TIKVAH-ETHIOPIA
1.42M subscribers
55.2K photos
1.38K videos
199 files
3.7K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbeba

በመኖሪያ በቱ ብሬን (የመትረየስ ጠመንጃ) የሆነ የቡድን የጦር መሳሪያ ከመሰል 83 ጥይት እና 30 የሽጉጥ ጥይቶችን ሸሽጎ ለመሸጥ ሲያስማማ የነበረ ግለሰብ ተይዞ ምርመራ እያጠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ግለሰቡ እና የጦር መሳሪያው ሊያዝ የቻለው ከህብረተሰቡ የተገኘን መረጃ መነሻ በማድረግ ነው፡፡

በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ኮተቤ መሳለሚያ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ አንድ ግለሰብ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ አንድ ብሬን (የመትረየስ ጠመንጃ) የቡድን የጦር መሳሪያ ከመሰል 83 ጥይቶች እና ከ30 የሽጉጥ ጥይቶች ጋር ደብቆ ገዥ በማፈላለግ ላይ እንዳለ መረጃ የደረሰው የፌዴራልና የአበባ ፖሊስ ኮሚሽን ከሕብረተሰቡ ያገኘውን መረጃ መሰረት በማድረግ በተደረገው ብርቱ ክትትል ሁኔታውን ለቅርብ ኃላፊዎቻቸው አሳውቀው ለፖሊስ በቂ ማስረጃ በማሰባሰብ ግለሰቡ የጦር መሳሪያውን አሳልፎ ሳይ ሸጠው ከፍ/ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማውጣት በመኖሪያ ቤቱ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ የጦር መሳሪያውንና ጥይቶቹን ማግኘቱን የጉዳዩ መርማሪ ም/ሳጅን ጌታነህ ታረቀኝ ገልፀዋል፡፡

https://telegra.ph/ETH-11-05-6

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

ኢ/ር ታከለ ኡማ በሁለት ክፍለከተሞች ከ15 ዓመት በላይ ምላሽ ሳያገኙ ለቆዩ 874 ነዋሪዎች የቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ሰጥተዋል፡፡ ነዋሪዎቹ በተለያዩ አደጋዎችና በተለያዩ ምክንያቶች ከመኖሪያ አካባቢያቸው ተነስተው የነበሩ ነዋሪዎች ናቸው፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በነገው እለት ሶስት አዳዲስ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ግንባታ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በሚገኙበት በይፋ ያስጀምራል።

ፕሮጀክቶቹ ከቦሌ ሚካኤል ቀለበት መንገድ የላይና የታች መንገድ-ቡልቡላ ካባ መግቢያ የሚደርሰው 5.5 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው፣ ሁለተኛው ደግሞ ከአውቶቡስ ተራ-መሳለሚያ-18 ቁጥር ማዞሪያ አድርጎ ኮልፌ ቀለበት መንገድ ፕሮጀክት 3.4 ኪ.ሜ ርዝመትና 40 ሜትር የጎን ስፋት የሚኖረው ሲሆን ከአውቶቢስ ተራ-18 ቁጥር ማዞሪያ ያለው ነባር መንገድ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ያለበት እንደሆነ ይታወቃል።

በተያያዘም ከለገሀር በጥላሁን ገሰሰ አደባባይ እስከ ጋዜቦ አደባባይ የመንገድ ፕሮጀክት በባለስልጣኑ የራስ ሀይል የሚገነባ ሲሆን 1. 1 ኪሎ ሜትር ርዝመትና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ የ 10 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከለገሀር በፍላሚንጎ ጀርባ አድርጎ ወደ ቦሌ ለመጓዝ አማራጭ መንገድ በመሆን በመስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ ይደረግ የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ ችግር በከፍተኛ ደረጃ ይቀርፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ከአዲስ አበባ ከተማ ፕሬስ ሴክሬታሪያት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው እነዚህን የመንገድ ፕሮጀክቶች በሁለት አመታት ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት ይሰራል ተብሏል።

(EPA)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

"ሰው መሆን ይቀድማል!" ኪነ ኢትዮጵያ- አዲስ መንፈስ የተሰኘ የህዝብ ለህዝብ መድረክ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በትላንትናው ዕለት በኤሊያና ግራንድ ሆቴል ተካሂዷል፡፡ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ሞያተኞች ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ይህ መድረክ በባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶክተር ሂሩት ካሳው ነበር የተከፈተው፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ታዋቂና አንጋፋ አርቲስቶች፣ የክልል ርዕሰ መስትዳድሮችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተው ነበት፡፡ የህዝብ ለህዝብ መድረኩ ዓላማም ሀገራዊ አንድነትን፣ ሰላምን፣ ወንድማማችነትንና አብሮነትን በማጠናከር ኢትዮጵያዊ አንድነትን ማጎልበት መሆኑን ከሚኒስቴሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbeba

ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ "አጠና ተራ አካባቢ" ከባድ የትራፊክ አደጋ መድረሱን የቤተሰባችን አባላት በቪድዮ በታገዘ መረጃ አሳውቀውናል። የደረሰውን ጉዳት በሚመለከት መረጃዎችን ለማግኘት ጥረት እናደርጋለን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

ኢ/ር ታከለ ኡማ ከአፋን ኦሮሞ ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ የሆነውን ቡርቃ ዋዩ እንደኛ ደረጃ ት/ቤትን ተመልክተዋል። ጆሞ አካባቢ የሚገኘው ትምህርት ቤቱ ወደሥራ የገባው በዚህ ዓመት ሲሆን 5342 ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ ይገኛል።

በትምህርት ቤቱ ያለውን የትምህር አሰጣጥ ሂደት የተመለከቱት ኢ/ር ታከለ ኡማ ከመምህራን እና የተማሪ ወላጆች ጋር ቆይታ አድርገዋል። ወላጆችም በዩኒፎርም ስርጭት ወቅት በትምህርት ቤቱ ስላጋጠመው እጥረት እና ሌሎች ችግሮችን በተመለከተ ለኢ/ር ታከለ ጥያቄ አቅርበዋል።

ኢንጂነር ታከለ በበኩላቸው አስተዳደሩ ይህንን ት/ቤት ጨምሮ በሌሎች ትምህርት ቤቶች ያሉ ጥያቄዎች ላይ በአጭር ጊዜ ማስተካከያ እንደሚያደረግ ተናግረዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የአማራና የትግራይ ክልል ምሁራን ለሶስት ቀናት የሚቆይ ውይይት በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄድ ጀምረዋል። የሁለቱን ክልሉች ምሁራን ጉባዔም የሰላም ሚኒስቴር ከሌሎች ተባባሪ አካላት ጋር በመሆን ማዘጋጀቱም ተገልጿል።

(EBC)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማህበር ለኢ/ር ታከለ ኡማ በህጻናትና እናቶች በመደገፍ በኩል ላበረከቱት አስተዋጽኦ ስጦታ አበረከተ፡፡ ማህበሩ 7ኛውን መደበኛ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡ በጉባኤው ላይ ኢ/ር ታከለ ኡማ ተገኝተዋል፡፡

የሴቶች ማህበሩ ኢ/ር ታከለ ኡማና የከተማ አስተዳደሩ በተያዘው አመት በስፋት የተጀመረው የተማሪዎች የምገባ መርሀግብር የመሪነት ሚና በመጫወታቸው ፤እንዲሁም የተማሪዎችን የመማሪያ ቁሳቁስና ዩኒፎርም አቅርቦት ላይ የከተማ አስተዳደሩ ያከናወነው ተግባር በማህበሩ አድናቆት ተችሮታል፡፡

ከዘህ በተጨማሪም በክረምቱ የአረጋውያንን ቤት በማደስ ከተማ አስተዳደሩ ያከናወነው ተግባር የሚመሰገንና መቀጠልም ያለበት ነው ተበሏል፡፡ ለእነዚህና የከተማ አስተዳደሩ ሴቶችና ሀጻናትን በሚመለከት ላከናወናቸው ተግባራት ምስጋና መገለጫ የሚሆን የ"ካባ" ስጦታ ለኢ/ር ታከለ ኡማ ተበርክቶላቸዋል፡፡

ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ -- የከተማ አስተዳደሩ ለሴቶችና ህጻናት የሚሰጠው ትኩረት ቀጣይነት ያለው መሆኑን ጠቅሰው"ለሴቶች ፣ህጻናትና አረጋውያን የማትመች ከተማን መፍጠር አንፈልግም " ብለዋል፡፡

(EPA)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

- በአዲስ አበባ ከተማ "ለአረንጓዴ ቦታነት" ተከልለው የነበሩ ቦታዎች ከግሉ ዘርፍ ጋር በጋራ በመሆን ፓርክ እንዲሰራባቸው ተወሰነ፡፡ በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች ለአረንጓዴ ቦታነት በሚል ለረጅም አመታት ተከልልው የነበሩ ቦታዎች ቢኖሩም ለህብረተሰቡ አገልግሎት እየሰጡ እንዳልነበረ የከንቲባ ፅህፈት ቤት አስታውቋል፡፡

- በተጨማሪም አካባቢዎቹ ለህገወጥ የመሬት ወረራ የተጋለጡ እና ለቆሻሻ ማከማቻነት የዋሉ ሆነዋል፡፡ ይህንን የገመገመው የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔም ቦታዎቹ ከባለሃብቶች ጋር በመሆን የተሟላና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ያማከሉ መዝናኛ ያላቸው ፓርኮች እንዲሰራባቸው ወስኗል፡፡

- ፓርኮቹ ለነዋሪዎች ተጨማሪ የመዝናኛ አማራጭ እንደሚሆኑና የከተማዋ አረንጓዴ ሽፋን ለማሳደግም የካቢኔው ውሳኔ አስተዋጽኦ ይኖረዋል፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በከተማዋ የሚገኙ የህዝብ መዝናኛ ማእከሎችን ማሳደግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም ነው ፅህፈት ቤቱ ያስታወቀው፡፡

(Mayor Office AA)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 7ኛ ዓመት የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ምክር ቤቱ የ2012 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ ያካሂዳል ተብሏል፡፡ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አዳራሽ ከዛሬ ጀምሮ በሚካሄደው መደበኛ ጉባኤ ተደጋጋሚ የህዝብ ጥያቄዎች የሚነሱባቸውን አራት ተቋማት ማለትም ትምህርት ቢሮ፣ የቤቶችና ኮንስራክሽን ቢሮ፤ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ እንዲሁም የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ሪፖርታቸውን ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

(አዲስ ሚድያ ኔትወርክ)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba #Lyon

ኢ/ር ታከለ ኡማ ከፈረንሳይዋ ሊዩን ከተማ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ኬሚልፊልድ ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በአዲስ አበባ እና በሊዬን ከተማ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ሲሆን በተለያዩ መስኮችም በጋራ ለመስራት የሚያስችል ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADDISABEBA

ማስታወሻ!

በነገው ዕለት (ታህሳስ 02/2012) ከለሊቱ 11:00 ሰዓት ለጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ የሚደረገው የአቀባበል ሥነ ሥርዓት እስከሚጠናቀቅ ድረስ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ እስከ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት ባሉት ግራና ቀኝ መንገዶች ላይ ተሸከርካሪን ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓት ማቆም የተከለከለ ነው።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገድ እንድትጠቀሙ፦

• ከኡራኤል ቤ/ክርስቲያን ወደ መስቀል አደባባይ

• ከቦሌ ዓለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ ወደ መስቀል አደባባይ

• ከቦሌ ኤድናሞል ወደ ቦሌ ዓለም አቀፍ አይሮፕላን ማረፊያ

• ከብሔራዊ ቤተ-መንግስት፤ ከፍል ውኃ፤ ከለገሀር፤ ከካሳንችስ፤ ከሳንጆሴፍ ትምህርት ቤት፤ ከስታዲየምንና ከሃራምቤ ሆቴል አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለጊዜው ዝግ ይሆናሉ።

የፖሊስን አገልግሎት ለማግኘት እና መረጃ ለመስጠት የምትፈልጉ በስልክ ቁጥሮች ፡-
011-1-11-01-11
011-5-52-40-77
011-5-52-63-02
011-5-52-63-03 ወይም በነጻ ስልክ መስመር 991 እና 987 መጠቀም ይቻላል፡፡

(የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን)

@tikvahethiopiaBot @tikvagethiopia
#MekelleUniversity #AddisAbeba

የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ምሩቃን የምክክር መድረክ በሀርሞኒ ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል። መድረኩ "የAlmuni ተሳትፎ ለመቐለ ዩኒቨርሲቲ የላቀ ውጤት" በሚል ርእስ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።ከ200 በላይ የቀድሞ ምሩቃን፣ መምህራን እንዲሁም የአሁን ተማሪዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ።

