TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#SouthAfrica

ከሰሞኑን በደቡብ አፍሪቃ " የ2024 ምርጫ " ተደርጎ ነበር።

በምርጫው ማንም አሸናፊ አልሆነም።

የዘንድሮ ምርጫ ገዢው ፓርቲ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት / ANC / 40.18 በመቶ ድምጽ በማግኘት ቀዳሚ ቢሆንም መንግሥት መመስረት የሚያስችለውን ድምጽ ግን አላገኘም።

ፓርቲው በ30 ዓመታት የመሪነት ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ አብዛኛውን የምክር ቤት መቀመጫ ተነጥቋል።

በዚህም መንግሥት ለመመስረት ከተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች መጣመር ግድ ይለዋል።

ፓርቲው ምክር ቤቱ ካለው 400 መቀመጫዎች 159 ብቻ ነው ያሸነፈው።

የወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎዛ መንግሥት ለመመስረት #ከተቃዋሚዎች ጋር እንደሚነጋገሩ አመልክተዋል።

በምርጫው 87 መቀመጫዎችን ያሸነፈው የመሃል ቀኝ ዘመሙ ዴሞክራሲያዊ ጥምረት (DA) ነው።

ከገዢው ፓርቲ ጋር ጥምር መንግሥት ለመመስረት የሚያስችል ንግግር ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።

ሶስተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው የቀድሞ ፕ/ት ጃኮብ  ዙማ ፓርቲ MK ሲሆን ከገዢው ፓርቲ ጋር የመነጋገር ፍላጎት ቢኖረውም " ራማፎዛ ሥልጣን ላይ እያሉ ንግግር አላደርግም " ማለቱን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።

በዘንድሮ ሀገር አቀፍ ምርጫ እጅግ በርካታ #ወጣቶች ድምፅ መስጠታቸው የተሰማ ሲሆን ገዢውን ፓርቲ የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቤት /ANC/ በድምጻቸው #ቀጥተውታል

ለዚህ ደግሞ  ፦
- የከፋ ሙስና
- የመልካም አስተዳደር ችግር
- ስራ አጥነት መፋፋት
- የወንጀል መባባስ ... ዋነኞቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ተነግሯል።

@tikvahethiopia