TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.6K photos
1.41K videos
203 files
3.86K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ደቡብ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በደቡብ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልል የሚታዩ የክልል እንሁን ጥያቄዎችን በጥናት ለመፍታት የክልሉ ገዥ ፓርቲ ደኢህዴን ሲያስጠና ቆየው ጥናት ውጤት ዛሬ ይፋ ሆነ።

የጥናት ቡድኑ ምክትል ሰብሳቢ ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ እንዳሉት 20 አባላት ያሉት የጥናት ቡድን ተዋቅሮ ላለፉት ሰባት ወራት ሰፊ ጥናት ሲያካሂድ ቆየቷል። በዚህም መሰረት ሶስት አማራጮችን አስቀምጧል ብለዋል ምክትል ሰብሳቢዋ።

በጥናቱ የተለየው የመጀመሪያው አማራጭ አብዛኛው የክልሉ ህዝብ አሁን ያለው የክልሉ አደረጃጀት ቢቀጥል የህዝቦችን አብሮነትና ያጠናክራል፤ ጠነካራ የደቡብ ህዝቦች ክልልንና የኢትዮጵያን አንድነት ያጠናክራል የሚል ነው።

በጥናቱ የተለየው መጀመሪያ አማራጭ አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሮ ተቀባይነት የሚያጣ ከሆነ በጥናቱ በሁለተኝነት የተለየው አማራጭ ደግሞ ክልሉን በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በመክፈል ከዚህ በፊት ይነሱ የነበሩ የፍተሃዊነት ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ማድረግ ነው።

በጥናቱ በሶስተኝነት የተቀመጠው ሃሳብ ደግሞ ሁለቱ አማራጮች ተግባራዊ የማይሆኑ ከሆነና ሁኔታው ከክልል አልፎ በአገሪቱ ሰላምና አንድነት ላይ ጫና የሚፈጥር ከሆነ ጉዳዩ ለጊዜው ቢቆይና በእርጋታ ቢታይ የሚል ነው። እንደጥናት ቡድኑ ምክትል ሰብሳቢ ከ17 ሺህ በላይ ሰዎች በላይ ለጥናቱ በመረጃ ሰጪነት ተሳትፈዋል።

ምንጭ፦ ኢፕድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ደቡብ

በ2011 ዓ.ም. በደቡብ ክልል በነበረ አለመረጋጋት በጉራጌ፣ ሲዳማ፣ ከፋ፣ ጎፋና በጌድዖ #ከ50 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ በመዘጋታቸው ከ40 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ትምህርት ማቋረጣቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተሰማ ዲማ ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ። «አሁንም ሎካ ብላቴ ዙሪያ ወረዳና ምሥራቅ አርሲ ድንበር አካባቢ ላይ ግጭቶች አሉ፤ ወደ 7 የሚጠጉ የተቃጠሉ ትምህርት ቤቶች አሉ። እዛ አካባቢ አሁንም ተመልሰን ለማስተማር እና የማካካሻ ፕሮግራም ለመስጠት እንቸገራለን የሚሉ ወረዳዎች አሉ» ብለዋል።

Via #DW
@tsegawolde @tikvahethiopia
#ደቡብ

ከፍተኛ ውጤት የተመዘገበባቸው የትምህርት አይነቶች ዛሬም የቤተሰባችን መነጋገሪያ እንደሆኑ ነው። ከላይ የምትመለከቱት #በደቡብ_ክልል ውስጥ በሚገኙ ሁለት የተለያዩ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተማሪዎች በBiology እና Civics የትምህርት አይነቶች ያስመዘገቡትን ተቀራራቢና ከፍተኛ ውጤት ነው።

🏷አስተያየታቸውን እያካፈሉን ያሉ ወላጆች እና ተማሪዎችም የፈተናዎች ኤጀንሲ የተፈጠረውን ስህተት ወይም ለምን እንዲህ ሊሆን እንደቻለ ጊዜ ወስዶ መመልከት አለበት፤ አንድና ሁለት ትምህርት ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ ፈተናውን ሊፈትሸው ይገባል ብለዋል።

@tsrgabwolde @tikvahethiopia
#ደቡብ_ኮሪያ

ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በደቡብ ኮርያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተዘጋጀ የእራት ግብዣ ከኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት ጋር ተገናኙ። ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ የኮሚኒቲ አባላቱ በመደመር እሴቶች ላይ በማተኮር ባሉበት ሆነው ሀገራቸውን እንዲረዱ አበረታትተዋል።

ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚ/ር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
5ኛው አመት የTIKVAH-ETH የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ ከነገ ነሃሴ 20 እስከ መስከረም 30 በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል!!

ላለፉት አመታት በአብዛኛውን በከተሞች አካባቢ የሰራነውን ስራ #በማጠናከር ዘንድሮ ደግሞ ከከተማ ውጭ ወደሚገኙ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ትኩረታችንን እናደርጋለን።

ምን አይነት መፅሃፍት ነው ከቤተሰባችን አባላት የምናሰባስበው?

•ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ መፅሃፍትን/Text Book/ እንዲሁም አጋዥ መፅሃፍት ብቻ

•በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ ትውልዱን ይጠቅማል፤ እውቀት ያስጨብጣል የምንላቸው መፅሃፍት።

•ትንሹ መስጠት የሚቻለው መፅሃፍ 1

•መፅሃፍቱ የሚገቡት ገጠራማ አካባቢ ለሚገኙ እና በአካል ሄደን ለምንለያቸው ቤተ መፅሃፍት

#እርሶ ምን ማድረግ ይችላሉ??

√ቢያንስ አንድ የመማሪያ መፅሃፍ ለሚወዷት ለኢትዮጵያ መለገስ ይችላሉ። እንዲሁም ከፍተኛ የመፅሃፍት ችግር ያሉባቸው ቦታዎችን በመለየት የማስተባበር ስራ ሊሰሩ ይችላሉ።

•TIKVAH-ETH በሀገሪቱ በየትኛውም አካባቢ ለምትገኙ የበጎ አድራጎት ማህበራት ይህን ሀገራዊ ስራ እንድታግዙ ጥሪውን ያቀርብላችኃል።

•የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ ትልቁን ድርሻ በመውሰድ ከተማራቹባቸው እና ስትጠቀሟቸው ከነበሩት መፅሃፍ መካከል ቢያንስ አንዱን ለመጪው ትውልድ በስጦታ አበርክቱ።

•በStopHateSpeech ጉዞ ተሳታፊ የነበራችሁ የቤተሰባችን አባላት ይህን ለሀገርና ለትውልድ የሚሰራን ስራ በሙሉ አቅማችሁ እንድታግዙ ጥሪ እናቀርባለን።

•በውጭ ሀገር የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት ጠቃሚ ናቸው የምትሏቸው መፅሃፍት በመላክ አልያም እዚህ ሀገር ባላችሁ ወዳጅና ዘመድ መፅሃፍት እንዲገዛ በማድረግ ይህን

#ኦሮሚያ
#አማራ
#ትግራይ
#ደቡብ
#ሱማሌ
#አፋር
#ሀረሪ
#ጋምቤላ
#ቤኒሻንጉል
#አ/አ ከተማ አስተዳደር
#ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር

🏷በማኛውም አይነት ቋንቋ የተዘጋጀ የመማሪያ መፅሃፍ መለገስ ይቻላል!!
-------------------------------------------------------
በአሁን ሰዓት ልየታ ከተደረገባቸው አካባቢዎች መካከል፦

#ራያ_ቆቦ በራያ ቆቦና ዙሪያዋ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት መፅሃፍት ለመለገስ እና ይህን ስራ ለማስተባበር ከቤተሰባችን አባል #ሉላይ ጋር ይገናኙ፦ +251949256094

#ድሬዳዋ በድሬዳዋ ከተማ እና አካባቢው የምትገኙ ደግሞ ከቤተሰባችን አባል መሃሪ 0915034762/መሃሪ/ ጋር መገናኘት መፅሃፍ መለገስ ትችላላችሁ።

ሌሎች አካባቢዎች ላይ እኛም ለሀገራችን መስራት እንፈልጋለን የምትሉ እውቅና ያላችሁ ማህበራት ካላችሁ መልዕክት አስቀምጡልን @tsegabwolde 0919743630

5ኛው አመት የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት የመፅሃፍ ማሰባሰብ ዘመቻ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ደቡብ_አፍሪካ

የዛምቢያ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን የፊታችን ቅዳሜ ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር ሊያደርገው የነበረውን የወዳጅነት ጨዋታ በአገሪቱ ባለው የዘረኝነት ጥቃት ምክንያት መሰረዙን አስታውቋል።

የጨዋታው መሰረዝ በዛምቢያ እና በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዜጎች ላይ በደቡብ አፍሪካ እየደረሰ ባለው የዘረኝነት ጥቃት እና መንግስት ጥቃቱን ለማስቆም ባሳየው ቸልተኝነት ምክንያት መሆኑ ታውቋል።
የዛምቢያ መንግስት የጸጥታው ሁኔታ እስኪሻሻል ድረስ የከባድ ተሽከርካሪ ሹፌሮች ወደ ደቡብ አፍሪካ እንዳይጓዙም አስጠንቅቋል።

በተመሳሳይ ዜና...

ታዋቂው የናይጄሪያ ድምፃዊ ቡራን ቦይ በዘርኝነት ጥቃቱ ምክንያት በጭራሽ ወደ ደቡብ አፍሪካ መጓዝ እንደማይፈልግ ተናግሯል።
ናይጄሪያም በደቡብ አፍሪካ ያሉ ዜጎቿ ላይ የሚደርሰው ጥቃት እንዲቆም አስጠነቅቃለች።

አቡጃ ባወጣችው መግለጫ በተለያዩ የደቡብ አፍሪካ ከተሞች የሚገኙ ዜጎቿን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ለመውሰድ መዘጋጀቷን ይፋ አድርጋለች።
የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ጥላቻን የሚያራምዱ ደቡብ አፍሪካዊያን በናይጀሪያዊያን ላይ ያደረሱት ጥቃት መንግስትን በእጅጉ አስቆጥቷልም ተብሏል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ መሃመት በበኩላቸው በደቡብ አፍሪካ ባሉ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ዜጎችን ኢላማ አድርጎ እየተፈፀመ ያለውን ጥቃት አውግዘዋል።

ሊቀ መንበሩ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ወደ ደቡብ አፍሪካ በማቅናት በንግድ ስራ ላይ በተሰማሩ ሰዎች ላይ ንብረት መዝረፍ እና ማውደምን ጨምሮ ሌሎች እየፈፀሙ ያሉ ድርጊቶችን ክፉኛ ኮንነዋል። የደቡብ አፍሪካ ባለስልጣናት አጥፊዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል መጀመራቸውንም ሊቀ መንበሩ የሚበረታታ ተግባር ነው ብለዋል።

Via #EBC
@tikvahethiopia
የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ እስካሁን ከ80 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በቁጥጥር ስር አውሏል። #ደቡብ_አፍሪካ #SouthAfrica
#ደቡብ_ሱዳን

የደቡብ ሱዳን ውጭ ጉዳይ ም/ሚኒስትር ሀገራቸው የናይል ወንዝን በመጠቀም ሀይል ማመንጫ ግድብ ለመገንባት ዕቅድ ማዘጋጀቷን አሳወቁ።

ም/ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴንግ ዳው ዴንግ ማሌክ ለናሽናል ጋዜጣ በሰጡት ቃል፥ ከዕርስ በርስ ጦርንት የተላቀቀችው ደቡብ ሱዳን ወደ ኢንዱስትሪ መር የገበያ ስርዓት ለመሸጋገር የሚያስችል ሀይል ማመንጫ ግድብ ለመገንባት የሚስችል ገንዘብ አላት ብለዋል።

ፕሮጀክቱ መንግስት ከነዳጅ ሽያጭ በሚያገኘው ገቢ ለመገንባት ዕቅድ ከተያዙ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ መሆኑን ተገልጿል።

ደ/ሱዳን ርካሽ፣ ታዳሽና በሀገሪቱ በየጊዜው የሚከሰተውን የጎርፍ አደጋ መከላከል የሚያስችል የግዙፍ ግድብ ግንባታን በይፋ ለማስጀመር ዕቅድ መያዟን ተናግረዋል፡፡

ሀገሪቱ በየወቅቱ በሚፈጠር የጎርፍ አደጋ፣ በሀይል እጥረት፣ የውሃ እጥረትና በደካማ የመሰረተ-ልማት ችግር እንደምትሰቃይ ጠቅሰዋል።

ወደ ኢንዱስትሪ መሸጋገር የሚቻለው በቅድሚያ የሀይል አቅርቦት አስተማማኝ በሆነ መልኩ ማምረት ሲቻል እንደሆነና ግድቡ የሀይል ፍላጎትን ታሳቢ ያደረገ እንደሆነም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

ግድቡ ምን ያህል ርዝመት፣ ምን ያህል ውሃ መያዝና ምን ያህል ሀይል የሚያመነጩ ተርባይኖች ሊኖሩት እንደሚገባ የሚሳይ መነሻ ዝርዝር ዕቅድ እና ጥናት በሀገሪቱ የመስኖ ሚኒስቴር በኩል መከናወኑ በዘገባው ተመላክቷል፡፡

ደቡብ ሱዳን ይህን ግድብ የመገንባት ሉዓላዊ መብት እንዳላት ምክትል ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ እየገነባች ባለው ግድብ ሚነሱ አለመግባባቶች በትብብር መንፈስ በውይይት ሊፈታ ይገባል ብለዋል።

www.thenationalnews.com/world/africa/south-sudan-poised-to-realise-nile-dam-dream-says-minister-1.1248408

#ENA

@tikvahethiopia
በደቡብ፣ ሐረሪ፣ እና ጋምቤላ ክልሎች የ2013 የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ዛሬ መሰጠት ተጀምሯል።

#ሐረሪ

በሐረሪ ክልል 56 በሚሆኑ የግል እንዲሁም የመንግስት ትምህርት ቤቶች ነው ተማሪዎች ፈተናው እየወሰዱ የሚገኙት ፤ በአጠቃላይ 5160 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተገልጿል።

ፈተናውን ለመስጠት 214 መምህራንና 24 የፈተና ጣቢያዎች መዘጋጀታቸው ተነግሯል።

#ጋምቤላ

በጋምቤላ ክልል ለ8ኛ ክፍል ፈተና 10 ሺህ 319 ወንድ እና 7 ሺህ 639 ሴት ተማሪዎች በድምሩ 17 ሺህ 958 የቀንና የማታ ተማሪዎች ተቀምጠዋል።

ፈተናው እየተሰጠ የሚገኘው በ186 የፈተና ጣቢያዎች ሲሆን 523 ፈታኞች ተሰማርተዋል።

#ደቡብ

በደቡብ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና በተለያዩ ዞኖች ከዛሬ ጥዋት አንስቶ እየተሰጠ ቢሆንም ምን ያህል ተማሪ ለፈተናው እንደተቀመጠና በስንት ጣቢያ ፈተናው እየተሰጠ እንደሆነ ይፋዊ መረጃ ማግኘት አልተቻለንም።

መረጃው የየክልሎቹ ትምህርት ቢሮ ነው።

@tikvahethiopia
" ሁለቱም ወገኖች ሰላም፣ ጸጥታና የኢትዮጵያ መረጋጋት ምኞታቸው መሆኑን ገልፀውልኛል " - ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ

በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ የመንግስትን እና የህወሃትን አመራሮችን ማነጋገራቸውን ካስታወቁ በኋላ መግለጫ አውጥተዋል፡፡

ኦባሳንጆ ሁሉም ወገኖች ወታደራዊ ፍልሚያውን እንዲያቆሙ ጠይቀዋል፡፡

ከመንግስትም ሆነ ሽብርተኛ ተብሎ ከተፈረጀው ህወሃት በኩል የሰላም ፍላጎቶች መኖራቸውን የገለጹት ከፍተኛ ተወካዩ ‘የሰላም መንገዱ ምን ይሁን’ የሚለው ግን ልዩነታቸው እንደሆነ ጠቅሰዋል።

የአፍሪካ መሪዎችና ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ሕብረቱ የጀመረውን የማሸማገል ጥረት እንዲደፉ እና ግጭቱን ሊያባብሱ ከሚችሉ ነገሮች እንዲቆጠብም ኦባሳንጆ ጥሪ አቅርበዋል።

ኦባሳንጆ፥ "ሆን ተብሎም ይሁን ባለማወቅ ግጭቱን የሚባብሱና ወደከፋ ደረጃ ከሚያደርሱ ንግግሮች መቆጠብ ያስፈልጋል" ብለዋል ።

ኦባሳንጆ፤ ውጊያው ከቆመ የንግግር ዕድል እንደሚኖር የገለጹ ሲሆን አሁን ባለው ሁኔታ ውጊያ እየተደረገ ግን ለመነጋጋር የሚመች እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

ኦባሳንጆ ፥ የኦሮሚያ እና አማራ ክልል አመራሮችን ማግኘታቸውን በመግለጫቸው ላይ የገለፁ ሲሆን በቀጣይ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ የአፋር ክልል አመራሮችን እንደሚያገኙ አሳውቀዋል።

ኦባሳንጂ ይህ የማሸማገል ስራ እንዲሳካ ቁርጠኛ እንደሆኑ የገለጹ ሲሆን ፦
- #የኬንያ
- #ኡጋንዳ
- #ጅቡቲ
- #ደቡብ_ሱዳን
- #ሶማሊያ እና ሱዳን መሪዎችን ማግኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት አስማሚ ሁኔታ ይፈጠራል ብዬ አስባለሁ ያሉት ኦባሳንጆ ሁለቱም ወገኖች ሰላም፣ ጸጥታና የኢትዮጵያ መረጋጋት ምኞታቸው መሆኑን እንደገለጹላቸው አሳውቀዋል።

Credit : #Al_AIN
Pic : AU

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ደቡብ_አፍሪካ

ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ ከወትሮ ለየት ከባድ ዝናብ በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ላይ እየጣለ ይገኛል:: ሰሞኑን የጣለው ይህ ከባድ ዝናብ በኳዙሉናታል፣ ፑማላንጋ እና ሊምፖፖ እንዲሁም ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ግዛቶች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ ጉዳት አድርሷል።

ይህን ተከትሎ ጆሃንስበርግ ከተማ እየጣለ ባለው ከፍተኛ መጠን ያለው ዝናብ ምክንያት የ " አስቸኳይ ግዜ ምላሽ " ለመስጠት በተጠንቀቅ ላይ ነች ሲል የሀገሪቱ ሚዲያዎች ዘግቧል። ዝናቡ ቀጣይነት ሊኖረው ስለሚችል የደቡብ አፍሪካ ነዋሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።

በደቡብ አፍሪካ የምትኖሩት ኢትዮጵያውያን ቤተሰቦቻችንም ጥንቃቄ ታደርጉ ዘንድ እናሳስባለን።

Video:- eNCA

Fa ya
(Tikvah-Family)
South Africa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትክክለኛ ፍትህ እንፈልጋለን " ህይወታቸውን ሙሉ ደክመው ያፈሩት ንብረታቸው በአንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ዶግ አመድ ሆኖባቸው የሰው እጅ ለማየት የተገደዱ ወገኖቻችን " ፍትህ እንፈልጋለን " እያሉ ነው። ሰሞኑን በደቡብ ክልል፤ ደቡብ ኦሞ ዞን ፤ ደቡብ አሪ ወረዳ ከዞን የመዋቅር ጥያቄ ጋር በተያያዘ በተነሳው የፀጥታ ችግር በርካቶች ንብረታቸው ወድሞ ከገዛ ቤታቸው ተፈናቅለው በየትምህርት ቤቱ እና መንግስት…
#ደቡብ_ኦሞ

🗣 " መልሶ ማቋቋም የተባለው ፖለቲካዊ ይዘት ያለው እንጂ ያለውን ችግር የሚፈታ አይደለም አቤት የምንልበት አጥተናል " - ተፈናቃዮች

🗣 " 72 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ እየተሰራ ሲሆን እስከ ሰኔ ድረስ የወደሙ ቤቶች ለመገንባትና ነዋሪዎችን ወደቀያቸው ለመመለስ ጥረት እየተደረገ ነው " - አቶ ባንቄ ኩሜ

በፀጥታ ችግር ሳቢያ በደቡብ ኦሞ ዞን " አሪ ወረዳ " የተፈናቀሉ ዜጎች ችግር ላይ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አንድ ተፈናቅለው በመጠላያ ጣቢያ የሚገኙ የቶልታ ነዋሪ ፥ " ያለንበት ችግሩ ተዘርዝሮ አያልቅም " ብለዋል ። መንግስት ነገሮችን የማለሳለስ ስራ ነው የሰራው አንድም የተሰራ ስራ የለም፤ ህዝቡ ያለው ሜዳ ላይ ነው እስካሁን ድረስ ፣ ዝናብ እና ፀሃይ ይፈራረቅበታል፣ ተጨናንቆ ነው ያለው አንድ ትምህርት ቤት ውስጥ በአንድ ክፍል እስከ 50 እና 60 ሰው ነው ያለው ፤ ይህ ለጤናም አስጊ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

እኚሁ ተፈናቃይ የጠየቀን አካል የለም መልሶ ማቋቋም የተባለውም ፖለቲካዊ ይዘት እንጂ የተፈናቃዮችን ችግር የሚፈታ አይደለም ፤ አቤት የምንልበትንም አጥተናል ሲሉ ገልፀዋል።

ተፈናቃዩ ፥ " ሰላሙን በትክክል አስጠብቆ ፣ ህዝቡን ወደቦታው መልሶ ማቋቋም አለበት ብለን ነው እኛ እየጮህን ያለነው። ነገር ግን የተደረገ ነገር የለም። ከወር በላይ ሆኖናል አሁን ዝም ብሎ ቦታውን በዶዘር እንደለድላለን ብሎ የአንድ ሰው ነው የሁለት ሰው ቤት እንደደለደለ ይኸው ሰላም ወርዷል በሚል የተለያየ ነገር በሚዲያ የማሰራጨት ስራ ነው እየተሰራ ያለው ይሄ የፖለቲካ ስራ ነው እየተሰራብን ያለው " ብለዋል።

አንድ ሌላ የቶልታ ተፈናቃይ መምህር ደግሞ ለስምንት አመታት ባስተማሩበት ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙ ገልፀው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ለችግር መጋለጣቸውን ገልፀዋል።

ሌላ ጥቃትም ይደርስብናል ብለን ስጋት ላይ ነን ሲሉም አስረድተዋል።

"ያየን ሰው የለም" የሚሉት እኚሁ መምህር የተደረገም ድጋፍ እንደሌለ አንስተዋል።

የደቡብ ኦሞ ዞን እርሻና ተፈጥሮ ሃብት መምሪያ ኃላፊ አቶ ባንቄ ኩሜ የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ወደ ቀያቸው ለመመለስ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው ብለዋል። ምግብ ነክ እንም ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎች እየቀረበ ነው ሲሉም ተፈናቃዮች የሚያነሱትን ቅሬታ ውድቅ አድርገዋል።

የተሠጠው ድጋፍ ለ1 ወር ከ15 የሚበቃ ነው ሲሉም ገልፀዋል።

መልሶ ለማቋቋም ፤ 72,000,000 ብር ለማሰባሰብ እየተሰራ መሆኑን እና እስከ ሰኔ ድረስ የወደሙ ቤቶች ተመልሰው ተገንብተው ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው እና ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

የዞኑ የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሞ በዛብህ በበኩላቸው የፀጥታ ችግር ተፈጥሮ የነበረባቸው ወረዳዎች ወደ ቀደመው ሰላማቸው ተመልሰዋል ብለዋል።

በወንጀል የተጠረጠሩ ከ1400 በላይ ሰዎች በወቅቱ ታስረው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን እና ከፍተኛ ተሳትፎ ያላቸውን እና መሪ ሚና የተጫወቱት ላይ ክስ ለመመስረት በሂድት ላይ ነው ብለዋል።

ለአሁን ላይ ተፈናቃዮች የማያቀርቡትን የደህንነት ስጋት በተመለከተ ፥ " አሁን ባለው ሁኔታ ጥቃት የሚያደርስ አካል አለ ወይ ብለን ስንገመግም ብዙም የለም " ሲሉ ተናግረዋል።

Credit : ቪኦኤ / ጋዜጠኛ ዮናታን ዘብዲዮስ

@tikvahethiopia
#ደቡብ_አፍሪካ | " በ3 ወራት በትንሹ 6,000 ሰዎች ተገድለዋል "

ከፍተኛ የሆነ የወንጀል ድርጊቶች ይፈፀምባቸዋል ተብለው ከሚጠሩ ሀገራት አንዷ ደቡብ አፍሪካ ናት።

ከፖሊስ በወጣ ሪፖርት መሰረት በሀገሪቱ በሶስት ወራት በትንሹ 6,000 ሰዎች ተገድለዋል።

በጥር እና መጋቢት መካከል 6,083 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ካለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር (4,976 ነበር) የ22.2 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል።

ከግድያ በተጨማሪ የፆታዊ ጥቃት ጋር በተያያዘ የተፈፀሙ ወንጀሎች በ13.7 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን 10,818 ሰዎች ተደፍረዋል።

እገታ እና አፈናም በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን 3,306 ኬዞች ሪፖርት ተደርጓል ፤ ይህም ከአንድ አመት በፊት ከነበረው በእጥፍ ይበልጣል ተብሏል።

የሀገሪቱ ፖሊስ " የዚህ አመት የመጀመሪያዎቹ 3 ወራት ጨካኔ የተሞላበት እና ለብዙ ደቡብ አፍሪካውያን ደህንነታቸው ያልተጠበቀ ነበር " ብሏል።

" ብቻዬን ከሚሰሩ ወንጀሎች ጋር ተፋልሜ ላሸንፍ አልችልም " ያለው የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ " ከማህበረሰቡ ጋር በጠንካራ እምነት ላይ የተገነባ ጥልቅ አጋርነት ያስፈልገኛል " ሲል ገልጿል።

#TikvahFamilySouthAfrica

@tikvahethiopia
የመንገደኞች እንግልት እና የመንግስት አካላት ምላሽ !

ከአማራ ክልል በተለይም #ከሰሜን እና #ደቡብ_ወሎ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ ለመግባት ብዙዎች እየተንገላቱ ነው።

ይህ ጉዳይ አንድ ወቅት ጠንከር አንዴ ላላ ፤ ያዝ ለቀቅ እያደረገ አሁንም ድረስ ቀጥሏል።

አንዳንዶች በብዙ ልመና ነው የሚያልፉት።

ወደ መጣችሁበት ተመለሱ የሚባሉ ወገኖች ምክንያት ቢጠይቁም በግልፅ አስረድቶ የሚነግራቸው አላገኙም።

ለመሆኑ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቻችን ምን አሉ ?

👉 " ... መላ ሊባልለት የሚገባ ነገር ነው። ከደሴ ተነስተን ወደ አ/አ እየሔድን ነበር ግን " ሸኖ " ላይ የአማራ ክልል መታወቂያ ይዛችሒ አትገቡም ተብለን ስንጉላላ ቆይተን ሹፌሩ ይዘሐቸው ተመለስ ተብሏል። ሌሎቹ ተመልሰዋል። እኔ ግን ግድ መሔድ ስላለብኝ ለፈተና ባጃጅም በግሬም ኡ/ ገብቻለሁ ፡፡ እባካችሁ ዛሬ ብቻ አደለም ያዝ ለቀቅ እያደረጉ ነው እንጅ ከብዶናል "

👉 " እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አሁንም ድረስ ከወሎ መዳረሻቸውን አ.አ አርገው የሚመጡ ተሳፋሪዎች ከበኬ ኬላ አየተመለሱ አሌልቱ ላይ ብዙ እንግልት እየገጠማቸው ይገኛል "

👉 " ወደ አዲስ አበባ አትገቡም ተብለው ብዙዎች ሲንገላቱ ቆይተው ወደ ኃላ እንዲመለሱ ተደርገዋል። እኛ በብዙ ልመና ለህክምና ነው ብለን አልፈናል። "

#ሪፖርተር_ጋዜጣ ያነጋገራቸው ፦

👉 " ሐምሌ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. መነሻችንን ከወልዲያ ከተማ አድርገን ወደ አዲስ አበባ ስንጓዝ የአማራ ክልልን አልፈን ኦሮሚያ ክልል ስንገባ ተደጋጋሚ ፍተሻ ተደርጎልናል። ለገዳዲ ከደረስን በኃላ ግን የአዲስ አበባ መታወቂያ የላችሁም በሚል ምክንያት ወደ ደብረ ብርሃን መልሰውናል። ሁኔታው በጣም አሳዛኝ ነው ።

ከሸኖ ከተማ ጀምሮ እስከ ሰንዳፋ ድረስ የተደረገብን ፍተሻ በጣም አድካሚ ከመሆኑም በላይ፣ የአዲስ አበባ መታወቂያ የላችሁም በሚል ሲሳለቁብን ማየት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ አሳፋሪ ተግባር ነው።

ፖሊሶች ፍተሻ ካደረጉ በኋላ የአዲስ አበባ መታወቂያ የሌላቸውን እዚያው ክልላቸው ወስደህ አውርዳቸው በማለት ለሾፌሩ ተናግሯል።

በዚህም የተነሳ በግዴታ ለገዳዲ ከደረስን በኋላ እንደገና ተመልሰን ደብረ ብርሃን ከተማ አድረናል። በስተመጨረሻም በነጋታው የቤት መኪና ተከራይተን ለቅሶ እንደምንሄድ በመናገር አዲስ አበባ ገብተናል።

የተፈጠረውን ክስተት አስከፊ ነው። በጊዜው ገንዘብ ስለነበረን ከፍለን ተመለስን ነገር ግን ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ከመኪና እንዲወርዱ ሲደረጉ ሕፃን ልጅ የያዙ እናቶች ጭምር ለመመለሻ የሚሆን ገንዘብ አጥተው ሜዳ ላይ ወድቀው ነበር።

ይህን ያህል አማራ ምን አድርጎ ነው ? ወስደህ አውርዳቸው እንዴት ይባላል ? ኢትዮጵያዊ አይደለንም ወይ ? ብዙ ግፍ ያለበት ክልል እኮ ነበር፣ በአማራ ላይ ይህ ሁሉ ሲደረግ ሕግ አለ ወይ ያስብላል ? "

👉 " አደራው ኃይሌ እባላለሁ ከደሴ ከተማ ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ እየተጓዝኩ ነበር 100 ኪሎ ሜትር በማይሞላ ርቀት ውስጥ ከጫጫ ከተማ እስከ ለገዳዲ ከተማ ቢያንስ 7 ጊዜ ተፈትሸናል።

የመጨረሻው የአዲስ አበባ መግቢያ ፍተሻ በነበረው ለገዳዲ ስንደርስ ከጥቂት የአዲስ አበባ ከተማ መታወቂያ ከያዙ ሰዎች ውጪ ቀሪዎቹ ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ድርጊቱ በጣም የሚያሳዝን ነው።

ከመኪና እንድንወርድ ከተደረገ በኋላ ስልካችንን ከፍተን በውስጥ ያሉ ምሥሎችና ድምፆችን ከፍተን እንድናሳይ ተደርጓል።

👉 " ሁኔታው የሕግ ድጋፍ ያለው እንደማይመስልና አልፎ አልፎ ፖሊሶቹ በመሰላቸው አሠራር እንጂ እንዲህ ዓይነት ድርጊት የሚፈቅድ ምንም ዓይነት የሕግ መሠረት ማቅረብ አይቻልም።

ድርጊቱ አሳፈሪ በመሆኑ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ለጉዳዩ አፋጣኝ መልስ መስጠት ካልቻለ፣ እንደ አገር አብሮ በኖረ ሕዝብ ላይ አሁን ያለው የፖለቲካ ግለት ተጨምሮበት የባሰ ቁርሾ፣ እርስ በርስ የመለያየትና ከፋፋይ የሆነ አጀንዳ ይሆናል "

የመንግስት አካላት ምን አሉ (ለሪፖርተር ጋዜጣ) ?

▪️የአማራ ክልል የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ፦

" ጉዳዩ ስለመከሰቱ መረጃ አለኝ። ነገር ግን የሕወሓት ሠርጎ ገቦችን ለመያዝ በሚል ግልጽ ባልሆነ መንገድ ዜጎች እየተንገላቱ በመሆኑ ጉዳዩን ለኦሮሚያ ክልል መፍትሔ እንዲሰጥበት አሳውቀናል። "

▪️የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ አራርሳ መርዳሳ ፦

ጥያቄ ከሰሙ በኋላ መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

▪️የሰሜን ሸዋ ዞን የፀጥታና አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ብርሃኑ ፦

" ጉዳዩ መከሰቱን መረጃ አለኝ።

ተሳፋሪዎች ደብረ ብርሃን ከተማ ካለፉ በኋላ እንዲህ ዓይነት ችግር ተፈጥሯል።

ከኦሮሚያ ክልልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ደውላችሁ አጣሩ "

▪️የአዲስ አበባ የፀጥታ ቢሮ የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ ፦

" ስለሚባለው ጉዳይ ምንም ዓይነት መረጃ የለንም "

▪️የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ፦

" የተጠቀሰው ጉዳይ አይመለከተንም "

▪️ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሪት ሰላማዊት ካሳ ፦

" ጉዳዩ የሕወሓት የሽብር ቡድን በወረራ ይዟቸው ከነበሩት የአማራ ክልል አካባቢዎች የተለያዩ የመታወቂያ ማኅተሞችና የአስተዳደር ሰነዶችን በመዝረፉና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እነዚህን ሐሰተኛ መታወቂያዎች ሰነዶችን የያዙ ሠርጎ ገቦች ወደ አዲስ አበባ ሊገቡ ሲሉ በመያዛቸው ምክንያት የሚደረግ የክትትል ሥራ ነው።

የጥፋት ተልዕኮ የያዙና ከአማራ ክልል ተዘርፈው በተወሰዱ ሰነዶች ተመሳስለው የተሰሩ መታወቂያዎችን የያዙ ግለሰቦች አሁንም ወደ አዲስ አበባ ለመግባት የሚያደርጉት ጥረት እንዳለ ለፀጥታ ኃይሎች መረጃው በመድረሱ ይህንን ለመከላከል ጥብቅ ፍተሻዎችና ማጣራቶች እየተደረጉ ነው።

ይሁን እንጂ አዲስ አበባን የጥፋት ተልኳቸው መዳረሻ ለማድረግ እየሞከሩ ያሉትን አካላት ለመከላከል በሚወሰደው ዕርምጃ፣ በመንገደኞች ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩንና ዜጎችም ለእንግልት እየተዳረጉ መሆኑን የተመለከቱ ቅሬታዎች ደርሰውናል።

ይህም በደኅንነት ፍተሻና ማጣራት አፈጻጸም ላይ መሻሻል ያለበትን ሁኔታ ለይቶ የፀጥታ ኃይሉ የማስተካከያ ዕርምጃ እንዲወስድ ይደረጋል ። "

▪️የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልና የአብን ከፍተኛ አመራር አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ ፦

" ... ከአማራ ክልል የወሎ አካባቢዎች ተነስተው መዳረሻቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዜጎች ኦሮሚያ ክልል ሸኖ ሲደርሱ መታወቂያቸው እየታየ ከተሳፈሩበት መኪና እንዲወርዱና ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጉን ተጨባጭ መረጃዎች አሉ።

የሚመለከታቸው የፌዴራልና የኦሮሚያ ክልል የሥራ ኃላፊዎች በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለውን መጉላላትና አግላይ የነውር ተግባር ታስቆሙ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 12ኛ ክልል እንዲቋቋም ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ተወሰነ። የፌዴሬሽን ምክር ቤት 12ኛ ክልል እንዲቋቋም የሚያስችል ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወስኗል። ምክር ቤቱ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ስር የነበሩ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ተቀብሎ ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወስኗል። ሕዝበ ውሳኔ የሚያካሂዱት ፦ - የወላይታ ዞን፣…
#ደቡብ_ኢትዮጵያ_ክልል

" በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንዲደራጅ "

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ፦
- የወላይታ፣
- የጋሞ፣
- የጎፋ፣
- የደቡብ ኦሞ፣
- የጌዴኦ፣
- የኮንሶ ዞኖች እንዲሁም
- የደራሼ፣
- የአማሮ፣
- የቡርጂ፣
- የአሌ፣
- የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በጋራ " የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " ለመመስረት ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጿል።

ም/ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት እንዲያስችል የሕዝብን ይሁንታ ማረጋገጥ በማስፈለጉ ከማንኛውም ተጽእኖ ነጻ በሆነ መልኩ ገለልተኛ በሆነው ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ አማካኝነት በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ ሕዝበ ውሳኔ እንዲደራጅ ወስኗል።

የሕዝብ ውሳኔው ውጤት ሪፖርትም ለምክር ቤቱ እንዲቀርብ፣ እንዲሁም የሕዝብ ውሳኔው ሂደት ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና የሕዝብን ሰፊ ተሳትፎ ባረጋገጠ መልኩ እንዲጠናቀቅ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮችና የጸጥታ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል።

በሌላ በኩል ምክር ቤቱ የሀድያ ፣ ሀላባ ፣ ከምባታ ጠምባሮ፣ ስልጤ፣ ጉራጌ  ዞኖችና የም ልዩ ወረዳ በነባሩ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አንድ ላይ የሚቀጥሉ ይሆናል ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የደሴ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ የከተማዋን ሰላም ሊያስጠብቁ እንደሚገባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ገልጿል። ነዋሪዎች በሚነዙ ሀሰተኛ ወሬዎች፣ መረጃዎችና አሉባልታ አትደናገሩ ብሏል። ማንኛውም የተለየና አጠራጣሪ ነገር ሲመለከቱ ነዋሪዎች ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ተጠይቋል። ከተለያዩ አከባቢዎች ለመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ነገር…
#Update

#ደቡብ_ወሎ

በደቡብ ወሎ ከታች ቀበሌ እስከ ዞን ድረስ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ህዝቡን እንዲረጋጋ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ተብሏል።

በዞኑ ባሉ ወረዳዎች ውስጥ የሀገር መከላከያን ልብስ በመልበስ መከላከያ በመምሰል በአቋራጭ መንገዶች ሲጓዙ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።

በአሉባልታ ከሰሜን ወሎ ዞን የተፈናቀሉ በርካታ ሰዎች ወደ ዞኑ እየገቡ መሆኑን የገለፀው የደቡብ ወሎ ዞን ከሰሜን ወሎ ዞን ጋር በመሆን መመለስ ያለባቸውን ተፈናቃዮች እና ሰሌዳ አልባ ተሽከርካሪዎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል።

#አምባሰል_ወረዳ

በአምባሳል ወረዳ ሀሰተኛ አሉባልታ ሲነዙ እና ህብረተሰቡን በማወክ ዘረፋ ሊፈፅሙ ተዘጋጅተው የነበሩ 9 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።

መላው ነዋሪ በሀሰተኛ ወሬና አሉባልታ ሳይደናገጥ በፍፁም መረጋጋት አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቦለታል።

#ሐይቅ

በሐይቅ ከተማ " ከዚህ ቀደም ህወሓት ቀብሮት የነበረ ከባድ እና ቀላል መሳሪያ ተገኘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የከተማው ፖሊስ አሳውቋል።

የህብረተሰቡን ሰላም ለማወክና አካባቢው እንዳይረጋጋ እንዲሁም ተከታይ ለማብዛት ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

" ምንም ባላያችሁበትና ባላረጋገጣችሁበት አዲስ አበባ ቁጭ ብላችሁ በሀሰተኛ መረጃ ህዝብ የምትረብሹ ኃላፊነት የጎደላችሁ የማህበራዊ አንቂ ነን የምትሉ ግለሰቦች፣ ዩትዩበሮች ከድርጊታችሁ ታቀቡ " ያለው የሐይቅ ፖሊስ ይህን የፈፀሙት ላይ በህግ እንዲጠየቁ እየሰራው ነው ብሏል።

ነዋሪዎች በሀሰተኛ መረጃ ይስደናገጡ በተረጋጋ ሁኔታ የአካባቢውን ሰላም በንቃት እንዲጠብቁ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አምባሳደር ማይክ ሐመር ኬንያ ይገኛሉ። የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ከአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር ጋር ተነጋግረዋል። ፕሬዜዳንት ሩቶ ከአሜሪካው አምባሳደር ሐመር ጋር ያደረጉትን ንግግር ተከትሎ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ፤ " ሰላምና መረጋጋት ለአገሮች ልማትና ብልፅግና የግድ አስፈላጊ ነው " ያሉ ሲሆን ኬንያ ፤ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ በተለይም…
#Update

አምባሳደር ማይክ ሐመር ኢትዮጵያ ይገኛሉ።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛው አምባሳደር ማይክ ሐመር በአሁን ሰዓት ኢትዮጵያ የሚገኙ ሲሆን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር #ዛሬ ውይይት አካሂደዋል።

አቶ ደመቀ መኮን በውይይቱ ወቅት ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈጠረው ግጭት በሰላም እንዲፈታ ቁርጠኛ መሆኑን መግለፃቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

አምባሳደር ማይክ ሐመር በበኩላቸው፤ አሜሪካ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለሚካሄደው የሰላም ድርድር ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፀዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር " በውይይቱ ረጅም ዘመን ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነት ይበልጥ አጠናክሮ ለመቀጠል ተስማምተዋል " ሲል አሳውቋል።

አምባሳደር ማይክ ሐመር ከቀናት በፊት #ኬንያ እንደነበሩና ከኬንያው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ጋር መምከራቸው ይታወሳል።

አሜሪካ አምባሳደር ሐመርን ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአፋጣኝ እንዲቆም እና በአፍሪካ ህብረት የሚመራ የሰላም ድርድር እንዲጀመር ለመደገፍ ወደ ኬንያ ፣ #ደቡብ_አፍሪካ ፣ ኢትዮጵያ እንደላከች ማሳወቋ የሚዘነጋ አይደለም።

Photo Credit : Ministry of Foreign Affairs of Ethiopia

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ #ደቡብ_ሲዳን

የኢፌዴሪ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ዛሬ ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ልዑካቸው #ጁባ ሲደርሱ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት ይፋዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደቡብ ሱዳን የገቡት ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#ደቡብ_አፍሪካ

• " የመንግሥት ለውጥ በምርጫ እንጂ በግርግር  አይመጣም " - ፕሬዜዳንት ሲሪል ራማፎሳ

• " መንግሥት እየተንቀጠቀጠ ነው ፤ ፈርቷል " - የራማፎሳ ተቃዋሚ ጁሊየስ ማሌማ (የኤኮኖሚ ነጻ አውጪዎች ፓርቲ)

• በተቃውሞው ሳቢያ የንግድ መደብሮች ገና ካሁኑ ሥጋት አድሮባቸዋል።

#በመጪው_ሳምንት በደቡብ አፍሪካ የተቃውሞ ሰልፍ ይካሄዳል ተብሎ ታቅዷል።

በዚህም ሳቢያ የአገሪቱ መንግሥት ቁልፍ የሚባሉ መሠረተ-ልማቶችን ለመጠበቅ እና የጸጥታ ጥበቃውን ለማጠናከር የሀገሪቱን ጦር (ወታደሮች) እንዳሰማራ ዶቼ ቨለ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ጁሊየስ ማሌማ የሚመሩት ግራ ዘመም የኤኮኖሚ ነጻ አውጪዎች ፓርቲ በመጪው ሰኞ በመላ ደቡብ አፍሪካ የሥራ ማቆም አድማ መጥራቱ ተነግሯል።

ፓርቲው ፕሬዝደንት ሲሪል ራማፖሳ የደቡብ አፍሪቃን ኤኮኖሚ በመሩበት ስልት፣ በመብራት እጥረት እና እየበረታ በሚሔደው የሥራ አጥነት ሳቢያ ከሥልጣን መልቀቅ አለባቸው የሚል አቋም አለው።

የደ/አፍሪቃ ጦር ለአገሪቱ ፖሊስ እገዛ እንዲያደርግ መታዘዙን አስታውቋል።

ጦሩ በእጁ በሚገኙ የስለላ መረጃዎች መሠረት ሥጋት አለባቸው የተባሉ ቁልፍ ቦታዎችን ለመጠበቅ ከትላንት አርብ ጀምሮ ለአንድ ወር ወታደሮች አሰማርቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ከጸጥታ አስከባሪ ተቋማት አቅም በላይ ለሚፈጠሩ ኩነቶች ወታደሮች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል።

የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዝደንታዊ ምርጫ አንድ ዓመት የቀረው ሲሆን ፕሬዜዳንት ራማፎሳ የታቀደው ሰልፍ " ፖለቲካዊ ሴራ ነው "  የሚል አቋም አላቸው።

ፕሬዜዳንቱ ባለፈው ሐሙስ " ሥርዓተ-አልበኝነት እና ግርግር እንደማይፈቀድ " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ራማፎሳ የመንግሥት ለውጥ " በምርጫ እንጂ በግርግር " እንደማይመጣም ገልጸዋል።

የኤኮኖሚ ነጻ አውጪዎች ፓርቲ መሪ ጁሊየስ ማሌማ ትላንት በስዌቶ ለደጋፊዎቻቸው " ማንም አብዮትን ሊያስቆም አይችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

" መንግሥት እየተንቀጠቀጠ ነው፤ ፈርቷል " ያሉት ማሌማ ራማፎሳ ከሥልጣን እንዲወርዱ ጠይቀዋል።

በተቃውሞው ሳቢያ የንግድ መደብሮች ገና ካሁኑ ሥጋት እንደገባቸው የፈረንሳይ ዜና አገልግሎትን ዋቢ በማድረግ ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
ስለብፁዕነታቸው የሚሰራጨው መረጃ ፍጹም ሐሰተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አሳወቀች።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ወደ #ደቡብ_አፍሪካ ሊያደርጉ የነበረውን ጉዞ መሰረዛቸውን ተከትሎ #የሐሰት_ዜና በመሰራጨት ላይ እንደሚገኝ ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፦
- በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ጆሐንስበርግ መንበረ ጵጵስና ጽርሐ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተበት ፳፭ኛ ዓመት በዓል ላይ ለመገኘት፣
- ቅዳሴ ቤቱን ለማክበር
- በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናትን ለመባረክ
-  ምዕመናንን ለማስተማር ዛሬ ከቅዱስነታቸው ጋር ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ መርሐ ግብር ይዘው ነበር።

ይሁን እንጂ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ካለባቸው ተደራራቢና አስቸኳይ ሥራዎች አንጻር ለ10 ቀናት ሙሉ ፦
° ከጽ/ቤታቸው ርቀው መቆየት በጠቅላይ ጽ/ቤቱ የዕለት ተዕለት ሥራዎች ላይ ክፍተት እንዳይፈጠር በመስጋታቸው
° ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊውና ምክትል ሥራ አስኪያጁ በሌሉበት ሁኔታ ለበርካታ ቀናት ከጠ/ጽሕፈቱ ርቀው ከተጓዙ ሥራዎች ስለሚበደሉ ቀደም ሲል ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊያደርጉት የነበረውን ሐዋርያዊ ጉዞ ከቅዱስነታቸው ጋር በጥሞና በመወያየት #ለመሰረዝ መገደዳቸው ተነግሯል።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በአንዳንድ ማኅበራዊ ገጾች ፈጽሞ እውነትነት በሌለው መንገድ " ብፁዕነታቸው ወደ ኤርፖርት እንዳይሔዱ እንደተከለከሉ እንዲሁም ፓስፖርታቸው እንደተያዘ " በማስመሰል የሚሰራጨው ዜና ፍፁም መሰረተ ቢስና የሐሰት ዜና መሆኑን ቤተክርስቲያን አሳውቃለች።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ከታቀደው ሐዋርያዊ ጉዞ ለመቅረት የተገደዱት በተደራራቢ ሥራ ምክንያት  መሆኑን እና የብፁዕነታቸው ፓስፖርትም ለጉዞ ሲባል ቀደም ብሎ ከሚመለከተው አካል መጥቶ በልዩ ጽሕፈት ቤቱ ጉዳይ አስፈጻሚ እጅ የሚገኝ መሆኑን ገልጻለች።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ከብፁዓን አባቶች ጋር ሆነው በዛሬው ዕለት ደቡብ አፍሪካ ፤ ጁሐንስበርግ ከተማ በሰላም የገቡ ሲሆን ምዕመናንም አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ደቡብ አፍሪካ ፦ https://telegra.ph/EOTC-05-10

@tikvahethiopia