(ኤልያስ መሰረት)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba

በአዲስ አበባ የሚገኙ የቆዩ ላዳ ታክሲዎች በአዳዲስ ታክሲዎች እንዲተኩ እንደሚደረግ ኢ/ር ታከለ ኡማ ተናገሩ። ለዚህም የታክሲ ባለቤቶችን ከባንክ ጋር የማስትሳሰር ስራ እንደሚሰራም ኢ/ር ታከለ ገልጸዋል። የአዲስ አበባ የታክሲና የሀይገር ባስ ማህበራት ለተገልጋዩ ክብርን በመስጠት ለማገልገል የሚያስችል መርሐ ግብር ይፋ ማድረጊያ መድረክ ተከናወናል። በመርሀ ግብሩ ላይ 13 የታክሲ እና ሶስት የሀይገር ባስ ማህበራት ተሳትፈዋል። መርሐ ግብሩ በተለይ ለአረጋውያን፣ ለነፍሰጡሮች እና ለአካል ጉዳተኞች በተሻለ መንገድ ለማገልገል የሚያግዝ ነው። በመርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት ኢ/ር ታከለ ኡማ አነስተኛ ታክሲዎችና ሀይገር ባሶች ለነዋሪው እየሰጡ ላሉት አገልግሎት አመስግነዋል።

(EPA)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የጥምቀት ክብረ በዓል በዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ መድረክ በሚሌኒየም አዳራሽ ተካሂዷል። የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) የጥምቀት በዓል አከባበርን ከመስቀል በዓል፣ የገዳ ስርዓት እና የፍቼ ጨምበላላ ክብረ በዓላትን ተከትሎ አራተኛው የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ መመዝገቡ የሚታወስ ነው፡፡

(Mayor Office of AA)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba

በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የላዳ ታክሲ ባለንብረቶች ጋር በመነጋገር በዝቅተኛ ወለድ የረጅም ጊዜ ብድር አመቻችቶ አዳዲስ ተሽከርካሪዎችን ለማስገባት  እየተሰራ መሆኑን የከተማ መስተዳድሩ የትራንስፖርት ባለስልጣን  አስታውቋል።

የትራንስፖርት ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ኮማንደር አህመድ መሐመድ እንዳሉት፤  አሮጌ ላዳዎችን በአዳዲስ ተሽከርካሪዎች የመቀየር ስራው የከተማዋን ገፅታ ከመቀየር ና የተገልጋዩን ምቾት ከመጠበቅ ባሻገር ለቱሪዝም መስህብነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል።

መቀየር አለባቸው ተብለው ተመዝግበው የሚገኙ ያገለገሉ ላዳ ታክሲዎች ምን ያህል ቁጥር እንዳላቸው የማጣራት ስራ መጠናቀቁን የጠቀሱት ኮማንደር አህመድ፤ ለጊዜው 8 ሺህ 95  ላዳዎች የተመዘገቡ ሲሆን አዳዲሶቹን በአንድ ግዜ ማስገባት ስለማይቻል በተለያየ ግዜ ወደ ሀገር  ውስጥ እንዲገቡ ይደረጋል ነው ያሉት።

አሮጌ ላዳዎቹን የመቀየር ስራ በአጭር ጊዜ እንደሚጀመር ገልጸው፤ ከናፍጣ በሚወጣው ጭስ የሚፈጠረውን የከተማዋን የአየር ብክለት ለመቀነስ አዳዲስ የሚገቡት በኤሌክትሪክ እንዲሰሩ ለማድረግ  እየተሰራ እንደሆነም ገልጸዋል።

(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Hawassa #AddisAbeba #Wolkite

በሞጣ ከተማ የተፈፀመውን የመስጂዶችና የንብረት ቃጠሎ የሚያወግዙ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል። በጅማ ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ህዝብ በጅማ ከተማ ስታዲየም ተገኝቶ ድርጊቱን አውግዟል። በሃዋሳ ከተማ በመስጂደ-ራህማ ፣ በወልቂጤ ፣ በአሰላ ፣ በአዲስ አበባ ኑር መስጂድ፣ በኢሊባቡር እና ሌሎች ከተሞች ህዝበ መስሊሙ "ድምፃችን ይሰማ" በሚል የተቃውሞ ድምፁን አሰምቷል።

በተቃውሞ ሰልፎቹ ላይ ህዝቡ መንግስት አጥፊዎችን በአስቸኳይ ለህግ እንዲያቀርብ፤ የንብረትም ሆነ ሌላ ጉዳት የደረሰባቸው ግለሰቦች እና ድርጅቶች ተገቢው ካሳ እንዲሰጣቸውና በክልሉ መንግሥት ይቅርታ እንዲጠየቁ፣ የተቃጠሉ መስጂዶችን በአፋጣኝ በማስገንባት የዘወተር አገልግሎታቸውን እንዲሰጡ እንዲደረግ ተጠይቋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን...

#AddisAbeba

የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን በበአላት መዳረሻ ወቅት የሚፈፀሙ ወንጀሎችንና ህገ - ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ባከናወነው ኦፕሬሽን ህገ- ወጥ የጦር መሣሪያዎችን እና ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ጨምሮ በርካታ የወንጀል ፍሬዎችን በቁጥጥር ስር አውሏል፦

- 11 ሽጉጦች ከ1600 በላይ መሰል የሽጉጥ ጥይቶች እንዲሁም ሀሰተኛ የብር ኖቶች ከማተሚያ ማሽን ጋር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

- ቅዳሜ ታህሣስ 25/2012 ዓ.ም ከጧቱ 2፡30 አካባቢ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ኒያላ ሞተርስ ጀርባ ወንጀል የፈፀሙ 6 አባላት ያሉት አንድ የዘረፋ ቡድን በህብረተሰቡ ትብብር በሰዓታት ልዩነት ተጠርጣሪዎቹን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

- በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ መርካቶ ሸክላ ተራ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ከበርበሬ ጋር ባዕድ ነገር ቀላቅለው ለመሸጥ ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 6 ተጠርጣሪዎች ከነ-ኤግዚቢቱ ሊያዙ ይችለዋል።

- ከተለያዩ ተሽከርካሪዎች ላይ 8 ተጠርጣሪዎች ከሰረቁት 331 ስፖኪዮ፤ የዝናብ መጥረጊያ እና ሌሎች የተሽከርካሪ አካላት፣ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ፣ላፕቶፕ ኮምፒውተር ፣ ቴሌቪዥን ፣ የቤት እና የግንባታ ዕቃዎች እንዲሁም ግራሙ ያልታወቀ አደዛዠ እፅ በተደረገ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውሏል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba

በንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ ይሰጥ የነበረውን የትራፊክ ክፍያ አገልግሎት ሌሎች አራት ባንኮችን በመጨመር በአምስት ባንኮች የክፍያ አገልግሎት መሠጠት ይጀምራል። ኢንጂነር ታከለ ኡማ የትራፊክ ክፍያን በዘመናዊ መንገድ ለመቀየር በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ ከዘርፉ ባለሞያዎች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

የትራፊክ ክፍያዎች የ"ለሁሉ" አገልግሎት ከተቋረጠ በኃላ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ብቻ አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየ ይታወቃል፡፡ ይህም አሽከርካርዎች እንዲጉላሉ እና ረዥም ወረፋ እንዲጠብቁ ምክንያት ሆኗል፡፡ ይህም ክፍያ ለመክፈል ያለውን መጉላላት ለመቀነስና ጊዜያቸውን ለመቆጠብ አሸከርካሪዎች የትራፊክ ክፍያዎችን በአቅራቢያቸው ባሉ፦

- የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣
- የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ፣
- የአዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ፣
- የአቢሲኒያ ባንክ እና የዳሽን ባንክ ቅርንጫፎች በመሄድ ክፍያ መፀጸም ይችላሉ፡፡

(Mayor Office Of AA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ዻዻስ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዘንድሮውን በዓለ ጥምቀት ጃን ሜዳ ተገኝተው ቡራኬና መልዕክት አስተላልፈዋል፦

- ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጆች መዋደድን አስተምሯል። እንደ ጥምቀት ያሉ በዓላት የአንደነትና ፍቅር አስተምሮት ያዘሉ በመሆናቸው ለአገር አንደነትና ነፃነት ጉልህ ሚና አበርክተዋል ብለዋል፡፡

- በዓለ ጥምቀቱ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንሰና የባህል ድርጅት በማይዳሰስ ቅርስነት በተመዘገበ ማግስት በመከበሩ የዘንድሮውን በዓል ልዩ ያደርገዋልም ሲሉ ገልፀዋል፡፡

- በዓሉ ከኢትዮጵያም አልፎ በዓለም ቅርስነት መመዝገቡ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ትልቅ ኩራት መሆኑን በመግለፅ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

- ቤተክርስቲያን በአገሪቱ እየተከሰቱ ያሉ አፍራሽ ድርጊቶችንም በፅኑ እንደምታወግዝ አስታውቀዋል፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በፍቅር ተሳስቦ፣ እርቅና ሠላም የሰፈነባት አገር እንድትኖር ጥሪ አቅርበዋል፡፡

- የመንግስት አካላትም በመላ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ መቻቻልና አንድነት እንዲጠነክር፣ እኩልትና ፍትህ እውን እንዲሆን በትጋት እንዲሠሩም ጠይቀዋል፡፡

#EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia