TIKVAH-ETHIOPIA
1.49M subscribers
56.6K photos
1.41K videos
203 files
3.86K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና-አብዴፓ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥትና ከአፋር ብሔራዊ ዲሞክራሲዊ ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አመራር ጋር ባለፈዉ ሳምንት የጀመሩትን ዉይይት ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጥለዋል፡፡

በዚህ ዉይይት በአገር አቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ ያለውን ለውጥ በክልል ደረጃ እንዴት መካሄድ እንዳለበት ትኩረቱን ተደርጎበታል፡፡ በውይይቱ መጨረሻ ለውጡን የበለጠ ለማሳካት እንዲቻል ነባር የፓርቲ አመራሮች በአዲስ አመራሮች #እንዲተኩ ተወስንዋል።

ከዚህም በተጨማሪ የክልሉን ሰላምና ፀጥታ በበለጠ #በማጠናከር ህዝቡ የልማት ተጠቃሚነቱን የበለጠ ለማረጋገጥ እንዲቻል ሁሉም አመራር በጋር ለመስራት ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡

በሌላም በኩል የክልሉን ወጣቶችን ይበልጥ በማሳተፍ የህዝቡን የልማትና የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ለመመለስ አመራሮቹ ቃል ገብተዋል፡፡

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የተሰጠ መግለጫ፦

ሰላም ለሁሉም ዜጎች መሰረታዊ ፍላጎት እንደሆነ ይታወቃል። ይህን ለዜጎችም ይሁን ለሀገር ልማታዊ እድገት ጉልህ አስተዋፆኦ ያለውን ሰላም የፀጥታ ሀይሉ ጥረት ብቻውን እውን ሊያደርገው እንደማይችል ይታመናል።

እንደ #ሀዋሳ ተጨባጭ ሁኔታም ከተማዋን የፈጣን እድገት ተምሳሌት አድርጎ ቀጣይነቷን ለማረጋገጥ ይቻል ዘንድ ሁሉም የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅበት አያጠያይቅም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ጥቂት ሁከትን ለግል ፍላጎታቸው ማስፈፀሚያ የሚጠቀሙ ግለሰቦች እና #የተደራጁ_ሀይሎች በተለያዩ ጊዜያት የከተማዋን ሰላም ከማደፍረስ ባሻገር በሰው እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እንዲደርስም ጥረት ሲያደርጉ ይስተዋላል።

ከእነዚህ የፀረ ሰላም ሀይሎች #እኩይ ተግባራትም መካከል በትናንትናው እለት በከተማዋ በኢትዮጵያ ትቅደም ትምህርት ቤት የተደራጁ ወጣቶች የግቢውን አጥር በመስበር ሁከት ለመፍጠር ያደረጉትን ጥረት የፖሊስ ሀይሉ እና ህብረተሰቡ ባደረገው ርብርብ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

የእኚህ ፀረ ሰላም ሀይሎች አላማ ከውጭ ተደራጅቶ ወደ ትምህርት ቤቱ ግቢ በመግባት ሁከቱን ተማሪዎች የፈፀሙት በማስመሰል የግጭቱን ቅርፅና ይዘት ሌላ መልክ እንዲኖረው በማስመሰል የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።

ሆኖም የአካባቢው ህብረተሰብ ለፖሊስ ባደረሰው #ጥቆማ እና በስፍራው ከነበረው የፀጥታ ሀይል ሌላ ተጨማሪ ሀይል #በማጠናከር ሁከቱን ሊያባብሱ የሚችሉ የጦር መሳሪያዎችን ሳይቀር ፖሊስ በቁጥጥሪ ስር ሊያውል ችሏል። በዚህ የተቀናጀ የፖሊስ እና የህብረተሰቡ ጥረትም ቱርክ ሰራሽ 12 ሽጉጦች በሁለት ግለሰቦች እጅ መያዝ ተችሏል።

በተመሳሳይም ፖሊስ በሁከቱ ግንባር ቀደም በመሆን ሲመሩ ነበሩ ያላቸውን 36 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢው ምርመራም እያደረገ ይገኛል።

ሁከቱን ለመቆጣጠር ፖሊስ ባደረገው ጥረት ምንም አይነት የሰውም ሆነ የንብረት ውድመት ሳይደርስ ማቆም ቢችልም በጊዜው በድርጊቱ ፈፃሚዎች ይወረወሩ የነበሩ ድንጋዮች በተወሰኑት የፀጥታ ሀይሎች ላይ እና በተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት ግን ሊደርስ ችሏል።

በዚህ አጋጣሚ የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ የፀጥታ ሀይሉ እና የአካባቢው ህብረተሰብ ሁከቱን ለመቆጣጠር ላደረገው ርብርብ ምስጋናውን ማቅረብ ይወዳል።

ፖሊስ ይህን የፀጥታ ሀይሉ ከህብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት ለከተማዋ ሰላም እና ለዜጎች ደህንነት መረጋገጥ ጥረቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን እየገለፀ ሰላማዊት ሀዋሳን በጋራ እንገባ የሚል መልእክቱን በማቅረብ ነው።

ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ ዛሬ ከሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሙስጠፋ_ኡመርና የኢትዮጲያ ሶማሌ ክልል ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ #አህምድ_ሽዴ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ዉይይቱም የተኮረው በሶማሌ ክልል ልማትና ጸጥታ ጉዳዮች ላይ ሲሄን ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድም የክልሉን ልማት የበለጠ #በማጠናከር ረገድ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

#PMOffice
@tsegabwolde @tikvahethiopia
5ኛው አመት የTIKVAH-ETH የመፅሃፍት ማሰባሰብ ዘመቻ ከነገ ነሃሴ 20 እስከ መስከረም 30 በመላው ሀገሪቱ ይካሄዳል!!

ላለፉት አመታት በአብዛኛውን በከተሞች አካባቢ የሰራነውን ስራ #በማጠናከር ዘንድሮ ደግሞ ከከተማ ውጭ ወደሚገኙ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ትኩረታችንን እናደርጋለን።

ምን አይነት መፅሃፍት ነው ከቤተሰባችን አባላት የምናሰባስበው?

•ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ መደበኛ የመማሪያ መፅሃፍትን/Text Book/ እንዲሁም አጋዥ መፅሃፍት ብቻ

•በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ ትውልዱን ይጠቅማል፤ እውቀት ያስጨብጣል የምንላቸው መፅሃፍት።

•ትንሹ መስጠት የሚቻለው መፅሃፍ 1

•መፅሃፍቱ የሚገቡት ገጠራማ አካባቢ ለሚገኙ እና በአካል ሄደን ለምንለያቸው ቤተ መፅሃፍት

#እርሶ ምን ማድረግ ይችላሉ??

√ቢያንስ አንድ የመማሪያ መፅሃፍ ለሚወዷት ለኢትዮጵያ መለገስ ይችላሉ። እንዲሁም ከፍተኛ የመፅሃፍት ችግር ያሉባቸው ቦታዎችን በመለየት የማስተባበር ስራ ሊሰሩ ይችላሉ።

•TIKVAH-ETH በሀገሪቱ በየትኛውም አካባቢ ለምትገኙ የበጎ አድራጎት ማህበራት ይህን ሀገራዊ ስራ እንድታግዙ ጥሪውን ያቀርብላችኃል።

•የዘንድሮ ተፈታኝ ተማሪዎች ደግሞ ትልቁን ድርሻ በመውሰድ ከተማራቹባቸው እና ስትጠቀሟቸው ከነበሩት መፅሃፍ መካከል ቢያንስ አንዱን ለመጪው ትውልድ በስጦታ አበርክቱ።

•በStopHateSpeech ጉዞ ተሳታፊ የነበራችሁ የቤተሰባችን አባላት ይህን ለሀገርና ለትውልድ የሚሰራን ስራ በሙሉ አቅማችሁ እንድታግዙ ጥሪ እናቀርባለን።

•በውጭ ሀገር የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት ጠቃሚ ናቸው የምትሏቸው መፅሃፍት በመላክ አልያም እዚህ ሀገር ባላችሁ ወዳጅና ዘመድ መፅሃፍት እንዲገዛ በማድረግ ይህን

#ኦሮሚያ
#አማራ
#ትግራይ
#ደቡብ
#ሱማሌ
#አፋር
#ሀረሪ
#ጋምቤላ
#ቤኒሻንጉል
#አ/አ ከተማ አስተዳደር
#ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር

🏷በማኛውም አይነት ቋንቋ የተዘጋጀ የመማሪያ መፅሃፍ መለገስ ይቻላል!!
-------------------------------------------------------
በአሁን ሰዓት ልየታ ከተደረገባቸው አካባቢዎች መካከል፦

#ራያ_ቆቦ በራያ ቆቦና ዙሪያዋ የምትገኙ የቤተሰባችን አባላት መፅሃፍት ለመለገስ እና ይህን ስራ ለማስተባበር ከቤተሰባችን አባል #ሉላይ ጋር ይገናኙ፦ +251949256094

#ድሬዳዋ በድሬዳዋ ከተማ እና አካባቢው የምትገኙ ደግሞ ከቤተሰባችን አባል መሃሪ 0915034762/መሃሪ/ ጋር መገናኘት መፅሃፍ መለገስ ትችላላችሁ።

ሌሎች አካባቢዎች ላይ እኛም ለሀገራችን መስራት እንፈልጋለን የምትሉ እውቅና ያላችሁ ማህበራት ካላችሁ መልዕክት አስቀምጡልን @tsegabwolde 0919743630

5ኛው አመት የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት የመፅሃፍ ማሰባሰብ ዘመቻ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia