TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
etv! በጋሞ ሽማግሌዎች እርጥብ ሳር የከሸፈው የአርባምንጭ አመጽ🕊

በአዲስ አበባ ዙሪያ በሰዉ ህይወትና ንብረት ላይ የደረሰዉን አደጋ ተከትሎ በጋሞ ጎፋ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ የወጡ #ወጣቶች በስሜት ተነሳስተዉ በንብረት ላይ ሊያደርሱ የነበረዉን ጥቃት የአካባቢዉ ሽማግሌዎች እርጥብ ሣር በመያዝ መስቆም መቻላቸዉ ተገለጸ፡፡

በአርባ ምንጭ የተቆጡ ወጣቶች በኦሮሞ ተወላጆች ንብረቶች ጥፋት እንዳያደርሱ የጋሞ ሽማግሌዎች እንደ ባህላቸው ቅጠል ይዘው በመማጸን ሀላፊነታቸውን መወጣታቸውን የጋሞ ጎፋ ዞን ኮሙኒኬሽን ባለሙያ አብዮት አባይነህ ለኢቢሲ ተናግረዋል።

ለሀዘን መግለጫ ተብሎ በተደረገዉ ሰልፍ የድንጋይ መወርወር ቢኖርም በንብረት ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩን የኮሙኒኬሽን ባለሙያው ገልጸዋል፡፡

በትላንትናው ዕለት የዞኑ ህዝብ ሀዘኑን ለመግለጽ በአርባምንጭ ከተማ በወጣበት ወቅት የተደራጁ ሀይሎች ሰልፉን ወደ አመጽ ለመቀየር ሙከራ ማድረጋቸውን የጋሞ ጎፋ ዞን ጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ አቶ ቤታ አንጁሎ ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡

ህግን ለማስከበር በተደረገ ጥረት ከፖሊስ ጋር በተወሰነ መልኩ ግጭት ተፈጥሮ የ2 ሰዎች ህይወት ማለፉን የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊው ገልጸዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ድሬዳዋ ፖሊስ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ሐምሌ 29/2010 ዓም ለ13 ሰዎች ህልፈትና ለንብረት መውደም ምክንያት በሆነው ግጭት ላይ ምርመራውን አጠናቆ ለአቃቤ ህግ ለመላክ መዘጋጀቱን ይፋ አደረገ ኮሚሽኑ ዛሬ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በእለቱ በተፈጠረው ሁከት በሶስት መኖሪያ ቤቶች ውስጥ የነበሩ የ13 ንፁሀን ዜጎች #ህይወት ማለፋንና በ42 ቤቶች ላይ ቃጠሎና ዝርፊያ መካሔዱን ገልጿል።

ኮሚሽኑ ባደረገው ምርመራ 4 ግለሰቦች በቤት ቃጠሎ ፣21 ግለሰቦች ደግሞ በቀጥታ በግድያው መሳተፋቸውን በማስረጃ ማረጋገጡን ገልጾ በ5 #ተጠርጣሪዎች ላይ ማስረጃ እያሰባሰበ መሆኑን በመግለጫው አስረድቷል።

ከ13ቱ ሟቾች 8ቱ የአንድ አመት ህፃንን ጨምሮ ከ15 አመት በታች እድሜ ያላቸው ሲሆኑ በንብረት ረገድም ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

በግጭቱ ወቀት የነፍስ ግድያ ፣ የቤት ቃጠሎና የዝርፊያ ተደራራቢ ወንጀል በመፈፀሙ ምርመራውን ለማጠናቀቅ ጊዜ መውሰዱን በመግለጫው ተመልክቷል።

የተፈጠረውን ግጭት የብሔር ግጭት ለማስመሰል ሙከራ መደረጉን፣ የድሬዳዋ ሕዝብ ያዳበረው የአብሮ መኖር እሴት ለእንዲህ አይነቱ ኋላ ቀር አስተሳሰብ የማይመች በመሆኑና ፖሊስ ሁኔታውን መቆጣጠር በመቻሉ የታሰበው ሊሳካ አለመቻሉን የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግኑኝነት ዲቪዥን ሀላፊ ዋና ሳጅን ባንታለም ግርማ ገልፀዋል።

ከሀምሌ 29 በኋላ ነሀሴ 29/2010 ዓም በድጋሚ ግጭት ለማስነሳት መሞከሩን የገለጹት ዋና ሳጂን ባንታለም ግርማ ፖሊስ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ሁኔታውን በመቆጣጠር 300 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን የያዘ ሲሆን ከተያዙት ውስጥ በ77 ቱ ላይ ምርመራ አጣርቶ
ለአቃቤ ህግ በመላኩ አቃቤ ህግ በፍርድ ቤት #ክስ መመስረቱን ተናግረዋል።

ሰሞኑን በቤቶች ላይ የተደረገውን ምልክት በተመለከተም ፖሊስ ከህብረተሰቡ ጋር እጅና ጓንት ሳይሆን መዳፍና ጣት ሆኖ በመስራቱ ምልክቱ ወደ ተግባር እንዳይለወጥ መደረጉን የህዝብ ግኑኝነት ሀላፊው ገልፀዋል።

ከነገ ጀምሮ በክርስትና እምነት ተከታዮች የሚከበረው የደመራና የመስቀል በአል ሀይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ በሰላም እንዲከበር ፖሊስ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን የገለጹት ዋና ሳጂን ባንታለም ግርማ ሰላም ወዳዱ የድሬዳዋ ሕዝብም ከስሜታዊነት ርቆ እንደ ሁልጊዜው ከፖሊስ ጋር በመተበባር ለሰላሙ ዘብ እንዲቆም ጠይቀዋል።

ኮሚሽኑ ህብረተሰቡ በተለይም #ወጣቶች እንዲሁም የአስተዳደሩ አመራሮች ሁከትን ለማክሸፍና ሠላምን ለማረጋገጥ ላሳዩት ቁርጠኝነት #ምስጋናውን አቅርቧል ።

ምንጭ፦ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቢሾፍቱ⬆️

ከአዲስ አበባ የተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ #ወጣቶች #የኢሬቻ በዓልን ምክንያት በማድረግ በቢሾፍቱ በዓሉ የሚከበርበትን አከባቢ #አፀዱ። ወጣቶቹ በመጪው እሁድ የኢሬቻ በዓል በድምቀት የሚከበርበትን ስፍራ ከቢሾፍቱ ከተማ ወጣቶች ጋር በመሆኑን ማፅዳታቸው ተነግሯል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢታብ ሣሙና ፋብሪካ ባለቤት አቶ #እስክንድር_ተስፋዬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። አቶ እስክንድር በ2006 ዓ.ም 14.6 ሚሊየን ብር ግብር በመክፈላቸው ከደቡብ ክልል ግብር ከፋዮች #አንደኛ ወጥተው የዋንጫና ሜዳልያ ሽልማት ከቀድሞ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ክቡር አቶ #ደሴ_ዳልኬ እጅ ተበርክቶላቸዋል። እንዲሁም በ2010 ዓ.ም. ጥቅምት ወር ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የ1 ሚሊዮን ብር ቦንድ በመግዛት ለሀገራቸው ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል። ከምንም በላይ ደግሞ አቶ እስክንድር ለበርካታ #ወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የቻሉ ባለሀብት ናቸው።

ኢትዮጵያ ታታሪ ልጇን አጥታለች!
ነብስ ይማር!
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዚህ ሳምንት ይለቀቃሉ‼️የአዲስ አበባ #ወጣቶች በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚለቀቁ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአራዳ ~ ወረዳ 5 ወጣቶች🔝

አራዳ ወረዳ 5 የሚገኙ #ወጣቶች "በቂ ማስረጃ እጃችን ላይ እያለ፤ ሁሉን ነገር ጨርሰን የድጋፍ ደብዳቤ ተፅፎልን (ኮንቴነር ይሰራ የሚል)፣ ውል ተዋውለን፤ የቲን ቁጥር አውጥተን #ስራ_ከጀመርን በኃላ #አፍርሱ ብለውናል።" ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል። የሚመለከተው አካል ጉዳዩን በትኩረት ተመልክቶ መፍትሄ ይስጠን ሲሉም ጠይቀዋል።

•ጉዳዩ የሚመለለተው አካል ምልሻ መስጠት ከፈለገ +251919743630 ወይም @tsegabwolde መጠቀም ይችላል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በድጋሚ ሀዘናችን ጥልቅ መሆኑን እንገልፃለን!

በሀገራችን #ወጣቶች ህልፈት የተሰማን #ሀዘን ጥልቅ ነው። ልባችን ደምቷል!! ለቤተሰቦቻቸው፤ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ለመላው የሀገራችን ህዝብ መፅናናትን እንመኛል።

ነብስ ይማር!!
#ቀይ_ባህር ወንድም እህቶቻችንን በላብን!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሰላም ተምሳሌት-ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ!!

በነገው ዕለት ከ3 ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ #የTIKVAH_ETHIOPIA ቤተሰብ አባላት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ይገባሉ። ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል #የተሰባሰቡት እኚህ #ወጣቶች ሀገራችን ኢትዮጵያ ላይ #ፍቅር እንዲነግስ ጥላቻ እንዲወገድ፤ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማችን እንዲታረም መልዕክት ያስተላልፋሉ።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አካላት፤ ተማሪዎች ህብረት የተለያዩ ማህበራት እና ክበባት እኚህን የሰላም እና የፍቅር መልዕክተኞች፤ የንፁህ ልብ ባለቤት #ወጣቶችን ለመቀበል እየተዘጋጁ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ተስፋ እኛ የሀገሪቱ ወጣቶች ነን!!
በፍቅር ተደጋግፈን ሀገራችንን እንገነባለን!!

ቦታ - የአፍሪካ ህብረት አዳራሽ
ሰዓት - ምሽት 12:00

ፍቅር፤ ተስፋ፤ አንድነት!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#በጎ_ኢትዮጵያዊያን!

በአማራ ክልል “በጎ ኢትዮጵያዊያን” በሚል ስያሜ የተደራጁ #ወጣቶች ትላንት #ባሕር_ዳር ላይ ወርኃዊ ስብሰባቸውን ሲያካሂዱ #ይቅር መባባል እስከዛሬ ለተጠራቀሙ ችግሮች መፍትኄ ያስገኛሉ ብለው እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

Via VOA 24
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማሳሰቢያ፦ TIKVAH-ETH ከየትኛውም የመንግስትም ሆነ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ጋር ግንኙነት የለውም። TIKVAH-ETH ትክክለኛ የኢትዮጵያን ቀለም የያያዙ #የጀግና ሀገር ወዳድ ወጣቶች ስብስብ ነው።

በተለይ የStopHateSpeech ጉዞ ከየትኛውም ወገን ድጋፍ የለውም፦ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጡን #መኪና ብቻ ነው። አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎቻቸው ለጉዞ የሚሆን ጥቂት ገንዘብ/ለድንገተኛ ጉዳዮች/ የሚሰጡት ካልሆነ ምንም አይነት አበል የለውም/እስካሁን የተሰጠውንም በቀጣይ ሳምንት ይፋ አደርጋለሁ/። ተማሪዎች የሚመገቡት በዩኒቨርሲቲ ካፌ ነው። "አበላችን እና ክፍያችን #ፍቅር ነው" ይህ ነው ቃላቸው!!

ሌላው፦
√በራሪ ወረቀት፣ ባነር የሚያሳትምልን ድርጅት ባለመኖሩ በራሳችን ወጪ ነው የምንሰራው።
√ተማሪው በጉዞ መሃል ለሚያፈልግው ወጪ ከራሱ ከኪሱ ነው የሚጠቀመው።
√ቢታመም እንኳን ገንዘብ ሳይኖረው ነው ለእናት ሀገር ሰላም የሚጓዘው።

ወጣቶቹ ትምህርታቸውን ጥለው፣ በአካዳሚክ ጉዳዮች ተጎድተው፣ ተንገላተው፣ ተርበው፣ ለፍተው እየዞሩ ያሉት ለፍቅር ነው፤ ለትውልዱ ሰርቶ ለማለፍ ነው፤ ሀገር ሲበጠበጥ ቁጭ ብሎ ላለማውራት ነው፤ ከህሊና እዳ ነፃ ለመሆን ነው፤ ለሀገሬ ምን ልስራላት በማለት ነው፤ ለሀገር ሰላም እና አንድነት መምጣት ከወጣቶች ውጪ አማራጭ ስለሌለ ነው።

መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እነዚህን #ወጣቶች የሚያስታውስበት ቀን እሩቅ አይደለም፤ ለምን እንደሚዞሩም የሚረዳበት ቀን ሩቅ አይሆንም፤ በሀገራችን ለተፈጠሩ እና እየተፈጠሩ ላሉ ግጭቶች ዋነኛው መንስኤ የጥላቻ ንግግር እና ጥላቻ ነው።

•ኦሮሚያ
•ትግራይ
•አማራ
•ደቡብ በፍቅር አቅፍችሁ #ስለተቀበላችሁን እናመሰግናለን!!

ኑ ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde
#attention

ጥቁር አንበጣ ወደ መርሳ እየገባ ነው!

አሁንም የአንበጣ መንጋ ወደ መርሳ እየገባ በመሆኑ የመርሳ ከተማ #ወጣቶች የተለመደ ትብብራችሁን በማድረግ አርሶ አደሩን ከጥፋት ታደጉት።

(መርሳ ከተማ)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

ኮሮና ቫይረስ ሁሉንም የእድሜ ክልል ነው የሚያጠቃው!

(በዶክተር ሊያ ታደሰ - የጤና ሚኒስትር)

በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎችን የእድሜ ስብጥር ብንመለከት እስካሁን በቫይረሱ ከተያዙት 272 ሰዎች ከህፃናት እስከ አረጋዊያን ድረስ በሁሉም የእድሜ ክልል ያሉ ተይዘዋል።

ትልቁ ቁጥር 99 ሰዎች ከ15-24 የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ናቸው ፤ ከዛ የሚቀጥለው ከ25-34 የእድሜ ክልል ውስጥ (75 ሰዎች) የሚገኙ ሲሆን ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ ሰዎች ቁጥርም 19 ነው። በህፃናት ላይ አነስተኛ ቁጥር ቢታይም ህፃናትም በሽታው እንደሚይዛቸው ያሳያል።

ይህ በሽታ የማያጠቃው የእድሜ ክልል የለም። በዓለም አቀፍ ደረጃ #ወጣቶች አይጠቁም የሚል #የተሳሳተ ግንዛቤ አለ ፤ በተለይ በእኛ ሀገር ያለው ስርጭት ትልቁ ቁጥር በወጣቶች ላይ የታየ ነው። ስለዚህ እያንዳንዳችን የምንወስደው ጥንቃቄ እጅግ አስፈላጊ ነው።

የዚህ በሽታ ስርጭት #እየጨመረ የሚሄድ ሊሆን ቢችልም ምን ያህል ይጨምራል የሚለውን የምንወስነው በየዕለቱ በምንወስናቸው ውሳኔዎች ፣ በየዕለቱ በምንመርጣቸው ምርጫዎች እንዲሁም በምንወስዳቸው እርምጃዎች ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ATTENTION

ባለፉት 5 ወራት በኮሮና ቫይረስ የተያዙ #ወጣቶች ቁጥር በሶስት እጥፍ መጨመሩን የዓለም ጤና ድርጅት አሳውቋል። የዚህ ምክንያት አካላዊ ርቀትን መጠበቁ ላይ ችላ መባሉ እንደሆነ አስረድቷል።

ካለፈው የካቲት ወር መጨረሻ እስከ ሃምሌ ወር አጋማሽ በነበረው ጊዜ ከተመዘገቡት 6 ሚሊዮን የኮሮና ቫይረስ ተጋላጮች ውስጥ 15 በመቶው ከ15-20 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ ያሉ ወጣቶች ናቸው ተብሏል። ድርጅቱ እንደንፅፅር ከዚያ በፊት የነበረው 4.5 በመቶ ብቻ እንደነበር አንስቷል።

ወጣቶች ከሁሉም ሲነፃፀር አፍና አፍንጫ ማሸፈኛ ማድረግ ፣ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ ችላ የሚሉ መሆኑ የጤና ባለሞያዎች ይናገራሉ።

ስራ መሄድ ያለባቸው እነሱ፣ ወደ ባህር ዳርቻ ለማዝናናት የሚሄዱት እነሱ፣ ወደ መጠጥ ቤትም የሚሄዱት፣ ሱቅ የሚያዘወትሩትም እነሱ ናቸው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አሳስቧል።

ወጣቶች በብዛት በኮሮና ቫይረስ እየተያዙ ካሉባቸው ሀገራት መካከል አሜሪካ ፣ ፈረንሳይ፣ ስፔን፣ ጀርመን እና ጃፓን ይጠቀሳሉ።

የጃፓን ቶኪዮ ባለስልጣናት በከተማዋ የሚገኙ ወጣቶች በሚያዘወትሯቸው የመዝናኝ መንደሮች ውስጥ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ለማካሄድ እቅድ ማውጣታቸውን ከቪኦኤ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አባታዊ የደስታ መልዕክት !

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በወቅታዊ ጉዳይ አባታዊ የደስታ መልእክት አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ውድ ወገኖቻችን ጦርነትን የሰሙ ጆሮዎቻችን ዛሬ #ሰላምን እና #እርቅን በመስማታቸው ደስታችን ወደር የሌለው መሆኑን ለኢትዮጵያውያንና ለኢትዮጵያውያት ልጆቻችን ለመግለጽ እንወዳለን።

አገራችን ኢትዮጵያን ከአስከፊ የጦርነት ታሪክ ለማውጣት፣ እግዚአብሔር በሰጣት መልካም ዕድል፣ የተፈጥሮና የሃይማኖት ሀብት እንድታድግ ሰላምን መናፈቅና የሰላም መልእክተኛ መሆን ያስፈልጋል።

ሀሳብ የበላይ ሲሆን የጦር መሣሪያ የእርሻ መሣሪያ ወደ መሆን ይለወጣል። እኛም በተደጋጋሚ የሰላም ጥሪያችንን እያስተላለፍን የቆየን እንደመሆኑ መጠን በዚህ መልካም የምሥራች ደስ ብሎናል።

አሁንም ኢትዮጵያውያን በሙሉ አገሩ የሁላችን ነውና ልንጠብቀው፤ አለመግባባታችንን በውይይት ልንፈታው ፤ ቃላችንን ከመሬት ላይ አሳርፈን እርቁን እውነተኛ ልናደርገው ይገባናል።

#ወጣቶች ሲሞቱ ሳይሆን ተምረው ሲመረቁ ፤ ተዋደው ጋብቻ ሲመሠርቱ ለማየት እንናፍቃለን።

የተዘጉ ደጆች ሁሉ በምሕረት እንዲከፈቱ ፤ የተጨነቁ ሁሉ ፀሐይ እንዲወጣላቸው በብርቱ እንሻለን።

ለዚህ እርቀ ሰላም መምጣት በብርቱ የደከሙትን የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ አባላትንና የሰላም ጥሪ የተቀበሉት ልጆቻችንን እግዚአብሔር አምላካችን ዐስበ ሐዋርያትን እንዲከፍልልን እንመኛለን። ለሞቱት ዕረፍተ ነፍስን ለታመሙት ፍጹም ጤንነት እንዲሰጥልን እንለምናለን። "

(የቅዱስነታቸው መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#መቐለ

" የተለያዩ በደሎች እየደረሱብን ነው " ያሉ በትግራይ የሚገኙ የጦር ጉዳተኞች ዛሬ በመቐለ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄዳቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ከመቐለ ዘግቧል።

ፖሊስ ሰልፉ ለመበተን አስለቃሽ ጭስ ተኩሷል ተብሏል።

የጦር ጉዳተኛ ሰልፈኞቹ ከመቐለ ከተማ ወጣ ብሎ ከሚገኘው " መለስ ካምፓስ የጦር ጉዳተኞች ማእከል " በመነሳት እስከ የትግራይ ክልል አስተዳደር መሥርያ ቤት የተለያዩ መፈክሮች እያሰሙ ነበር የተጓዙት።

ሰልፍ የወጡት በአብዛኛው #ወጣቶች የጦር ጉዳተኞች ፦

- «እየደረሰብን ያለውን አስተዳደራዊ በደል ሕዝብ ይስማልን፣ ይወቅልን»

- «በኛ ስም ከሕዝብ የሚሰበሰብ መዋጮ እኛጋ እየደረሰ አይደለም፤ በተደጋጋሚ ጥያቄ ብናቀርብም ምላሽ አጥተናል»

- «በቂ ምግብና ውኃ እንኳን አጥተን የከፋ ሁኔታ ላይ ነን»

- «የታጋዮች ድምፅ ይሰማ»

- «ትኩረት ለጦር ጉዳተኞች»

- «ተክደናል» የሚሉና ሌሎች ብልሹ አሠራሮች የሚያወግዙ መፈክሮችን ያሰሙ እንደነበር ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።

ሰልፈኞቹ " ድምፃችንን ለማሰማት ወደ ከተማ እንዳንገባ መቐለ ዩኒቨርስቲ አሪድ ካምፓስ አካባቢ አስለቃሽ ጭስ በመተኮስ ጭምር እንድንበተን ሙከራ ተደርጓል "  ሲሉም ተናግረዋል።

ዶቼ ቨለ ሬድዮ ፤ የጦር ጉዳተኞቹ ሰልፍ ከፍተኛ የቁጣ ስሜት ይታይበት ነበር ያለ ሲሆን ሁኔታው በሃይማኖት አባቶች ሸምጋይነት እንዲረጋጋ ተደርጓል ብሏል።

ሰልፈኞቹ የክልሉ አስተዳደር መ/ቤት በሆነው ደጀን ቢሮ በር  ቆይታ የነበራቸው ሲሆን የሕወሓት ከፍተኛ አመራር አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ከሌሎች ወታደራዊ መሪዎች ጋር በችግሮቻቸው ዙርያ መወያየታቸውን ሬድዮ ጣቢያው ዘግቧል።

#ዶቼቨለ_ሬድዮ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ዛሬ ከሠዓት ላይ በአዲስ አበባ፣ አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 1 መርካቶ በተለምዶ " ማር ተራ " ተብሎ በሚጠራው ቦታ የእሳት አደጋ ደርሶ ነበር።

የእሳት አደጋው የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

የእሳት አደጋው የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር የተቻለው በእሳት አደጋ ሰራተኞች፣ የፖሊስ አባላት እና በአካባቢው #ወጣቶች ከፍተኛ ርብርብ መሆኑ ተመላክቷል።

የእሳት አደጋው መንስኤ እንዲሁም ያስከተለው የጉዳት መጠን በቀጣይ ተጣርቶ ይገለፃል ተብሏል

መረጃው የክ/ከተማው ኮምንኬሽን ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጋብቻ እየተጠናቀቀ ባለው በ2015 ዓ/ም የጋብቻ ፍቺ የፈፀሙ እና የተመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ባለትዳሮች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር #በእጥፍ እንደበለጠ ታውቋል። የአ/አ ሲቪል ምዝገባ እና ነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የነዋሪዎች አገልግሎት ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በሰጡት ቃል፤ " በ2015 ዓ/ም በጀት አመት 4,696 ሰዎች ፍቺ አስመዝግበዋል ፤ አምና መጥተው ያስመዘገቡት 2…
#ጋብቻ

አሳስቢውን የጋብቻ ፍቺ ለመግታት ወደ ጋብቻ ከማምራት በፊት የጋብቻን መርህ ፣ ዓላማ ምንነት ጠንቅቆ ማወቅ ይገባል ሲሉ የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ ባለሞያው ተናገሩ።

የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪ አቶ ይመስገን ሞላ ትዳራቸውን ለማትረፍ ምክር ፈልገው የሚመጡ ቤተሰቦች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።

የጋብቻ እና ቤተሰብ አማካሪው ምን አሉ ?

" የችግሩ አይነት እየበዛ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ቢሯችን የምናስተናግደው እንኳን አብዛኛው ችግር ሲገጥማቸው ለምክር የሚመጡ ናቸው ለመገንባት ከሚመጡ ይልቅ።

በሀገራችን ምክንያት ተብለው የሚሰጡ አሉ፦
- የመጀመሪያው በወሲብ አለመጣጣም ይባለል ፣
- በገንዘብ እጥረት ይባለል አብዛኛው የሚፋታው ግን ገንዘብ ሲያገኝ ነው፣
- የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት / የጓደኛ ጠልቃ ገብነት ይባለል ይህም ቢሆን የግንኙነቱን ስስ መሆን ያሳያል፣
- የኮሚኒኬሽን ችግር ይባላል ፣
- አሁን እየጨመረ የመጣው የእምነት ጉዳይ ይነሳል በሁለቱ መካከል አለመተማመን አለ ምክንያት የሚባሉት እነዚህ ናቸው።

ለእኔ ግን ከዚህም በላይ ተጨማሪ ምክንያቶች አሉ ፦
- ያለን መንፈሳዊ እሴት መበላሸት አንድ ነገር ነው ፤
- በጾታዊ አክራሪነት የመጣው የወንድ እና የሴት ፆታ መገፋፋት ፣ አለመቀባበል በሁለቱ መካከል ያለው መተባበር ሳይሆን መፎካከር ስላለ፣ እንደ ባል እና ሚስት ሚናቸውን አለማወቃቸው ምክንያት ናቸው።

መጋባት ይፈልጋሉ ተዋደን ይሆናል ብለው መዋደድ ግን የጋብቻ መሰረት አይደለም ወይም ፍቅር ስላለ ጋብቻ መሰረት አያገኝም ውጤታማም አይሆንም። የጋብቻ መርህ አላማ፣ የጋብቻን ምንነት መረዳት ይጠይቃል። የነዚህ ሁሉ ድምር ውጤቶች ጋብቻ እንዳይፀና ቤተሰብ እንዲፈርስ ያደርጋል።

ወደ ጋብቻም ወደ ቤተሰብም የገቡ ሰዎች አስበው አይገቡበትም፤ ገብተው ምን እንደሚያደርጉ፣ ከመግባታቸው በፊት ምን መዘጋጀት እንዳለባቸው ስለማያውቁ ጋብቻው እንዳይዘልቅ ቤተሰብም እንዲፈርስ ዋነኛ ምክንያት ይሆናሉ። "

ባለሞያው ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ ወደ ትዳር የሚገቡ #ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ከጋብቻ በፊት ስልጠና የመውሰድ ልምድም እያደገ ነው ብለዋል። ይህ ፍቺን ለመቀነስ ሚና እንዳለው ጠቁመው ከምንም በላይ ግን ቤተሰብ ልጆችን ሲያሳድግ አርያ መሆን አለበት ብለዋል።

ባለሞያው ፦

" ጋብቻ ብዙ ጊዜ እኛም ሀገር አይተን እንደሆነ ስመረቅ፣ ቤት ስገዛ ፣ስራ ስይዝ ብለው condition ያስቀምጣሉ ጋብቻ ግን Condition ሳይሆን Qualification ነው የሚጠይቀው። የበቃች ሚስት የበቃ ባል ለመሆን እራሱን አስቀድሞ ማዘጋጀት አለበት።

ለምሳሌ ፦ ባልነት ለበሰለ ወንድ ነው ኃላፊነት ለመሸከም ለበቃ ወንድ ነው ሚስትነትም እንደዛው ስለዚህ ከመዋደድ ያለፈ የመጋባት ምክንያትና ኃላፊነት የመወጣት አቅም ይጠይቃል። አንድ ወንድ ባል የሚሆነው ብስለቱና ብቃቱ ነው ወንድነቱ ብቻ ባል አያደርገውም። ስለዚህ ይህን ለማድረግ በግል እራስን መገንባት አለበት።

ወላጆች ልጆቻቸውን ለራሳቸው ጥሩ ልጅ፣ ለዛ ቤት ደግሞ ጥሩ ባልና ሚስት እንዲሆኑ፤ ሲወልዱ ጥሩ አባት እና እናት እንዲሆኑ ሞዴል መሆን አለባቸው።

አሁን የሚታየው የጋብቻ መፍረስ፣ የፍቺው ብዛት፣ የልጆች መጎዳት ትላንት ያልተሰራው ስራ መዘዝ ነው። ነገም እንደዚያ ይቀጥል ከተባለ ዛሬ እያንዳንዳችን የራሳችንን ቤት ጠብቀን ልጆቻችንን ለጋብቻ ማብቃት (የራሳችንን ጋብቻ በመጠበቅ)፣ ልጆቻችን እንዲሰለጥኑ ማድረግ ጋብቻን አውቀው እንዲኖሩ ማድረግ መፍትሄ ነው " ብለዋል።

ፁሁፍ በቲክቫህ ቤተሰብ አባላት።
Credit፦ ቪኦኤ (አስማማው አየነው)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ቅዳሜ የመጨረሻው ገንዘቡን የመመለሻ ቀን ነው " - ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የራሳቸው ያልሆነን ገንዘብ የወሰዱ ወይም ወደተለያየ ሂሳቦች ያስተላለፉ ግለሰቦች እስከ መጪው ቅዳሜ መጋቢት 14 ድረስ በፈቃዳቸው እንዲመልሱ አሳስቧል። ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነውም ብሏል። በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ተጠቅመው አላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ተመላሽ የማያደርጉ ግለሰቦች ላይ…
የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር ምን አለ ?

የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር መጋቢት 6 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ ተፈጥሮ የነበረውን የሲስተም ችግር ተገን በማድረግ #ተመዝብሯል ያለውን " የህዝብ ገንዘብ " አስመልክቶ መግለጫ አወጣ።

ማኅበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቴክኖሎጂ ሥርዓት ላይ ችግር በተፈጠረበት ቅፅበት የነበረውን ክፍተት እንዴት እንዳገኙ ለጊዜው ባልተረጋገጠ ሁኔታ መረጃ የደረሳቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሌሊቱን በሙሉ በመደዋወል ከአውቶማቲክ ገንዘብ መክፈያ ማሽኖች (ATM) ገንዘብ በመውሰድና ልዩ ልዩ ገንዘብ መክፈያና ማስተላለፊያ ማዕቀፎችን በመጠቀም የራሳቸው ያልሆነውንና በሂሳባቸው ውስጥ ያልነበረን ገንዘብ " ዘርፈዋል " ብሏል።

ከዚህ ባለፈ ደግሞ ፤ " የተፈጸመውን #ምዝበራ እንደ በጎ ተግባር ሁሉ በሁሉም የማኅበራዊ መገናኛ አውታሮች በጀብድ መልክ ሲዘዋወር መመልከታችን ከፍተኛ ኃዘን አሳድሮብናል " ሲል ገልጿል።

የባንኮች ማህበሩ ፤ " ከማኅበረሰቡ በተሰበሰበ አንጡራ ገንዘብ በመንግሥት ከፍተኛ ወጪ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ወደ ከፍተኛ ተቋማት /ዩኒቨርስቲ/ የተላኩ አፍላ #ወጣቶች ኢትዮጵያዊ ከሆነው ነባር ዕምነት እና ባህል ባፈነገጠ ሥነምግባር ላይ ወድቀው መገኘታቸው ልብ የሚሰብርና አገራችን ካለባት ጊዜያዊ ችግሮች በላይ የሚያሳስብ አሳዛኝ ድርጊት ሁኖ አግኝተነዋል  " ብሏል።

ድርጊቱንና የድርጊቱን ፈጻሚ እና ተባባሪ የሆኑትን አካላት ሁሉ ማኅበሩ በጽኑ #እንደሚያወግዝው ገልጾ ፤ እነዚህን መሠል ወጣቶች በተመሳሳይ ውድቀት ውስጥ እንዳይገኙ ለመከላከል ሁሉም አካላት የሚጠበቅባቸውን ሁሉ ትኩረት ሰጥተው እንዲፈጽሙ ጥሪ አቅርቧል።

በንግድ ባንክ ላይ የተፈጠረው ችግር እና ችግሩን ተገን አድርገው በባንኩ፣ በባንኩ ደንበኞችና በኅብረተሰቡ ላይ ጉዳት ባደረሱ አካላት ላይ እየተደረገ ባለው ሕጋዊ ማጣራት እና በቀጣይነት ወደ ህግ በማቅረብ በቂ ተመጣጣኝና አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ በማድረግ ረገድ ፤ ሁሉም አባል ባንኮች አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር ጠቁሟል።

ሁሉ አቀፍ ትብብር ለህግና ጉዳዩ ለሚመለከታው ተባባሪ አካላት ለመስጥትም ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቀዋል።

#TikvahFamilyAddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 " አሁን ላይ ያሉ ችግሮች ምፍትሄ እስካላገኙ  ስለ ምርጫ ማሰብ #ቀልድ ነው " - አቶ ግርማ በቀለ የሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሕብር) ሊቀ መንበር አቶ ግርማ በቀለ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ቆይታ አድረገዋል። Q. የዜጎች በሕይወት የመኖር መብት ጥሰትን በተመለከተ ስለሚነሱ ጉዳዮች የፓርቲዎ ግምገማ ምን ይላል ?   አቶ ግርማ…
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል።

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

Q. ከዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት አንፃር የፓርቲዎን ግምገማና መፍትሄውን ቢገልጹ ?

አቶ ጀሚል ሳኒ፦

“ ሰዎች በተደጋጋሚ ሕይወታቸውን እያጡ ነው። በዋና ከተማዋ ሲይቀር ሰዎች እየታሰሩ፣ እየታገቱ ነው።

የትኛውም ዜጋ የደህንነት ስሜት እየተሰማው አይደለም። 

መንግስት #በዋነኛነት የተመሠረተበትና እንዲሰራው ኃላፊነት የተሰጠው ስራ ከየትኛውም ቅድሚያ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ የተዘነጋ የሚመስልበት ዘመን ላይ ነን።

በመወያየትና በመነጋገር ጦርነትን ማስቆም ይገባል።

ሰላምን ከማስፈን ይልቅ #ስልጣንን_የመጠበቅ ፣ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት ነው አብዛኛው አቅም እየባከነ ያለው።

ከዚያ ይልቅ አገሪቱን በሚያሻግሩ ሀሳቦች ላይ አተኩሮ መስራት ያስፈልጋል።

ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦተ እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው። ”

Q. በሙስና ተዘፍቀው ስለሚገኙ ባለስልጣናት እንዲሁም በአጠቃላይ ስለብልሹ አሰራር ፓርቲዎ ምን ይላል ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ አሁን ላይ #ሀዘኔታዎች_የጠፉበት ፣ ሌላው ይቅርና የዜጎች ቤቶች ‘ሕገ ወጥ ናቸው’ ተብለው ቤታቸው የሚፈርስባቸው ሰዎች ላይ ገንዘብ የሚጠየቅበት ሁኔታ ነው ያለው። 

ከኢትዮጵያ Norm ሁላ ያፈነገጠበት ወቅት ላይ ነው ያለነው። በአብዛኛዎቹ መስሪያ ቤቶች የተለመደውን አይነት አሰራር ከመስራት ይልቅ ከእግሮች እጆች እየቀደሙ ነው።

#ሙስና_በግልጽ_እየተጠየቀ ፣ ቢሮ ውስጥ ሥራ አስፈጻሚዎች #በግልጽ_ድርድር እያደረጉበት ያለበት ሂደት ነው አሁን ያለው።

አለ የተባለ የትኛውም ችግርን ለመቅረፍ ላይከብድ ይችላል ፤ ነገር ግን ከተንሰራፋ የትኛውንም ችግር ልቅረፍ ማለት የማይታሰብ ይሆናል። 

ሙስና የሀገር ተቋርቋሪነትን፣ ስሜትን ያጠፋል።

እያየነው ያለውም ይሄው ነውና ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።”

Q. እንደ ፓርቲ የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የምስረታ ጉባዔ ባደረግንበት፣ የጉባዔውን ውጤትና የምርጫ ቦርድ ኮሮጆ ጭምር ይዘን በነበረበት ሰዓት ነው እስር የተጀመረው። ክፍለ አገርም አዲስ አበባም እስሮች አሉ። 

በአባል ደረጃ አንድ የፓርቲው አባል ከ5 ወራት በላይ ያለ ክስና ዋስትና በእስር ላይ ይገኛሉ። ከአባላቶች እስራትና ተንቀሳቅሶ ከመስራት ጋር ዘተያያዘ ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው።

ፓርቲውን የሚደግፉ አባላት #ወጣቶች_እየተላኩ ማስፈራሪያ ያደርሱባቸዋል።

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ሕገ መንግስቱን ያልከተለ በመሆኑ ምስረታው እንዲታገድ፣ ኢ - ሕገ መንግስታዊ ስራዎች በሰሩ ባለስልጣናት ላይ የመሰረትነው ክስ በቀጠሮ እየተጉላላ ነው ያለው። ”

Q. ሕዝቡ በኑሮ ውድነቱ ተማሯል። ለዚህም “ መንግስት ትኩረት አልሰጠም  ” የሚሉ ወቀሳዎች ይቀርባሉ። የፓርቲዎ ግምገማ ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የኑሮ ውድነት በራሱ የሚፈጠር ነገር አይደለም። እስካሁን ከላይ የተነጋገርንባቸው ነገሮች ናቸው እየገፉ የሚያመጡት። 

አንዲት አገር #በጦርነት ላይ ሆና ሚሊዮን ዶላሮችም ለጦርነት እያወጣች ፣ አርሶአደር ማምረትና በሰላም ወጥቶ መግባት ባልቻለበት ፣ የመልካም አስተዳደር ፣ የአቅም ፣ የብቃት ጉዳዮች የመጨረሻ ውጤታቸው የኑሮ ውድነቱ ማምጣት ነው።

እነዚህን ችግሮች ማጥፋት፣ መቀነስ ካልተቻለ የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የተረጋጋ ኢኮኖሚ ማስፈን አይቻልም። ”

Q. ስለምርጫ ያላችሁ አስተያዬት ምንድን ነው ? በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ?


“ ከምርጫ ጋር በተገናኘ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው፣ አጀንዳውም የሚያዘው ከሚደረገው #የፓርላማ እና #የክልል_ምክር_ቤቶች ጋር በተገናኘ ነው። 

ይሄ ስርዓቱን ለመቀየር የሚያስችል ብቸኛው መንገድ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ምርጫ በየአካባቢው ማድረግ ያስፈልጋል። የአካባቢ ምርጫ የተደረገው ከ8 ዓመታት በፊት ነው።

የአካባቢ ምርጫ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።

አሁን ባለንበት ሁኔታ ላይ #ምርጫ ሊደረግ ይችላል ብሎ ማለት ትንሽ አዳጋች ነው። ”

◾️በቀጣዩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፓርቲ የሰጠው ቃል ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
#SouthAfrica

ከሰሞኑን በደቡብ አፍሪቃ " የ2024 ምርጫ " ተደርጎ ነበር።

በምርጫው ማንም አሸናፊ አልሆነም።

የዘንድሮ ምርጫ ገዢው ፓርቲ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት / ANC / 40.18 በመቶ ድምጽ በማግኘት ቀዳሚ ቢሆንም መንግሥት መመስረት የሚያስችለውን ድምጽ ግን አላገኘም።

ፓርቲው በ30 ዓመታት የመሪነት ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አብዛኛውን የምክር ቤት መቀመጫ ተነጥቋል።

በዚህም መንግሥት ለመመስረት ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መጣመር ግድ ይለዋል።

ፓርቲው ምክር ቤቱ ካለው 400 መቀመጫዎች 159 ብቻ ነው ያሸነፈው።

የወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎዛ መንግሥት ለመመስረት #ከተቃዋሚዎች ጋር እንደሚነጋገሩ አመልክተዋል።

በምርጫው 87 መቀመጫዎችን ያሸነፈው የመሃል ቀኝ ዘመሙ ዴሞክራሲያዊ ጥምረት (DA) ነው።

ከገዢው ፓርቲ ጋር ጥምር መንግሥት ለመመስረት የሚያስችል ንግግር ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

ሶስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው የቀድሞ ፕ/ት ጃኮብ  ዙማ ፓርቲ MK ሲሆን ከገዢው ፓርቲ ጋር የመነጋገር ፍላጎት ቢኖረውም " ራማፎዛ ሥልጣን ላይ እያሉ ንግግር አላደርግም " ማለቱን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

በዘንድሮ ሀገር አቀፍ ምርጫ እጅግ በርካታ #ወጣቶች ድምፅ መስጠታቸው የተሰማ ሲሆን ገዢውን ፓርቲ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት /ANC/ በድምጻቸው #ቀጥተውታል

ለዚህ ደግሞ  ፦
- የከፋ ሙስና
- የመልካም አስተዳደር ችግር
- ስራ አጥነት መፋፋት
- የወንጀል መባባስ ... ዋነኞቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia