን ላይ መጥተው ነው ጥቃህት ያደረሱት" ብለው፣ መንግሥት ለጉዳዩ ትከረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

የትግራይ እና የአማራ ክልል አዋሣኝ ቦታ የሚገኙ የስራ ኃላፊዎች በራያ በተፈጠረው ጉዳይ እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ ይገኛሉ።

በትግራይ ክልል በኩል ያሉ አመራሮች ሰሞነኛውን ተኩስ የከፈቱት የአማራ ክልል ታጣቂዎች እንደሆኑ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ግጭቱም ሆን ተብሎ  ፦
- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ለማደናቀፍ
- የትግራይ ማህበረሰብ ተወካዮች ከጠቅላይ ሚንስተር ዶ/ር አብይ አህመድ ያደረጉት ውይይትና የአማራ እና የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንቶች በፕሪቶሪያ ውል አተገባበር ዙሪያ የፈጠሩት መድረክን ተከትሎ 'ውሉ ተግባራዊ ይሆናል' የሚል ስጋት ስለፈጠረባቸው ነው " ብለዋል።

" አሁንም የአማራ ክልል ታጣቂዎች ለቀጣይ ትንኮሳ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ደርሰንበታል " ብለዋል።

የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ውል እንዲከበርና የአማራ ክልል ታጣቂዎች በኃይል ከያዟቸው የትግራይ አካባቢዎች እንዲወጡ እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

እስካሁን ድረስ በሁለቱም በኩል በክልል ደረጃ ስለ ጉዳዩ ያወጡት መግለጫ የለም። የፌዴራል መንግሥትም ያለው ነገር የለም።

መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ራያ

“ ሕወሓት /TPLF ወረራ ፈጽሟል። የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሷል ” - አቶ ሀይሉ አበራ

የትግራይ እና አማራ ክልሎች የወሰን ይገባኛል ጥያቄዎች በሚያነሱባቸው የራያ አላማጣ አካቢዎች ሰሞኑን በተለይ ዛሬ የተኩስ ልውውጥ መደረጉን የአላማጣና አካባቢው ባለስልጣናትና የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የአላማጣ ከተማ እና ዙሪያው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ የትግራይ ታጣቂዎች በስናይፐርና ሌሎች መሳሪያዎች የታገዘ ተኩስ ተከፍቶብናል ” ብለዋል።

አክለውም፣ “ ባለፈው ጦርነት በደረሰብን ሀዘን እንባችን አልደረቀም። መንግሥት ግን እስከመቼ ድረስ ነው የዚህን አካባቢ ችግር የማይቀርፈው ? ነው ወይስ ሕዝቡ እርስ በእርሱ እንዲተላለቅ ነው የፈለገው ? ” ሲሉ ጠይቀዋል።

“ ወያኔ የኔ ናቸው የሚላቸው የአላማጣና አጠገቡ አካባቢዎች በሙሉ የአማራ እንጂ የትግራይ መሬት ሆነው አያውቁም። ደማችን ይፍሰስ እንጂ መሬታችንን አንለቅም። መንግሥት የትግራይ አመራሮችን ይዳኝልን ” ብለው፣ በንጹሐንና በንብረት ላይ ጉዳት ሳይደርስ እንዳልቀረ፣ አሁን ግን ትክክለኛውን ቁጥር ለመግለጽ ለጊዜው እንደሚያስቸግር አስረድተዋል።

ስለጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው አንድ የአላማጣና አካባቢው አመራር በሰጡት ቃል፣ “ ወያኔ ሰሞኑን በሰላማዊ ሰልፍ ሽፋን ተቆጣጥሯቸው ከነበሩ ቦታዎች በተጨማሪ ተቆጣጥሯል። አርሚ 24 ነው ተኩስ የከፈተብን ” የሚል አጭር ቃሎ ሰጥተው ሁነቱን በሂደት እንደሚገልጹ ጠቁመዋል።

በተጨማሪ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለግጭቱ ሁኔታ፣ የደረሰው ጉዳት ምን እንደሚመስል አላማጣ ከተማን በከንቲባነት እያስተዳደሩ ለሉትና የወሎ ራያ አማራ ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ ለሆኑት አቶ ሀይሉ አዱኛ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ፥ “ ሕወሓት ወረራ ፈጽሟል። የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሷል። ፍላጎታቸውን በኃይል ለመፈጸም እየሞከሩ ነው። ሂደቱ በዋነኝነት ይህን ነወሰ የሚመስለው። ዝርዝር ገለጻ ነገ እሰጣለሁ ” ብለዋል።

ዝርዝር ምላሻቸው ነገ ይቀርባል።

🔵 በትግራይ በኩል ምን ተባለ ?

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለው አባል ፥ በትግራይ በኩል ነዋሪዎችን እና የመንግስት ሰዎችን ስለ ሁኔታው ጠይቋል።

ዛሬ ከሰዓት ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፥ " የራያ ጨርጨር ፣ የራያ አላማጣ ፣ ኮረም ኦፍላና ዛታ አከባቢ ያሉ ቀበሌዎች ከታጣቂዎች ነፃ ሆነዋል " ብለዋል።

አጠቃላይ በርካታ ስፍራዎች ቦታውን ይዘው ከነበሩ ታጣቂዎች ነጻ ሆኗል ሲሉ ገልጸዋል።

በከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ምክንያት ከአካባቢው የወጡ ነዋሪዎችም አሉ ሲሉ ገልጸዋል።

አሁንም ቢሆን የፕሪቶሪያው ስምምነት ተከብሮ የአማራ ታጣቂዎች ከአካባቢው ሊወጡ የተፈናቀለው ህዝብም ወደ ቦታው ሊመለስ ይገባል ብለዋል።

ትናንትና ወደ ራያ ጨርጨር አስተዳዳሪ አቶ ካልኣዩ ግደይ ደውለን የነበረ ሲሆን መጠነኛ ግጭት እንደነበረ ተናግረዋል።

ዛሬ በሰጡት ቃል ደግሞ ፥ " በወረዳው በአማራ ታጣቂዎች ሰር የነበሩት ሁለት ቀበሌዎች ነፃ ወጥቷል " ብለዋል።

ሌሎች የክልሉን ኃላፊዎች ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

የትግራይና አማራ ክልሎች ይገባኛል በሚያነሱበት በራያ አካባቢ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የግጭት ሁኔታዎች ይታዩ እንደነበር በሁለቱም በኩል ያሉ የመንግስት አካላትን በማነጋገር መረጃ ማድረሳችን ይታወሳል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia