TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.36K videos
198 files
3.63K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ወታደሮችን እየመሩ የቦሊቪያው ፕሬዚዳንት አርሴ ቤተ መንግስትን በኃይል ሰብረው በመግባትና በመውረር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ያደረጉት ጄነራል ሁዋን ሆዜ ዙኒጋ በሀገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው እስር ቤት ገብተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት እና ምክትል ፕሬዜዳንት በጋራ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ አስገቡ። ስራ መልቀቂያውን ያስገቡት ፤ " በፍትህ እና የዳኝነት ሰርዓቱ ለውጥ ለማምጣት ያሰብናቸው ፣ ያቀድናቸው የጀመርናቸው ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች ለማሳካት የሚያስችል ሁኔታ ማግኘት ስላልቻልን ነው " ብለዋል። ሰኞ ሰኔ 17/2016 ዓ.ም የተፃፈው የስራ መልቀቅያ ደብዳቤ በበርካታ የማህበራዊ…
#Update

" ጊዚያዊ አስተዳደሩ ጥያቄያችን ለመመለስ ቃል ስለገባ የስራ መልቅቅያ ጥያቄያችን ትተነዋል " - የትግራይ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት

የትግራይ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንትና ምክትል ፕሬዜዳንት ያስገቡትን የመልቀቂያ ደብዳቤ እንደተውት አሳወቁ።

ፕሬዜዳንቱና ምክትል ፕሬዜዳንቱ ይፋ ባደረጉት መግለጫ ፤ ሰኔ 17 ቀን 2016 ዓ.ም ያቀረቡት የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ተከትሎ ሰኔ 18 /2016 ዓ.ም ከክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ውይይት ማደረጋቸውን ገልጸዋል።

በዚ ውይይት ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ለመመለስ ቃል በመገባቱ ስራ የመልቀቅ ጥያቄያቸውን እንደተውት አሳውቀዋል።

ያቀረቡዋቸው ጥያቄዎች ምን እንደሆኑ በግልፅ ያላብራሩ ሲሆን ከላይ እስከ ታች የሚገኘው የፍርድ ቤት አካል ስራውን ተረጋግቶ እንዲሰራ መልእክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዜዳንቱና  ምክትል ፕሬዜዳንቱ የስራ መልቀቂያ ማስገባታቸው ተከትሎ የወረዳና የዞን ፍርድ ቤቶች ስራ የማቆም አድማ መምታት ጀምረው ነበር

ከክልሉ ፕሬዜዳንት ከተደረገው ውይይት በኃላ ችሎቶች ተከፍተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መሆናቸው የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል በአካል ተዘዋውሮ ተመልክቷል።

ከመቐለ ውጪ በመላው ክልል ያሉ ፍርድ ቤቶች መደበኛ አገልግሎት መስጠት መቀጠላቸው የከፍተኛ ፍርድ ቤቱ የፕሮቶኮል ሹም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጠዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
TIKVAH-ETHIOPIA
#Hawassa በሀዋሳ ከተማ የስፓርት ውርርድ ( #ቤቲንግ ) ቤቶች እየታሸጉ / እየተዘጉ ይገኛሉ። ይህ ተከትሎ የስፖርት ውርርድ ቤት ባለቤቶች " እንዴት የንግድ ፈቃድ እያለን ይዘጋብናል ? " ሲሉ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል። እነዚህ የስፖርት ውርርድ ቤቶች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክኒያቶች ተዘግተው የቆዩ ሲሆን በቅርቡ ተከፍተው ነበር። አሁን ላይ ተመልሰው መዘጋት/መታሸግ መጀመራቸው…
#Update

" የስፖርት ውርርድ ቤቶችን የመዝጋትና የመክፈት አሰራር አድሎአዊነት የተንጸባረቀበት ነው " - ቅሬታ አቅራቢዎች

" የተከፈቱ ቤቶች ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያመጡ ናቸው " - የሀዋሳ ከተማ ፖሊስ

በቅርቡ በሀዋሳ ከተማ ያሉ የስፖርት ውርርድ ቤቶች  " ህጋዊ አይደሉም ፣ በብዛት  የተከፈቱበት አካባቢም የትምህርትና የመኖሪያ ሰፈር ነው " በሚል ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቢዘጉም ከቀናት ቆይታ በኋላ ግን የተወሰኑት ተከፍተዉ ስራ ጀምረዋል።

ይህንን ተከትሎ ፥
- ለምን ሁሉም በህግና ስርአት እየሰራ እና ግብርም እየከፈለ እያለ በከፊል ተከፍቶ በከፊል ይዘጋል ?
- ቤቶቹን የመዝጋትና የመክፈት ስራን የሚሰራዉ የከተማው ፖሊስ አሰራሩ አድሏዊነት የታየበት ነው፤
- ገንዘብ ሰጥተው የሚያስከፍቱ ሰዎችም እንዳሉ እየተሰማን ነው ሲሉ የስፖርት ውርርድ ቤታቸው የተዘጋባቸዉ ግለሰቦች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸዉ የከተማዉ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር መልካሙ አየለ ፥ አሁን ላይ ተከፍተዉ ወደስራ የተመለሱት ከብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ህጋዊ ደብዳቤ ያቀረቡ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

በተጨማሪም " ለሀገር ፈጽሞ ጥቅም የማይሰጠዉ የቨርቹዋል አሰራር አሁንም እንደተከለከለ ነው። ካሁን በፊት እንደህግ ያስቀመጥነዉ የመኖሪያ ቤትና የትምህርት ቤቶች ዙሪያ የተጣለዉ ክልከላ ዛሬም ቀጥሏል " ብለዋል።

ከዚህ ውጭ አከፋፈቱን በተመለከተ የሚነዛዉ ስም ማጥፋት አግባብ አለመሆኑን ገልጸዉ ማንኛዉም አካል ህጋዊ ሆኖ ከመጣ ድርጅቱን ማስከፈት እንደሚችል ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የ2016 ዓ/ም የመውጫ ፈተና እና የሪሚዲያል ማጠቃለያ ፈተና ውጤቶች መቼ ይፋ ይደረጋሉ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች የማጠቃለያ ፈተና እና የዕጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና መቼ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል። የትምህርት ሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራር ፥ የሪሚዲያል ተማሪዎቹ ውጤት ከሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና መጠናቀቅ በኋላ ባሉት ቀናት ይፋ እንደሚደረግ…
#Update

የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ውጤት ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኳል።

የተማሪዎቹ ውጤት ዛሬ ለተቋማቱ መላኩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአንድ የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር አረጋግጧል።

በዚህም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የተማሪዎቻቸውን የመውጫ ፈተና ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የዘንድሮው የመውጫ ፈተና ለ57 የመንግሥት እና ለ124 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በ244 የቅድመ ምረቃ መርሐግብሮች መሰጠቱ ይታወቃል።

Via @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#ቴፒ #አሽከርካሪዎች ° “ ከቴፒ ቡና ጭነን ለመውጣት ተከልክለን ከቆምን ወር ሊሞላን ነው ” - አሽከርካሪዎች ° “ ክልል ኮሚቴ አቋቁቁሞ ነገሩን እያጣራ ነው ”- ቡናና ሻይ ባለስልጣን የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይንቀሳቀሱ በመከልላቸው ያለምንም መፍትሄ ከሦስት ሳምንታት በላይ ለመቆም እንደተገደዱ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አማረዋል። “ ለሥራ የምንወጣው ቤተሰቦቻችንንም ለማስተዳደር…
#Update

“ አሁንም ድረስ ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ ” - አሽከርካሪዎች 

“ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” - ቡናና ሻይ ባለስልጣን

ከቴፒ የጫኑትን ቡና ይዘው እንዳይወጡ ከዚህ ቀደም ተከልክለዋል ከተባሉት 24 ተሽከርካሪዎች መካከል 3ቱ አሁንም እንዳልተለቀቁ አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቲክቫህ የሰጡ አንድ አሽከርካሪ፣ “ አሁንም ቡና ጭነው የቆሙ ተሽከርካሪዎች አሉ። ደቡብ ምዕራብ ቦንጋ ከተማ በቡናና ሻይ ባለስልጣን ግቢ ውስጥ አቁመዋቸዋል ” ብለዋል።

ሌሎችም አሽከርካሪዎች፣ በበኩላቸው ይህንኑ ሀሳብ ተጋርተው፣ ተሽከርካሪዎቹ ቦንጋ የቆሙት ቴፒ ከወጡ በኋላ ቡናው ' Commercial ነው ’ ተብሎ መሆኑን አስረድተዋል።

የተለቀቁት ተሽከርካሪዎችም ቢሆኑ የተለቀቁት ከአንድ ወር መጉላላት በኋላ በመሆኑ በኑሮ ላይ ከባድ ጉዳት እንደገጠማቸው አስረድተው፣ “መጨረሻ ላይ ቡናው Local ነው ተብሎ ተለቀቅን፣ በዚህ ጉዳይ ሲጀመር መጠየቅ ያለበት ሹፌር አልነበረም” ብለዋል።

ከአሽከርካሪዎቹ በኩል ለተነሳው ለዚህ ቅሬታ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ጥያቄ ያቀረበላቸው የቡናና ሻይ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተርና የግብይት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሻፊ ዑመር፣ “ ስንመረምር 3ቱ መኪና Local ብለው የጫኑት የExport ቡና ሆነ ” ብለዋል።

“ ስለዚህ የExport ቡና መሸጥ ህገ ወጥ ነው። አገርን ዶላር ማሳጣት ነው። 3ቱ መኪና እዛው ቆመው ነው ያሉት በፓሊስ እጅ ነው ” ሲሉ ተናግተዋል።

አቶ ሻፊ “ አሁን ላይ የቆሙት ተሽከርካሪዎች በወንጀል ተጠርጣሪዎች ናቸው ” ብለው “ እንደዚህ ያደረጉ አካላትም ለህግ እንዲቀርቡ ለደቡብ ምዕራብ ደብዳቤ ፅፈናል ” ሲሉ አክለዋል። 

ትክክለኛ የችግሩ ምንጭ ማነው ? በማለት ላቀረብነው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ አቶ ሻፊ፣ “በሁሉም Side አለ” ብለዋል።

“ ላኪዎቹ የ Local አስመስለው Exportable ቡና ሲገዙ በጥሩ ዋጋ ስለሚሸጡ። ለአገር አያስቡም። አቅራቢው ደግሞ ቡናን በአፈርና ውሃ እያሸ ወደ Local እንዲገባ ስለሚያደርግ ችግር አለበት” ሲሉ ተናግረዋል።

አክለው፣ “አሽከርካሪዎቹም ቢሆኑ እያወቁ ነው የተሻለ ዋጋ ስለሚከፈላቸው ቴፒ ሂደው የሚጭኑት። ሲጀመር የExports ቡና ማከማቻ፣ Localን ወደ Export የሚለየው አዲስ አበባ ነው። ቴፒ የሚያስሄዳቸው ነገር የለም” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል። ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው…
#Update

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ ከትላንትና ጀምሮ በጦርነት ምክንያት ከቤትን ንብረታቸው ተፈናቅለው እስካሁን በመጠለያ የነበሩ የሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማፀብሪ ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ መጀመሩን አሳውቋል።

ከማይ ዓይኒ፣ ከማይ አንበሳ፣ ከመድኃኔዓለም እና ውሕደት ከተባሉ ቀበሌዎች የተፈናቀሉ ከአንድ ሺሕ አምስት መቶ በላይ ተፈናቃዮች ትላንት ተመልሰዋል።

ዛሬም ማይ ፀብሪን ጨምሮ የፀለምቲ ወረዳ ስድስት ቀበሌዎች ተፈናቃዮች ተመልሰዋል።

አንዳንድ ቃላቸውን ለቪኦኤ የሰጡ ተመላሾች ህዝቡ " እንኳን ደህንና መጣችሁ ! " ብሎ በመልካም ሁኔታ እንደተቀበላቸው ፤ ታጣቂዎች ግን እስካሁን እንዳልወጡ፣ ትጥቅም እንዳላወረዱ ይህ ስጋት እንዳሳደረባቸው ገልጸዋል።

ይህ አካባቢ ጦርነቱን ተከትሎ በአማራ ክልላዊ መንግሥት ስር የጠለምት ወረዳ አስተዳደር ተብሎ ነበር።

የጠለምት አማራ ወሰንና ማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ አለቃ አለነ አሰጋ ፤ " የጠለምት ወረዳ አስተዳደር የጸጥታ መዋቅር፣ ከዛሬ 3 ቀናት በፊት በግዳጅ ሥራ እንዲያቆም ተደርጓል " ብለዋል።

አለቃ አለነ ፥ በሥራ ላይ የቆየው ፖሊስ እና የጸጥታ መዋቅሩ ወደ ዓዲኣርቃይ አካባቢ መንቀሳቀሳቸውን ገልጸዋል።

እርሳቸው ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ግን ከአካባቢው አለመልቀቃቸውን ጠቁመዋል።

በአካባቢው የጸጥታ ስጋት መኖሩን ጠቁመው፣ መንግሥትም ይህንኑ ተገንዝቦ፣ ነዋሪው ኅብረተሰብ የራሱን የጸጥታ መዋቅር እንዲዘረጋ ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል፡፡

አለቃ አለነ የጠለምት የወሰንና የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ ሰብሳቢ እንደመሆናቸው በአካባቢው ላይ ያላቸውን የወሰን እና የማንነት ጥያቄውን በቦታው ላይ እያሉ ማቅረባቸውን እንደሚቀጠሉ ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ፌደራል መንግሥት የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው የትግራይ እና አማራ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ተፈናቃዮች ወደቦታቸው ከተመለሱ በኃላ ከነዋሪው ህብረተሰብ ጋራ በመሆን የጋራ አስተዳደር ከአቋቋሙ በኋላ የሚነሳው ጥያቄ በሕዝበ ውሳኔ / ሪፈረንደም ምላሽ ቢያገኝ የተሻለ እንደሆነ መግለጹ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍርዱ ለሚዲያ 16 ዓመት ከተባለ በኃላ ወደ 10 ዓመት ዝቅ እንዳለ ሰምቻለሁ " - ጸጋ በላቸው " ጉዳዩ ለቢሮዉም ሆነ ለኔ አዲስ ነው " - ወ/ሮ ወይንሸት ብርሀኑ በሀዋሳ ከተማ የዳሽን ባንክ ሰራተኛ ከሆነችዉ ጸጋ በላቸዉ ጋር በተያያዘ በጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል ተከሶ  የነበረው ኮንስታብል የኃላመብራት ወ/ማርያም " ለብዙዎች አስተማሪ ይሆናል " በተባለ መልኩ የ16 አመት ጽኑ እስራት…
#Update

" ውሳኔዉ መስተካከሉ አስደስቶኛል ጥንካሬም ሆኖኛል " - ጸጋ በላቸዉ

" የይግባኝ ዉሳኔዉን ተከትሎ ፍርዱ ወደ 10  መቀነሱ ልክ አልነበረም " - የክልሉ ዋና ዐቃቤ ህግ


• ግለሰቡ በ14 ዓመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጣ ተፈርዷል።

በሀዋሳ ፥ የዳሽን ባንክ ሰራተኛዋን ጸጋ በላቸዉ ላይ የጠለፋ ወንጀል የፈጸመዉ የጸጥታ አባሉ ምክትል አስር አለቃ የኋላመብራቱ  ወልደማርያም የጠየቀው ይግባኝ ተቀባይነት አግኝቶ ፍርዱ ከ16 አመት ወደ 10 መውረዱ ተሰምቶ ነበር።

በወቅቱ በዉሳኔዉ ያዘነችዉ ተበዳይ ጸጋ በላቸዉ ቅሬታ ውስጥ መግባቷን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ ያሳለፈዉ ውሳኔ አግባብ አለመሆኑንና ቅጣቱ በጣም እንዳሳመማት ገልጻ  ቅሬታ ማቅረቧን መዘገባችን ይታወሳል።

ይህን የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሳኔ በመቃወም ይግባኝ የጠየቀዉ የክልሉ ዐቃቤ ህግ ቅጣቱ መውረዱ ከህግ አንጻር አግባብ አይደለም ብሎ በመከራከር የቅጣት ማቅለያውን ውድቅ በማድረግ ቅጣቱ ተስተካክሎ የ14 አመት ከ6 ወር ውሳኔ ተሰጥቷል።

በዚህ የፍርድ ሂደት አስተያየቷን በመልእክት ያጋራችን ወይዘሪት ጸጋ በላቸዉ በፍርዱ መስተካከል  ደስታ እንደተሰማትና ይህም  ጥንካሬ  እንደሚሰጣት ገልጻልናለች።

" እንደኔ አይነት ጉዳት የደረሰባችሁ እህቶች ሁሉ ወደህግ በመሄድ መጠየቅን አትፍሩ " የምትለው ጸጋ ፥ ከመጀመሪያውም በህግ ላይ እምነት እንደነበራት ተናግራለች።

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ኃላፊው አቶ ማቶ ማሩ ፥ " ምንም እንኳን ሚዲያዎች ለዚህ ኬዝ የሰጡት ትኩረት ጉዳዩን ታዋቂ ቢያደርገውም ክልሉ ለሴት ልጅ ጥቃት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ በመሆኑ በርካታ ጠንካራ ውሳኔዎች ተላልፈዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" ይህ የጸጋ በላቸዉ ኬዝ ማህበረሰቡን ያስተምራል ለተጎጅዋም ፍትህ ይሰጣል ብለን ስንከታተለዉ የነበረ ጉዳይ ከመሆኑ በላይ ድርጊቱን የፈጸመዉ ግለሰብ ማህበረሰብ ይጠብቃል ተብሎ ኃላፊነት የተሰጠዉ በመሆኑ ትኩረት ሰጥተነው ነበር " ሲሉ ገልጸዋል።

አቶ ማቶ ከወራት በፊት የተሰጠውን የይግባኝ ውሳኔ ህጋዊ ድጋፍ የለውም ብሎ በመቃወም የክልሉ ዐቃቤ ህግ ፍርዱ እንዲስተካከል የጣረው ለዚህ ነበር  ብለዋል።

ቅጣቱ ከ10 ወደ 14 አመት መስተካከሉን ገልጸው " እንደክልል በዚህ አመት ብቻ ከ256 በላይ ሴቶችንና ህጻናትን የተመለከተ ኬዝ በትኩረት ይዘን እየሰራንበት ነው በተወሰኑት ላይም አስተማሪና  ጠንካራ ውሳኔዎች እየተሰጡ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaHawassa

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  ሊቀ ማእምራን ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በዛሬው ዕለት ከጠዋቱ 12:00 በፌዴራል ፖሊስ " #ለጥያቄ_ይፈለጋሉ " በሚል ከቤታቸው ተወስደው መታሠራቸውን ቤተሰቦቻቸው መናገራቸውን ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል ዘግቧል። ቀደም ብሎ ፥ የሰንበት ት/ ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ስዩም እና የማኅበረ ቅዱሳን…
#Update

መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር ተፈቱ።

የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ  መሪጌታ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከእስር መለቀቃቸውን የማሕበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ዋና ሥራ አስኪያጁ ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ነበር ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ለእስር የተዳረጉት።

ከሁለት ወራት በኋላ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2016  ዓ.ም  ከእስር  መለቀቃቸውን  ከቤተሰቦቻቸው ማረጋገጥ ተችሏል።

#MahibereKidusanTV

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DireDawa በድሬዳዋ ከተማ " ሰልባጅ ተራ / አሸዋ " ከጥዋት አንስቶ እስካሁን ድረስ ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ያልተቻለ ከባድ የእሳት አደጋ ደርሷል። አደጋው ጥዋት 1:45 የተነሳ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ለመቆጣጠር ማስቸገሩን ድሬ ቲቪ የሶማልኛ ቋንቋ ክፍል ዘግቧል። በቃጠሎ እስካሁን በሰዎች ሕይወት ላይ የደረሰ የሞት አደጋ ባይኖርም ከፍተኛ የንብረት ውድመት መድረሱ ግን ተጠቁሟል። አሁንም እሳቱን…
#Update #DireDawa

በድሬዳዋ ከተማ አሸዋ የገበያ ስፍራ የተከሰተው እሳት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

በተለምዶ ' አሸዋ ' በመባል በሚጠራው የገበያ ስፍራ ዛሬ ጠዋት ተነስቶ የነበረው የእሳት አደጋ፥ በርካታ የመሸጫ ሱቆችና ማሽላ ተራ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በስፍራው ተገኝተው ሁኔታውን ተመልክተዋል።

የአደጋውን መንስኤና የጉዳት መጠን በምርመራ በማጣራት ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

የእሳት አደጋው ተጨማሪ ጉዳት እንዳያደርስ ከፍተኛ ርብርብ ላደረጉ ነዋሪዎች የጸጥታ ኃይል ምስጋና አቅርበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከድሬ ቴሌቪዥን ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፥ " በጦርነቱ ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሽረ እንዳስላሰ ከተማ የነበሩ ተፈናቃዮች ከሰኔ 22/2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ቄያቸው ሰሜን ምዕራብ ዞን ፀለምቲና ማይ ፀብሪ እንዲመለሱ የማድረግ ስራ ተጀምሯል " ሲል አሳውቋል። ከ3 ዓመት በላይ በእንዳስላሰ ሽረ ከተማ ተጠልለው የነበሩ ተፈናቃዮች ወደ ቤታቸው ለመጓዝ ዝግጁ እንዲሆኑ አርብ ማታ ተነግሯቸው…
#Update

የሀገር መከላከያው ስለ ትግራይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው እንዲመለሱ የማድረግ እንቅስቃሴ ምን አለ ?

የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌ/ጄነራል ብርሃኑ በቀለ ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ አድርገው ነበር።

የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነትን መሰረት በማድረግ በጦርነቱ የተፈናቀሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።

ሀገር መከላከያው ተፈናቃዮችን የመመለስ ስራ እንዲያስተባብር አቅጣጫ ተሰጥቶ እየሰራ እንዳለ አመልክተዋል።

የፀለምት እና አካባቢው ተፈናቃዮችን ወደ ቄያቸው የመመለስ ስራ ኃላፊነት የተሰጠው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ መሆኑን ተናግረው " ስራው እጅግ በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ነው " ብለዋል።

ዛሬን ረቡዕ ጨምሮ ባለፉት ቀናት የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቄያቸው እንዲመለሱ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ሌ/ጄነራሉ ፥ ተፈናቃዮች እየተመለሱ ያሉት አስፈላጊና መሟላት አለባቸው የተባሉ ቅድመ ሁኔታዎች ከጎን እየተሰሩ ነው ብለዋል።

ስራው በፍጥነት እየሄደ ያለው አብዛኛዎቹ አርሶ አደር የክረምቱ ወቅት ሳያልፍ እርሻውን እንዲሰራና ህይወቱን እንዲመራ በማሰብ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

በፀለምት ካሉ 25 ቀበሌዎች አብዛኛው ተፈናቃይ ከ22 ቀበሌዎች ነው አሁን ባለው ሁኔታ በአስራዎቹ ቀበሌዎች ተፈናቃይ ተመልሷል ፤ እስከዚህ ሳምንት መጨረሻ ቀሪ 11 ቀበሌዎች  አብዛኛው እንዲገባ ይደረጋል ሲሉ አሳውቀዋል።

የቀረውም ስራ በቀጣይ ይሄዳል ብለዋል።

ስለ ታጣቂዎች መውጣት ምን አሉ ?

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የትግራይ ታጣቂዎች በኃይል ገብተዋል " ስለሚባለው ጉዳይ ሌ/ጄነራሉ ፥" ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኃላ በፀለምትም ይሁን በወልቃይት በኃይል የገባባቸው ቦታዎች የሉም " ሲሉ መልሰዋል።

ፀለምት ካሉት ቀበሌዎች 3 ቀበሌዎች ላይ የትግራይ ታጣቂዎች እንዳሉ እነዚህም ጦርነት ሲቆም ባሉበት የቆሙ ናቸው ሲሉ አስረድተዋል።

ባለው መግባባት ከሁለቱም ክልል ጋር የሁለቱም ክልል ታጣቂ መውጣት ስላለበት ተፈናቃዮችን በመመለስ ታጣቂዎቹን የማስወጣት ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በዚህም ፀለምት ያለው የትግራይ ታጣቂ እንዲወጣ እየተደረገ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከተፈናቃይ ጋር ታጣቂ እንዳይመለስ ስለሚሰራ ስራ ምን አሉ ?

በአማራ በኩል " ከተፈናቃይ ጋር ታጣቂ ይገባል " የሚል ስጋት እንዳለ ያልሸሸጉት አዛዡ ፥ በትግራይ በኩልም " ታጣቂዎች (በአማራ በኩል ያሉ) እንደ አዲስ ተደራጅተዋል ስጋት ናቸው " የሚል ነገር እንዳለ ገልጸዋል።

" የሀገር መከላከያው ከሁለቱም በኩል ከተፈናቃዮች እና እዛው ከነበሩት ነዋሪዎች ( ካልተፈናቀሉት ) ሽማግሌዎች እንዲውጣጡ አድርጎ የተፈናቃዮችን ዝርዝር ለመከላከያ ተሰጥቶ ከዛም መከላከያው ከሽማግሌዎቹ ጋር አብሮ ሰዎቹ የዛ ቦታ ነዋሪ መሆናቸውን እየጠየቀና እያረጋገጠ ተፈናቃዮች ይመለሳሉ " ብለዋል።

' ይሄ ታጣቂ ነው ፣ ይሄ ሚሊሻ ነው ' የሚል ክርክር በሽማግሌ ደረጃ ከተነሳ ወደ ህዝብ ተወስዶ ህዝቡ እራሱ ይፈርዳል ሲሉ ተናግረዋል።

" እንግዳ ሰው ሲገባ ይታወቃል ይህ ጉዳይ አሳሳቢ አይደለም " ያሉት አዛዡ ፥ ገጠር ይሁን ከተማ መሬት ከሌላቸው / ሊገቡበት የሚችሉበት ቤት ከሌላቸው ተለይቶ ይታወቃል ብለዋል።

#Ethiopia
#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጎጆብሪጅ #ጤናባለሙያዎች ➡️ " ውላችን ይቋረጥ ፣ #ገንዘባችንም_ይመለስልን ብለው የፈረሙ 4,000 ቆጣቢዎች አሉ " - የቤት እጣ ቆጣቢዎች ➡️ " ከጤና ሚኒስቴር፣ ከዳሽን ባንክ ጋር የመግባቢያ ሰነድ ስላለን ተመካክረን መልስ እንሰጣለን " - ጎጆ ብሪጂ ከ7 ሺህ 500 በላይ ለሚሆኑ #የጤና_ባለሙያዎች ቤት ገንብቶ ለማስረከብ ከጤና ሚኒስቴር እንዲሁም ከዳሽን ባንክ የሦስትዮሽ ውል የፈረመው ጎጆ…
#Update

“ ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት እንገደዳለን ” - የጎጆ ብሪጂ ቆጣቢዎች

“ ሶስቱም ተቋማት ቃለ ጉባኤውን አጽድቀውታል ፤ መፈራረም ነው የቀረው እንደደረሰ ይጀመራል ” - ጎጆ ብሪጂ 

የጎጆ ብሪጂ ሃውሲንግ የቤት እጣ ቆጣቢ ከ7,500 በላይ የጤና ባለሙያዎች “ ድርጅቱ ውሉ መሠረት እየሰራ ባለመሆኑ ” 4,000 የሚሆኑት ጤና ባለሙያዎች ገንዘብ እንዲመልስላቸው መጠየቃቸው ይታወሳል።

በወቅቱም ምላሽ የጠየቅነው ጎጆ ብሪጂ የሦስትዮሽ ውሉን ከተዋዋሉት ተቋማት ጋር ተነጋግሮ በሳምንት እንደሚመልስ ገልጾ ነበር።

አሁንስ የጤና ባለሙያዎቹ ምን አሉ?

- የመውጫ ፎርሙን ሞልተን ካስገባን በኋላ ገንዘብ መመለሱን በ1 ሳምንት ውስጥ እንደሚጨርሱልን ተነጋግረን ነበር። ነገር ግን 2 ሳምንታት አለፋቸው።

- ሂደን ' ለምንድነው የዘገየው  ? ' ብለን ስንጠይቅ የተለዬ የማይረባ አጀንዳ ዘርግተው ‘ የሦስትዮሽ ውሉን ጤና ሚኒስቴር ስላልፈረመልኝ አናስገባም ’ አሉ ዋና ስራ አስኪያጁ አቶ አልማው።

- ጤና ሚኒስቴር ያልፈረመው ገና ከጅምሩ ስንዋዋል ለጎጆ ብሪጅ የምዝገባና የሥራ ማስኬጃ በሚል ቅድሚያ 4,000 ብር ተከፍሏቸው ስለነበር ምንም ስራ ስላልሰራ፣ ውሉንም ስላፈረሰ ከ4,000 ብሩ ላይ ተቀናንሶ ተመላሽ እንዲሆን እና ፎርሙን ጎጆ ባዘጋጀው ብቻ ላለመፈረም ስለፈለገ ነው።

የቆጠቡት ገንዘብ እንዲመለስላቸው የሚፈልጉት አባላት ብዛት ከዚህ ቀደም ከነበረው ከ4,000 ወደ 7,000 ከፍ ማለቱን አስረድዋል።

አሁን ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት እንደሚገደዱ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎቹን ቅሬታ ይዞ ጎጆ ብሪጂ ሃውሲንግን አነጋግሯል።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጂ የሆኑት አቶ አልማው ጋሪ ፥ “ በሦስትዮሽ ውል ነው ስራውን የጀመርነው። ‘ ገንዘባችን ይመለስልን ’ ብለው ሲጠይቁ ተነጋግረን በምን አይነት መንገድ ገንዘቡ ይመለሳል የሚለውን ተስማማን። ቃለ ጉባኤ ተዘጋጀ፣ ፈርመን ላክን ፈርመው እንዲመልሱልን ” ብለዋል።

“ በመካከል እንዳይቆም ተብሎ እንዲመለስላቸው የጠየቁትን ዝርዝር ላኩልን ከሰነዶቹ ጋር። ጉዳዩን እያጣራን ነው። ፊርማ እንደደረሰልን ግን መመለስ መጀመር እንችላለን ” ሲሉም አክለዋል።

“ ይሄ ደግሞ የሆነበት ምክንያት እጣም የደረሳቸው ሰዎች አሉ። እኛ ከፍተኛ ገንዘብ ቀብድ ብለን ሰጥተን እየተጠባበቅን ነበር። የእነርሱን የያዘ ጉዳይ ስለሆነ በመካከላችን መግባባት መኖር አለበት ” ብለዋል።

“ ጎጆ ብቻውን ምንም ማድረግ አይችልም ” ያሉት አቶ አልማው፣ የሦስትዮሽ ውሉን የተዋዋሉት ተቋማት ቃለ ጉባኤው ላይ እስከሚፈርሙ እየጠበቁ እንደሆነ፣ እንደፈረሙ መመለስ እንደሚጀምሩ ተናግረዋል።

ውሉ በጋራ የገባችሁት እንደመሆኑ መጠን ተቋማቱ እንዲፈርሙ ጠይቃችኋቸው ነበር ? ለሚለው ጥያቄ፣ “ ተነጋግረን፣ ተግባብተን ቃለ ጉባኤ ሰጥተን ነበር እሱ ነው እንዲፈረም እየጠበቅን ያለነው ” ሲሉ መልሰዋል።

ገንዘብ የመመለስ ተግባሩ በመዘግየቱ የተነሳውን ቅሬታ በተመለከተም መዘግየቱን አምነው፣ “ ትንሽ ይታገሱ። የአንድ ግለሰብ ጉዳይ ስለሆነ ተግባብቶ መጨረሱ ጥሩ ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION🚨 “ የ2 አውቶብስ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታግተዋል ” - ከእገታ ያመለጠ ተማሪ “ ‘ ከአሁን ወዲህ ስልኬ አይሰራም ፤ ታግተናል ’ አለችኝና ከዛ ስልኳ አይሰራም ” - የአንዷ ታጋች ተማሪ እህት “ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እየጠየቁ ነው ” - የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ሰኞ እለት ተሳፍረው ወደ ቤተሰብ እየተጓዙ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ከ2ኛ እስከ…
#Update

“ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” - ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ ገብረ ጉራቻ ላይ በታጣቂዎች የታጋቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው ፤ ምን እየተሰራ ነው ? ሲል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል።

የዩቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስማማው ዘገዬ፣ “ ጉዳዩን ሰምተናል። ከዚህ ድርጊት ያመለጡ ተማሪዎች ነግረውናኛል ” ብለዋል።

“ እንደነገሩኝ እኔ ማድረግ ያለብኝን ለሚመለከተው የፌደራል መስራያ ቤት፣ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” ነው ያሉት።

“ እነርሱም ‘ ለሚመለከተው የጸጥታ አካል ሪፓርት እናደርጋለን ’ ብለውኛል ” ያሉት ዶክተር አስማማው፣ “ እኔ ከእገታ ያመለጡትን ልጆች Informally communicate አድርጌአቸው ነበር ” ብለዋል።

አክለው፣ “ መከላከያ አብዛኛዎቹን ልጆች አስመልሶ መከላከያ ካምፕ ውስጥ ያደሩ ልጆች እንዳሉ ሰምቻለሁ። የተወሰኑ ደግሞ በሌላ መኪና ተሳፍረው አዲስ አበባ የገቡ እንዳሉ ሰምቻለሁ ” ነው ያሉት።

“ ግን ቀሪ ልጆች በጣም ዝናባማ ስለነበር መከላከያና ፓሊስ ሳይደርስባቸው አጋቾቹ ይዘዋቸው የሄዱ የተወሰኑ ልጆች እንዳሉ ሰምቻለሁ ” ሲሉ ተናግረዋል።

ከዩኒቨርሲቲው የወጡት ተማሪዎች ቁጥራቸው ስንት ነው ? ለሚለው ጥያቄ በምላሻቸው፣ “ ቁጥራቸውን አናውቀውም የኛ ሲነር ተማሪዎች የመጨረሻ ግቢ የቆዬ 2ኛ፣ 3ኛና 4ኛ ዓመት ተማሪዎች ከደባርቅ ጎንደር ነው የተሳፈሩት በአውቶብስ ” ብለዋል።

“ ቁጥራቸውን በእርግጠኝነት አላውቀውም ” ያሉት ዶክተር አስማማው ፥ “ ግን በሶስት አውቶብስ የኛ ተማሪዎች እንደተሳፈሩ መረጃው አለኝ። ከ3ቱ ሁለቱ አውቶብሶችን ነው ያስቆሟቸው ” ነው ያሉት።

የታጋች ተማሪዎች ሁኔታ የሚመለከታቸው አካላትን በመጠየቅ መረጃ የምናደርሳችሁ ይሆናል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EHRC የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ዓመታዊ የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ሁኔታ ሪፖርት ይፋ ያደርጋል። የዛሬው ሪፖርት ለሦስተኛ ተከታታይ ዓመት የሚቀርብ ነው። ሪፖርቱ ከሰኔ ወር 2015 ዓ.ም. እስከ ሰኔ ወር 2016 ዓ.ም. ያለውን ጊዜ የሚሸፍን ነው፡፡ ይኸው ሪፖርት በሚሸፍነው ጊዜ የነበረውን የሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ጠቅለል ባለ መልኩ ይቃኛል። በትኩረት ዘርፎች…
#Update

ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የኃላፊነት ቦታውን ይረከባሉ።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን መግለጫ ሰጥቷል።

ላለፉት 5 አመታት ያገለገሉት ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የአገልግሎት ጊዜያቸው ማብቃቱን አሳውቀዋል።

በሕ/ተ/ም/ ቤት ዋና ኮሚሽነር እስኪሰይም ድረስ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ የኃላፊነቱን ቦታ እንደሚረከቡ ተገልጿል።

ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፤ " ከዛሬ ጀምሮ ፓርላማው ስለተዘጋ በሚቀጥለው ሲከፍቱ ነው የዕጩዎች ሂደቱ የሚጀምረው እስከዛው ድረስ በአዋጁ መሰረት ምክትል ዋና ኮሚሽነር ተረክቦ ይሰራል ስለሚል እኔ ነው የምሰራው " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update “ ለትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ሪፓርት አድርጌአለሁ ” - ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፣ ገብረ ጉራቻ ላይ በታጣቂዎች የታጋቱ ተማሪዎች ቤተሰቦች በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው ፤ ምን እየተሰራ ነው ? ሲል ደባርቅ ዩኒቨርሲቲን ጠይቋል። የዩቨርሲቲ ተወካይ ፕሬዚዳንት ዶክተር አስማማው ዘገዬ፣ “ ጉዳዩን ሰምተናል። ከዚህ ድርጊት ያመለጡ ተማሪዎች ነግረውናኛል ” ብለዋል።…
#Update

በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ?

ትምህርት ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ መታገታቸውን  አይዘነጋም።

ታጋቾቹን ከእገታ ለመልቀቅ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እንደጠየቁ ፤ ዩኒቨርሲቲውም ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፓርት እንዳደረገ መረጃ ተለዋውጠን ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ አለ ?

የተወሰኑ ታጋቾች ከእገታ ቢለቀቁም የተወሰኑት ግን አሁንም እንዳልተለቀቁ፣ ቤተሰቦቻቸው እና በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ የወንጌላዊያን የክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የታጋች ቤተሰቦች በገለጹት መሠረት፣ 150 የሚሆኑ ተማሪዎች ዛሬ ወደ አዲስ አበባ እየተመለሱ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ግን እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር ካልከፈሉ እንደማይለቀቁ ተነግሯቸዋል።

በዛሬው ዕለት ወደ አዲስ አበባ ከተማ እየተመለሱ ነው የተባሉት ተማሪዎች በአጋቾች ስር ከነበሩት መካከል እና በተለያዩ ቦታዎች ተደብቀው ከእገታ ማምለጥ የቻሉ መሆናቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቲክቫህ ተናግረዋል።

የወንጌላዊያን ተማሪዎች ህብረት በበኩሉ፣ አሁንም ገና በአጋቾች እጅ ያሉ ፣ ወደ ቤተሰብ መመለስ እየቻሉ ተሽከርካሪ ያላገኙ ፣ የተወሰኑት ታጋቾች ግን እንደተለቀቁ ማረጋገጡን ጠቁሟል።

ተለቀቁ የተባሉትም ከአጋቾቹ ጋር ተግባብተው እንጂ ገንዘብ ከፍለው እንዳልሆነ የተመላከተ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ በችግር ላይ እንደሆኑ መረጃው እንደደረሰው ገልጿል።

ታጋቾቹ በትልቅ ጫካ ታጉረው እንደሚገኙ እና ገንዘብ እየተጠየቁ መሆናቸውን የታጋች ቤተሰቦች ጠቁመዋል።

በዚህ ኑሮ ውድነት ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደማያገኙ ለገልጸው መንግስት ለታጋቾች እንዲደርስላቸው በእንባ ታጅበው ተማጽነዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ዙሪያ ምን እየሰራ እንደሆነ ለመጠየቅ የተደረገው ሙከራ ተደጋጋሚ ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለጊዜው ሳይሳካ ቀርቷል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WKU " አሳይመንቱን ቤት ድረስ አምጥተሽ ስጪን " በማለት ተማሪውን ደፍሯል የተባለው የዩኒቨርሲቲ መምህር ጉዳዩ በፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ #ሴት ተማሪዎች መልዕክቶችን ተቀብሏል። ይህም " የሴቶች ጥቃት አሳስቦናል " የሚል ነው። ተማሪዎቹ የመደፈር እና የጥቃት ወንጀል በመምህር ሳይቀር መፈጸሙን በመግለጽ ስጋታቸውን ገልጻዋል። በየጊዜው እንዲህ…
#Update

ተማሪውን በመድፈር የተከሰሰው የዩኒቨርሲቲ መምህር በ9 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል።

ከሳምንታት በፊት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ መምህር ስለተደፈረች ተማሪ እና ሂደቱም በሕግ እንደተያዘ መረጃ ተለዋውጠን ነበር።

ይኸው መምህር በ9 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጥቷል።

ተከሳሽ አየለ ሀይሉ ሞላ  ይባላል።

የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም በግምት ከረፋዱ 9፡00 ሰዓት ላይ የሚያስተምራትን የወልቂጤ ዩንቨርሲቲ ተማሪ " የተበላሸብሽን ዉጤት አስተካክልሻለሁ ፤ አሳይመንት ይዘሽ ኢስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አካባቢ ነይ " ሲል ይቀጥራታል።

የግል ተበዳይ ተማሪ ነይ ወደ ተባለችበት ቦታ ለመሄድ በጉዞ ላይ ሳለች ተከሳሽ በወልቂጤ ከተማ ጉብሬ ክ/ከተማ ከሚገኘዉ  የመምህራን መኖሪያ አፓርታማ ላይ ሆኖ  የግል ተበዳይን ጠርቶ ወደ መኖሪያ ክፍሉ እንድትገባ  ያደርጋታል።

ተከሳሽ የግል ተበዳይን ውጤት ለማስተካከል ሴትነቷን ለመጠቀም ያቀረበላትን ጥያቄ " አልቀበልም " ስትል በእምቢታ ትፀናለች።

ተከሳሽ ካንተ ጋር አልተኛም ስትል አሻፈረኝ ያለችውን የግል ተበዳይ በጥፊ እያላጋ  ከለፈቃዷ በኃይል አስስገድዶ እንደደፈራት  የተከሳሹ የክስ መዝገብ ያስረዳል።

ተከሳሽ የተከሰሰበት ክስ የወልቂጤ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በችሎት ቀርቦ የተነበበለት ክስ የወንጀል ድርጊቱ " አልፈፀምኩም " ሲል ክዶ ተከራክሯል።

ዐቃቤ ህግም የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አስቀርቦ አሰምቷል። በዚህም ግለሰቡ የወንጀል ተግባሩን መፈፀሙ አረጋግጧል።

ተከሳሽ የመከላከያ ምስክር አስቀርቦ ቢያሰማም ክሱን ማስተባበል ባለመቻሉ ፍርድ ቤቱ ተከሳሹን ጥፋተኛ ሲል ብይን ሰጥቷል።

ፍ/ቤቱ መምህሩን በ9 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ፥ " የዚህ መምህር የቅጣት ዉሳኔ በመሰል ችግር ዉስጥ ለተዘፈቁ መምህራን የማስጠንቀቂያ ደወል ይሁን " ሲል አስጠንቅቋል።

https://t.me/tikvahethiopia/88052

#CentralEthiopiaPolice

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በታጣቂዎች የታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከምን ደረሱ ? ትምህርት ጨርሰው ወደ ቤተሰቦቻቸው እየተመለሱ የነበሩ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ረቡዕ ሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ረፋድ 4 ሰዓት ገደማ ገብረ ጉራቻ መታገታቸውን  አይዘነጋም። ታጋቾቹን ከእገታ ለመልቀቅ አጋቾቹ ለአንድ ተማሪ 400 ሺህ ብር እንደጠየቁ ፤ ዩኒቨርሲቲውም ለትምህርት ሚኒስቴር ሪፓርት እንዳደረገ መረጃ ተለዋውጠን…
#Update

(ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም)

ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ?

በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል።

የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት ቦታ በቡድን ከፋፍለው በእግር እያጓጓዟቸው እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህንን ነገር የሰሙት አጋቾቹ ደውለው " ልጆቻችሁ እንዲለቀቁ ገንዘብ አምጡ " ብለው በዛቱበት እና ከልጆቻቸው ጋር በስልክ በተገናኙበት ወቅት ነው።

አጋቾቹ ገንዘብ እንዲላክላቸው ፤ ለዚህም ትንሽ ጊዜ እንዲሰጡ ቢጠየቁም ለመስማት ፈቃደኞች እንዳልሆኑ የታጋች ቤተሰቦች ገልጸዋል።

የልጆቻቸው ደህንነት እጅግ በጣም በከፋ ጭንቀት ላይ እንደጣላቸው ገልጸው ልጆቻቸውን ወደ ሌላ አገር እንዳያስወጧቸው መከላከያ እና ፌደራል ፓሊስ ክትትል አድርገው እንዲታደጉላቸው ተማጽነዋል።

ቲክቫህ ያነጋገረው የወጌላዊያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረትን በበኩሉ፣ ትላንት መኪና እየጠበቁ የነበሩት መኪና አግኝተው ወደ ቤተሰብ ጉዞ ማድረጋቸውን ገልጿል።

ቀሪዎቹ ግን አሁንም ገንዘብ በታጋቾቹ እየተጠየቁ ነው ብሏል።

በታጋች ተማሪዎቹ ጉዳይ አዲስ ነገር አለ ? ሲል ቲክቫህ የጠየቃቸው የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አንድ አካል ፥ ለበላይ ሪፓርት ከማድረግ ውጪ ምንም ማድረግ እንዳልተቻለ ገልጸዋል። 

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጎንደር ° “ ውሃ ካጣን ከወራት በላይ ሆነን፤ እንኳን ለመታጠብ ለመጠጥም አልተገኘም ” - የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ° “ ጉድጓድ ስናስቆፍር በ4 ወራት ይደርሳል ብለን አንድ ዓመት ከ8 ወራት ወስዷል ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ  በአማራ ክልል የጎንደር ከተማ ነዋሪዎችና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች፣ የውሃ ችግር እንደፈተናቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። የከተማው ነዋሪዎች…
#Update

“ ‘ የ24 ሰዓት ሙሉ የውሃ አገልግሎት እንሰጣለን ’ የሚለው ውሸት ነው ” - የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቅሬታ አቅራቢዎች

“ ሆስፒታል ማለት ለተማሪ አይደለም የምንሰጠው። ሆስፓታሉ ማለት ህክምና የሚካሄድበት ነው ” - የከተማው ውሃና ፍሳሽ ቢሮ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ኢንተርን ሀኪሞች እና ተማሪዎች የውሃ አቅርበት ከተቋረጠ ከወር በላይ ሆኖት እያለ የከተማው ውሃና ፍሳሽ ሰሞኑን የሰጠው ማብራሪያ ትክክል አለመሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በአጠቃላይ በጎንደር ከተማ የውሃ አቅርቦት ችግር እንዳለ ነዋሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች፣ ኢንተርን ሀኪሞች ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል።

በወቅቱ ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው የጎንደር ውሃና ፍሳሽ ቢሮ ፥ የከተማው ነዋሪዎች ቅሬታ ትክክል እንደሆነ አምኖ ለመፍትሄው መንግስት ርብርብ እንዲያደርግ አሳስቦ ነበር።

ቢሮው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ላይ የተነሳውን ቅሬታ በተመለከተ በሰጠው ምላሽ ግን፣ “ሆስፒታል ላይ ግን 24 ሰዓት ነው የምንሰጠው። መብራትና አጠቃላይ ምርት ቆሞ ካልሆነ አይቋረጥም” ነበር ያለው።

የዩኒቨርሲቲው የኢንተርን ሀኪሞቹ በሰጡት የአጸፋ ቃል፣ ‘የ24 ሰዓት የውሃ አገልግሎት እንሰጣለን’ የሚለው ውሸት ነው። እውነታው ውሃ የለም” ሲሉ ወቅሰዋል።

ውሃ በግቢ ከጠፋ ከወር በላይ እንደሆነው ገልጸው፣ እንኳን ለመጸዳጃ ለመጠጥ እንደተቸገሩና በቦቴ የሚቀርበውም አነስተኛ እንደሆነ አስረድተዋል።

የተነሳውን ቅሬታ በተመለከተ በድጋሚ የጠየቅናቸው የከተማው ውሃና ፍሳሽ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቅነህ አያል፣ "ሆስፒታል ማለት ለተማሪ አይደለም የምንሰጠው። ህክምና ለሚካሄድበት ነው" ብለዋል።

" በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በስኬጁል ነው የሚሰጣቸው ሌላው ማህበረሰብ በወር እያገኘ ለሀኪም 24 ሰዓት ልሰጠው አልችልም። ሆስፒታል ግን 24 ሰዓት ህክምና የሚካሄድበት ስለሆነ 24 ሰዓት ሙሉ ነው አሁንም የምንሰጠው" ነው ያሉት።

" ለሀኪሞች የራሳቸው ፕሮግራም አላቸው እንደሌላው ማህበረሰብ አይደሉም በእርግጥ በሳምንት፤ በ3፤ በ4 ቀናት ነው። ድሮ 24 ሰዓት ነበር የሚሰጣቸው። አሁን ግን የውሃ እጥረት ስላለ አንችልም " ሲሉ አክለዋል።

#TikvahEthiopiaFamily

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (ቅዳሜ ሰኔ 29/2016 ዓ/ም) ስለ ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲውን ፣ የግቢው የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት እና የታጋች ቤተሰብን ምን አዲስ አለ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬም ጥያቄ አቅርቧል። የታጋች ቤተሰቦች አጋቾቹ ወደ 20 የሚሆኑ ታጋቾችን ከትላንት ጀምሮ ወደ ማያውቁትና ጫካ በበዛበት…
#Update (No. 5)

የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ በነበሩበት በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተደጋጋሚ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር።

ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ?

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለታጋቾቹ ምን አዲስ አለ ? ሲል የተማሪ ወላጆችን የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት፣ ደርባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።

ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት ወቅት ድረስ ከእገታው ያልተለቀቁ ተማሪዎች እንዳሉ ወላጆች ቃላቸውን ሰጥተዋል።

አጋቾቹ አሁንም ለአንድ ተማሪ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደጠየቋቸው፣ ያሰባሰቡትን የተወሰነ ገንዘብ ልከው ታጋቾቹን እንዲለቁላቸው ቢማጸኑም ገንዘቡ ካልተሟላ እንደማይለቋቸው ገልጸዋል።

በርካታ ተማሪዎች አሁንም እንደታገቱ መሆናቸውን እንዳረጋገጡ የገለጹት ሁለት የታጋች ቤተሰቦች፣ ጉዳዩ በሚዲያ እየተንሸራሸረ ስለሆነ መንግስት ሰምቷል ፤ ታዲያ ለምን መፍትሄ አይሰጠንም ? ሲሉ ጠይቀዋል።

የታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ከምን ደረሰ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጠየቃቸው አንድ ስማቸው እንዲነገር ያልፈለጉ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ አካል፣ ትንሽ ታጋቾች ቢለቀቁም አብዛኛዎቹ ገና እንደሆኑ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ከዚህ የተለዬ መረጃ ግን እንዳልተገኘ አስረድተዋል።

ከትምህርት ሚኒስቴር ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረበላቸው ጉዳዩ ይመለከታቸዋል የተባሉ አቶ አብዱ ናሲር፣ ስለጉዳዩ ከፍተኛ አመራሮች እንዲጠየቁ ከመናገር ውጪ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በዩኒቨርሲቲው የወንጌላውያን ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት በሰጠው ቃል፣ ታጋቾቹ ወደ ወለጋ መስመር እንደተወሰዱ መስማቱን ገልጿል።

በሌላ በኩል ፥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 138 ታጋቾች እንደተለቀቁ መግለጹን ሪፓርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ደግሞ በሸኔ ታግተው የነበሩት 167 ተማሪዎች ናቸው ከነዚህ ውስጥ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች ባካሄዱት ኦፕሬሽን 160ዎቹ ከእገታ ተለቀዋል ብሏል።

ይህንን የመረጃና በየሚዲያው " አብዛኛው ተለቀዋል " እየተባለ የሚሰራጨውን መረጃ ተመልክተው ከደቂቃዎች በፊት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መልዕክት የላኩ የተማሪ ወላጆች በጣም እንደተበሳጩ ገልጸው " ውሸት ባይዘገብስ " ሲሉ ገልጸዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update (No. 5) የዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ቤተሰብ እየተመለሱ በነበሩበት በታጣቂዎች ስለታገቱ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በተደጋጋሚ መረጃ አድርሰናችሁ ነበር። ዛሬስ ምን አዲስ ነገር አለ ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ ስለታጋቾቹ ምን አዲስ አለ ? ሲል የተማሪ ወላጆችን የወንጌላውያን ተማሪዎች ህብረት፣ ደርባርቅ ዩኒቨርሲቲ እና ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል። ይህ ዘገባ እስከተዘጋጀበት…
#Update

እህታቸው የታገተችባቸው የአዲስ አበባ ነዋሪ ለዶቼ ቬለ ከሰጡት ቃል ፦

" በጣም ይገርማል በእውነት፤ እኔ እኮ በእራሳቸው ስልክ (በአጋቾቹ ማለታቸው ነው) ትናንት ጠዋትም ከሰአት በኋላም እራሴ አግኝቻታለሁ በድምፅ፣ ሰዎቹንም አግኝቻቸዋለሁ። ልጆቹ አሁንም እዚያው ነው ያሉት፤ ተፈተዋል ምናም የሚባለው ነገር ውሸት ነው። ማታ ዜና ስንሰማ ነበር። እንዴት እንዲዚህ ያለ ነገር ይሰራል እስኪ ? " ብለዋል።

ከቀናት በፊት እጅግ በርካታ የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ጨርሰው ወደ ቤት ሲመለሱ በታጣቂዎች መታገታቸው ይታወቃል።

ትላንትና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡ አንድ የዩኒቨርሲቲው አካል እስከ ትላንት ድረስ አብዛኛዎቹ ታጋቾች እንዳልተለቀቁ ፤ ትንሽ ታጋቾች ግን እንደተለቀቁ አሳውቀዋል።

በተለያዩ ሚዲያዎች " በርካታ ታጋቾች ተለቀዋል " የሚለውን ዜና የሰሙ የታጋች ቤተሰቦች በድርጊቱ ተበሳጭተዋል፤ አዝነዋል። ለምን ውሸት ይዘገባል ? ሲሉም ጠይቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Africa #Kenya " በሙስና የተዘፈቀውን ካቢኔዎትን ይበትኑ ! " - የኬንያ አብያተ ክርስቲያናት ብሔራዊ ምክር ቤት ምንም እንኳን ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ የፋይናንስ ረቂቅ አዋጁን ቢሰርዙም ተቃውሞው ቀጥሏል። የኬንያ አብያተ ክርስትያናት ፕሬዜዳንቱ ካቢያናቸውን እንዲበትኑ ጠይቀዋል። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና በርከታ ኬንያውያን ሩቶ በሀገሪቱ የተንሰራፋውን ሙስና እንዲያጸዱ ጥሪ እያቀረቡ…
#Kenya #Update

ሩቶ ካቢኔያቸውን በተኑ።

ለሳምንታት በህዝብ ተቃውሞ ስትናጥ የከረመችው ኬንያ ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ የካቢኔ ሚኒስትሮቻቸውን በተኑ።

ሩቶ ዛሬ ነው ይህን እርምጃ የወሰዱት።

የፕሬዜዳንቱ እርምጃ በመላው ሀገሪቱ ለተነሳው የፀረ መንግሥት ተቃውሞ እንደምላሽ ነው የተወሰደው።

ፕሬዝደንት ዊሊያም ሩቶ ፥ የካቢኔያቸው ተቀዳሚ ዋና ጸሐፊ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሳሊያ ሙዳቫዲ እንዲሁም ምክትል ፕሬዝደንት ራጋቲ ጋቻጉ ሲቀሩ ሌሎቹን ሚኒስትሮቻቸውን በሙሉ ማሰናበታቸውን ተናግረዋል።

ፕሬዝደንቱ እርምጃውን የወሰዱት የሕዝባቸውን ድምፅ በመስማት መሆኑን ተናግረዋል።

#DW
#CitizenTV

@tikvahethiopia