TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) ምርጫ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት #ምርጫ ተካሂዷል።

በጅማ ከተማ እየተካሄደ ባለው የፓርቲው 9ኛ ድርጅታዊ ጉባዔ ነው የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫው በዛሬው እለት የተካሄደው።

በዚህም መሰረት፦

1. ዶክተር አብይ አህመድ
2. አቶ ለማ መገርሳ
3. ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ
4. አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ
5. ወይዘሮ አዳነች አቤቤ
6. አቶ አዲሱ አረጋ
7. አቶ ሽመልስ አብዲሳ
8. አቶ ፍቃዱ ተሰማ
9. ዶክተር ዓለሙ ስሜ
የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ሆነው ተመርጠዋል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን⬇️

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን #ወደነበረበት የሚመልስ ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ። ለመጀመርያ ጊዜ በአዲስ አበባ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ይቋቋማል

በግንቦት 1997 ዓ.ም. ከተካሄደው #ምርጫ በኋላ በተፈጠረው ቀውስ ወደ #ፌዴራል መንግሥት የተዘዋወረውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ወደ ከተማው አስተዳደር መመለስ የሚያስችል ረቂቅ ዕቅድ ተዘጋጀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ጥናት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ባካሄደው ጥናት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የራሱ የሆነ አዲስ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እንዲመሠርት ምክረ ሐሳብ አቅርቧል፡፡

የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ባከናወነው ጥናት ላይ የመጀመርያ ዙር ውይይት ረቡዕ መስከረም 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ወቅት በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ፣ ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ›› የተሰኘ አዲስ የካቢኔ አባል የሚሆን ተቋም እንዲመሠረት ሐሳብ ቀርቧል፡፡

ይህ አዲስ ተቋም ላለፉት 14 ዓመታትአስተዳደር በፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሥር ሆኖ የቆየውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በድጋሚ ወደ ከተማው በመመለስ፣ የከተማውን ደንብ ማስከበር አገልግሎትና በክፍለ ከተማና በወረዳ የሚቋቋሙትን የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶችን አቅፎ ይይዛል፡፡

#የአዲስ አበባ ከተማ የፀጥታና ቢሮ ተጠሪነቱ በቀጥታ ለከተማ #አስተዳደሩ ከንቲባ ይሆናል ተብሏል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አደረጃጀትና መዋቅር ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰይፈ ፍቃዱ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የተዘጋጀው ጥናት ለካቢኔ ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ ለአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ቀርቦ ሲፀድቅ ተግባራዊ ይሆናል፡፡

በቀረበው ረቂቅ ጥናት ላይ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 2 እና በቻርተሩ 95 አንቀጽ 10 መሠረት፣ አዲስ አበባ ከተማ ራሱን የማስተዳደር #መብት አለው፡፡

‹‹የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ራሱን በራሱ የማስተዳደር ሙሉ ሥልጣን ይኖረዋል፣ ዝርዝሩ በሕግ ይወሰናል፤›› ሲል ሕገ መንግሥቱ በአንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ ደንግጓል፡፡

ረቂቅ ጥናቱን ያቀረቡት የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤቱ ከፍተኛ አማካሪ አቶ ቤተ ማርያም መኮንን እንዳሉት፣ አዲስ አበባ ከተማ እስካሁን የራሱ የፀጥታ አስተዳደር ቢሮ የለውም፡፡

‹‹ራሱን የቻለ የፀጥታ መዋቅር ባለመኖሩ የከተማውን ነባራዊ ሁኔታ መሠረት ባደረገ መንገድ ባለመደራጀቱ፣ የፀጥታ ተቋማቱ በተለያየ መዋቅር እንዲመሩ ሆኗል፤›› በማለት የገለጹት አቶ ቤተ ማርያም፣ ‹‹አዲስ የፀጥታ አስተዳደር መዋቅር ተግባራዊ ሲሆን ይህ ችግር ይፈታል፤›› ብለዋል፡፡

በአዲሱ መዋቅር መሠረት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ የፀጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤቶች፣ በማዕከል፣ በክፍለ ከተማና በወረዳ ያሉ የደንብ ማስከበር ጽሕፈት ቤቶች በቢሮው ሥር ይተዳደራሉ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ዓመታት የፍትሕ፣ የፀጥታ፣ የሰላም፣ የመልካም አስተዳደርና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች መነሳታቸውን ያስታወሱት ደግሞ፣ የከተማው ፍትሕ ቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ ኤፍሬም ግዛው ናቸው፡፡

ከነዋሪዎች የሚነሱትን እነዚህን ችግሮች ለመፍታት፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ አስተማማኝ ለማድረግ አዲሱ መዋቅር ወሳኝ ድርሻ እንዳለው አቶ ኤፍሬም ተናግረዋል፡፡

ይህ ጥናት እንዲካሄድ መመርያ የሰጠው የከተማ አስተዳደር ካቢኔ በመሆኑ፣ በሒደት ላይ ያሉ ሥራዎች ሲጠናቀቁ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደኢህዴን 10ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት #ምርጫ እያካሄደ ነው፡፡ 70 አባላት ተጠቁሞ የድምፅ ቆጠራ እየተካሄደ ሲሆን እጩዎች :-

1. ጓድ ማስረሻ በላቸው
2. ጓድ ስንታየሁ ወ/ሚካኤል
3. ጓድ የሺዋስ አለሙ
4. ጓዲት ሙፈርያት ካሚል
5. ጓድ አንተነህ ፍቃዱ
6. ጓዲት ማርታ ሉዊጄ
7. ጓድ ሺሰማ ገብረስላሴ
8. ዶ/ር ጌታሁን ጋረደው
9. ጓድ ሚሊዮን ማቴዎስ
10. ጓዲት ፋጤ ሰርሜሎ
11. ጓድ ጥበቡ ዪሃንስ
12. ጓድ ሙሉጌታ ተፈራ
13. ጓድ ደሴ ዳልኬ
14. ጓድ ዘይኑ ጀማል
15. ጓድ ኢንጂነር የማታም ቸኮል
16. ጓድ ዶክተር ቴክሌ ሌዛ
17. ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዪ
18. ጓድ ቃሬ ጫዊቻ
19. ጓዲት ስምረት ግርማ
20. ጓዲት ህይወት ሃይሉ
21. ጓድ መለሰ አለሙ
22. ጓድ ኤልያስ ሽኩር
23. ጓድ አክሊሉ ታደሰ
24. ጓድ ሃይለማርም ተስፋዪ
25. ጓድ አብዱልፈታ የሱፍ
26. ጓድ ተስፋዪ በልጅጌ
27. ጓድ እርስቱ ይርዳው
28. ጓድ ታምራት ዲላ
29. ጓዲት አስቴር ዳዊት
30. ጓዲት ኢ/ር ሌላ አለም ገ/ዮሐንስ
31. ጓድ ክፍሌ ገ/ማሪያም
32. ጓድ አያሌው ዝና
33. ጓድ ዘይኑ ቢታ
34. ጓድ አክሊሉ ለማ
35. ጓድ ሞገስ ባልቻ
36. ጓድአስራት አለማየሁ
37. ጓድአ/ር ምስጋናው አረዳ
38. ጓድ ተስፋዬ ይገዙ
39. ጓድ አብይ አንዳሞ
40. ጓድ አለማየሁ ባውዲ
41. ጓድ ጥላሁን ከበደ
42. ጓድ ዶ/ር ደመቀ አጪሶ
43. ጓድ አብራሃም ማርሻሎ
44. ጓድ ከበደ ሳህለ
45. ጓዲት መሰረት መስቀሌ
46. ጓድ ስኳሬ ሹዳ
47. ጓድ ኃ/ብርሃን ዜና
48. ጓድ አማኑኤል አብደላ
49. ጓድ ምትኩ ካሳ
50. ጓዲት ሂክማ ሐይረዲን
51. ጓድ አሰፋ አቢዩ
52. ጓድ ተፈራ ሞላ
53. ጓድ ፍቅሬ ግዛው
54. ጓድ አስራት አሰፋ
55. ጓድ ታከለ ነጨ
56. ጓድ ኢ/ር ዶ/ር ማርቆስ ተክሌ
57. ጓድ ዋዱ ዳና
58. ጓድ ኡስማን ሱሩር
59. ጓድ አያኖ በራሶ
60. ጓድ አማኑኤል አብረሃም
61. ጓድ ተዘራ ወ/ማሪያም
62. ጓዲት ሄለን ደበበ
63. ጓድ ደገቶ ኩምቤ
64. ጓድ ፍፁም አረጋ
65. ጓዲት አለምፀሐይ ጳውሎስ
66. ጓድ ገ/መስቀል ጫላ
67. ጓድ አልጋየሁ ጅሎ
68. ጓድ በላይ ኮጆአብ
69. ጓድ ብሌን ግዜወርቅ
70. ጓድ ዶ/ር ተሸመ ታደሰ
ናቸው ፡፡ ውጤቱን ዛሬ ምሽት ይፋ ይደረጋል፡፡

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድ🔝

በኢትዮጵያ የሚገኙ ከሰባ በላይ ፓርቲዎች ለሚቀጥለው #ምርጫ እንዲዘጋጁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ጥሪ አቀረቡ።

ከፓርቲዎቹ መሪዎች ጋር ዛሬ ውይይት ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ፤ ከቀጣዩ ምርጫ በፊት ቁጥራቸው ወደ አምስት እና ስድስት ዝቅ እንደሚል ተስፋቸውን ገልፀዋል።

ለቀጣዩ ምርጫ ነፃና ፍትሃዊ መሆን የሚያስፈልጉ ዝግጅቶች በጊዜ ካልተጠናቀቁ ምርጫውን ማራዘሙ የግድ አስፈላጊ ሊሆን እንደሚችል የገለፁት ደግሞ፤ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ናቸው።

ምንጭ፦ VOA አማርኛው አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Election2012

ምርጫ ቦርድ ለሚቀጥለው #ምርጫ የሚውሉ የፕላስቲክ ሳጥኖችን ግዢ እያከናወነ እንደሚገኝ የቦርዱ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች አማካሪ ሶልያና ሽመልስ ገለጹ።ሳጥኖቹ ለ48 ሺህ ምርጫ ጣቢያዎች የሚሆኑ የምርጫ ቁሳቁሶች ታሽገው የሚሰራጩባቸው ናቸው።

(Ethiopia Election)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Election2012

"ኢትዮ-ፎረም" የቴሌቪዥን ዝግጅት ምርጫን የተመለከቱ በርካታ ጥያቄዎች ለምርጫ ቦርድ አባል ለዶ/ር ጌታሁን ካሳ አቅርቧል።" 'ምርጫ ይካሄዳል፤ አይካሄድም' የሚል ክርክር ሲደረግ #ምርጫ ቦርድ ለምን ዝም አለ?"ለሚለው ጥያቄ የሰጡትን መልስ ይመልከቱ።

(Ethiopia Election)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Election2012

"ኢትዮጵያ ውስጥ #ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ አለ ወይ?" በሚል የተጠየቁት ዶ/ር ጌታሁን ካሳ "እኛ እስካሁን ድረስ አለ ብለን ነው የምናምነው" ብለዋል። በ"ኮማንድ ፖስት" ስር ስላሉ ቦታዎች ስለሚቀርበው አቤቱታም ምላሽ ሰጥተዋል።

(Ethiopia Election)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
#Election2012 "ኢትዮጵያ ውስጥ #ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ አለ ወይ?" በሚል የተጠየቁት ዶ/ር ጌታሁን ካሳ "እኛ እስካሁን ድረስ አለ ብለን ነው የምናምነው" ብለዋል። በ"ኮማንድ ፖስት" ስር ስላሉ ቦታዎች ስለሚቀርበው አቤቱታም ምላሽ ሰጥተዋል። (Ethiopia Election) @tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Election2012

የአዲስ አበባና የድሬዳዋ ከተሞች ምክር ቤቶች እንዲሁም የአካባቢ ምርጫዎች ከጠቅላላ ምርጫ ጋር አብረው እንዲካሄዱ በሐምሌ 2011 በፓርላማ ውሳኔ ተላልፎ ነበር። ዶ/ር ጌታሁን ካሳ (የምርጫ ቦርድ አባል) ግን "ቦርዱ እየተዘጋጀ ያለው ለጠቅላላ #ምርጫ ነው" ብለዋል።

(Ethiopia Election)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Election2012

ኦነግ ከኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከሌሎችም ኃይሎች ጋር ግንባር በመፍጠር በመጪው #ምርጫ "ጥሩ ተፎካካሪ" ለመሆን በሂደት ላይ እንደሚገኝ የኦነግ ቃል አቃባይ ቶሌራ አደባ ለፋና ተናግረዋል። ጥምረቱ "እስከ ውህደት" ሊዘልቅ እንደሚችልም ጠቁመዋል።

(ETHIOPIA ELECTION)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Election2012

ለመጪው #ምርጫ ወደ 300,000 ገደማ የምርጫ አስፈጻሚዎች እንደሚመለመሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አባል ብዙወርቅ ከተተ ተናግረዋል። ቦርዱ የምርጫ አስፈጻሚዎችን ለመመልመል እና ለማሰልጠን ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ለፋና ገልጸዋል።

(ETHIOPIA ELECTION)
@tikvahethiopia @tsegabwolde
#Election2012

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ በጀቱን ሲያዘጋጅ የመራጮች ቁጥር 53.9 ሚሊዮን ይደርሳል በሚል ግምት ነበር። እንደ ቦርዱ ግምት በቀጣዩ #ምርጫ 45.3 ሚሊዮን ህዝብ ለመራጭነት ይመዘገባል ተብሎ ይጠበቃል።

(ETHIOPIA ELECTION)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Election2012

በዛሬው የምርጫ ቦርድ የውይይት መድረክ ላይ የ2012 #ምርጫ የጊዜ ሰሌዳን በተመለከተ በቦርዱ ሰብሳቢ፤ ብርቱካን ሚደቅሳ፤ ከሚደረገው ገለጻ በተጨማሪ የቦርዱ "ኦፕሬሽን" አበይት ዕቅዶችም ለተሳታፊዎች ይቀርባል።

#Election2012 #Election2020

(ETHIOPIA ELECTION)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ምርጫ2013

የቁሳቁስ ስርጭትን በተመለከተ በተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ላይ ሰማያዊ ሳጥኖች ተከፍተው መገኘታቸውን ምርጫ ቦርድ አሳወቀ።

ሳጥኖቹን ከፍተው የተገኙበት ምርጫ ክልሎች ላይ አንዳንዶቹ ወደወንጀል ምርመራ ሲላኩ አንዳንዶቹ #ምርጫ_እንዳይካሄድ ተወስኖባቸዋል።

- ደንቢያ የምርጫ ክልል ሰማያዊ ሳጥኖቹ ተከፍተው ፤ ውስጣቸው የድምፅ መስጫ ወረቀቶችን የሚያሳየው የቡክሌት ተከፍቶ ውስጡ ያለውን ነገር አይተው ተገኝቷል፤ በዚህ ምክንያት 3 አስፈፃሚዎች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ለፌዴራል ፖሊስ ደብዳቤ ተፅፏል።

ደምቢያ ምርጫ ክልል የድምፅ መስጫ ቁሳቁሶችን መነካካት ፣ መክፈት በጥብቅ የተከለከለ የወንጀል ተግባር በመሆኑን አስፈፃሚዎች ምርመራ እንዲደረግባቸው ተልኳል።

በደምቢያ ምርጫ ክልል ምርጫው #አይካሄድም

- ተውለደሬ 1 እና 2 ሰማያዊ ሳጥን ተከፍቶ ውስጡ ያሉእጩዎች እነማን እንደሆኑ ፣ የድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ ያሉትን እጩዎች የማየት (ፓርቲዎች ቅሬታ አለን ስላሉ ነው እዩ ተብለን ነው) በሚል ተክፍቶ ታይቷል።

በዚህ ምክንያት ተውለደሬ 1 እና 2 ነገ ድምፅ አይሰጥም፤ ታግዷል።

- ግንደበረት (ኦሮሚያ) ነገ ድምፅ #አይሰጥም ፦ ድምፅ የማይሰጥበት ምክንያት የድምፅ መስጫ ወረቀት እና ቁሳቁስ ስለተከፈተ ሳይሆን የአስፈፃሚዎች እጥረት ነበር። ከዚህ ውጭ ግን ወረዳው አስፈፃሚዎችን አሰልጥኖ ለማስፈፀም ለማሰማራት ሲል በመገኘቱ ገንደበረት ላይ ድምፅ አይሰጥም።

- ነገሌ ምርጫ ክልል (ጉጂ-ኦሮሚያ) ፦ በምርጫ ክልሉ የሚወዳደር የግል ተወዳዳሪ በምርጫ መስጫ ወረቀቱ ላይ ዝርዝሩ ባለመካተቱ ባቀረበው ቅሬታ መሰረት ቦርዱ ምርጫውን ወደ ጳጉሜ 1 አዛውሮታል።

#TikvahEthiopia #SolianaShimeles

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር ከነገ መስከረም 23 ጀምሮ የብሔራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ የልምምድ ፈተና (Mock Exam) መሰጠት እንደሚጀመር አሳውቋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሠጠው ብሔራዊ የድህረ-ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ከመስከረም 28 እስከ 30 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል። ሚኒስቴሩ ፤ በሁሉም የመንግስትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት…
" ፈተናው የምርጫ ጥያቄዎችን የያዘ ነው " - ትምህርት ሚኒስቴር

ትምህርት ሚኒስቴር ከመስከረም 28 እስከ 30 /2016 ዓ/ም በሀገር ደረጃ የሚሰጠው የድህረ ምረቃ ትምህርት የመግቢያ ፈተና ወጥ በሆነ መንገድ በአንድ የፈተና መተግበሪያ የሚከወን መሆኑን ገልጿል።

ፈተናው #ምርጫ_ጥያቄዎችን የያዘ ነው ብሏል።

ለፈተናው 53 የፈተና ማእከላት እና 84 የፈተና ጣቢዎች የተዘጋጁ ሲሆን በግማሽ ቀን ውስጥ የሚጠናቀቅ ይሆናል ተብሎ ታቅዷል።

አይነስውራን ተፈታኞች የቃል እና ምክንያታዊ አስተሣሠብ ክህሎቶቻቸው ላይ ያተኮሩ ፈተናዎችን ይወስዳሉ ያለው ሚኒስቴሩ በወሠዱትም ፈተና ከ100% ይመዘናሉ ብሏል።

ብሄራዊ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ጥያቄዎች አመልካቾች መርጠው በሚያመለክቱበት የትምህርት መስክ ላይ ትኩረት ያደረገ እንዳልሆነ ትምህርት ሚኒስቴትር ገልጿል።

ትምህርት ሚኒስቴር የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና ዓላማ ፦

- በግል እና በመንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተው የድህረ ምረቃ ትምህርት በ2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ገብቶ ትምህርት ለመከታተል ፍላጎት ያላቸውን አመልካቾች ብቃት ለመመዘን፤

- ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራሞች የሚገቡ ተማሪዎች ሂሣባዊ ትንተና (Quantitative reasoning) ፣ ምክናያታዊ አስተሳሠብ (Analytical reasoning) ፣ የቃልና የጹህፍ ከህሎት ለመመዘን ነው ሲል አስታውሷል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹 " አሁን ላይ ያሉ ችግሮች ምፍትሄ እስካላገኙ  ስለ ምርጫ ማሰብ #ቀልድ ነው " - አቶ ግርማ በቀለ የሕብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሕብር) ሊቀ መንበር አቶ ግርማ በቀለ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ቆይታ አድረገዋል። Q. የዜጎች በሕይወት የመኖር መብት ጥሰትን በተመለከተ ስለሚነሱ ጉዳዮች የፓርቲዎ ግምገማ ምን ይላል ?   አቶ ግርማ…
🇪🇹 የፖለቲካ ፓርቲዎች ምን ይላሉ ? 🇪🇹

“ ... ያለፉትን ዘመናት እኮ #እንደ_ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው ” - ጎጎት ፓርቲ

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ' #የፖለቲካ_ፓርቲዎች_ምን_ይላሉ ? ' በሚል በህጋዊ መንገድ ተመዝገበው ለሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እያቀረበ ያለውን ወቅታዊ ሀገራዊ ጥያቄዎች በመቀጠል ጎጎት ፓርቲን አነጋግሯል።

የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ጀሚል ሳኒ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል።

Q. ከዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ጥሰት አንፃር የፓርቲዎን ግምገማና መፍትሄውን ቢገልጹ ?

አቶ ጀሚል ሳኒ፦

“ ሰዎች በተደጋጋሚ ሕይወታቸውን እያጡ ነው። በዋና ከተማዋ ሲይቀር ሰዎች እየታሰሩ፣ እየታገቱ ነው።

የትኛውም ዜጋ የደህንነት ስሜት እየተሰማው አይደለም። 

መንግስት #በዋነኛነት የተመሠረተበትና እንዲሰራው ኃላፊነት የተሰጠው ስራ ከየትኛውም ቅድሚያ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ የተዘነጋ የሚመስልበት ዘመን ላይ ነን።

በመወያየትና በመነጋገር ጦርነትን ማስቆም ይገባል።

ሰላምን ከማስፈን ይልቅ #ስልጣንን_የመጠበቅ ፣ የፕሮፓጋንዳ ስራ በመስራት ነው አብዛኛው አቅም እየባከነ ያለው።

ከዚያ ይልቅ አገሪቱን በሚያሻግሩ ሀሳቦች ላይ አተኩሮ መስራት ያስፈልጋል።

ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦተ እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው። ”

Q. በሙስና ተዘፍቀው ስለሚገኙ ባለስልጣናት እንዲሁም በአጠቃላይ ስለብልሹ አሰራር ፓርቲዎ ምን ይላል ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ አሁን ላይ #ሀዘኔታዎች_የጠፉበት ፣ ሌላው ይቅርና የዜጎች ቤቶች ‘ሕገ ወጥ ናቸው’ ተብለው ቤታቸው የሚፈርስባቸው ሰዎች ላይ ገንዘብ የሚጠየቅበት ሁኔታ ነው ያለው። 

ከኢትዮጵያ Norm ሁላ ያፈነገጠበት ወቅት ላይ ነው ያለነው። በአብዛኛዎቹ መስሪያ ቤቶች የተለመደውን አይነት አሰራር ከመስራት ይልቅ ከእግሮች እጆች እየቀደሙ ነው።

#ሙስና_በግልጽ_እየተጠየቀ ፣ ቢሮ ውስጥ ሥራ አስፈጻሚዎች #በግልጽ_ድርድር እያደረጉበት ያለበት ሂደት ነው አሁን ያለው።

አለ የተባለ የትኛውም ችግርን ለመቅረፍ ላይከብድ ይችላል ፤ ነገር ግን ከተንሰራፋ የትኛውንም ችግር ልቅረፍ ማለት የማይታሰብ ይሆናል። 

ሙስና የሀገር ተቋርቋሪነትን፣ ስሜትን ያጠፋል።

እያየነው ያለውም ይሄው ነውና ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።”

Q. እንደ ፓርቲ የሚደርስባችሁ ጫና ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የምስረታ ጉባዔ ባደረግንበት፣ የጉባዔውን ውጤትና የምርጫ ቦርድ ኮሮጆ ጭምር ይዘን በነበረበት ሰዓት ነው እስር የተጀመረው። ክፍለ አገርም አዲስ አበባም እስሮች አሉ። 

በአባል ደረጃ አንድ የፓርቲው አባል ከ5 ወራት በላይ ያለ ክስና ዋስትና በእስር ላይ ይገኛሉ። ከአባላቶች እስራትና ተንቀሳቅሶ ከመስራት ጋር ዘተያያዘ ያለፉትን ዘመናት እንደ ቅንጦት እንድናይ የተገደድንበት ጊዜ ነው።

ፓርቲውን የሚደግፉ አባላት #ወጣቶች_እየተላኩ ማስፈራሪያ ያደርሱባቸዋል።

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ሕገ መንግስቱን ያልከተለ በመሆኑ ምስረታው እንዲታገድ፣ ኢ - ሕገ መንግስታዊ ስራዎች በሰሩ ባለስልጣናት ላይ የመሰረትነው ክስ በቀጠሮ እየተጉላላ ነው ያለው። ”

Q. ሕዝቡ በኑሮ ውድነቱ ተማሯል። ለዚህም “ መንግስት ትኩረት አልሰጠም  ” የሚሉ ወቀሳዎች ይቀርባሉ። የፓርቲዎ ግምገማ ምንድን ነው ?

አቶ ጀሚል ሳኒ ፦

“ የኑሮ ውድነት በራሱ የሚፈጠር ነገር አይደለም። እስካሁን ከላይ የተነጋገርንባቸው ነገሮች ናቸው እየገፉ የሚያመጡት። 

አንዲት አገር #በጦርነት ላይ ሆና ሚሊዮን ዶላሮችም ለጦርነት እያወጣች ፣ አርሶአደር ማምረትና በሰላም ወጥቶ መግባት ባልቻለበት ፣ የመልካም አስተዳደር ፣ የአቅም ፣ የብቃት ጉዳዮች የመጨረሻ ውጤታቸው የኑሮ ውድነቱ ማምጣት ነው።

እነዚህን ችግሮች ማጥፋት፣ መቀነስ ካልተቻለ የኑሮ ውድነቱን ማረጋጋት፣ የተረጋጋ ኢኮኖሚ ማስፈን አይቻልም። ”

Q. ስለምርጫ ያላችሁ አስተያዬት ምንድን ነው ? በቀጣዩ ሀገራዊ
ምርጫ ተመራጭ ሆኖ ለመቅረብ ዝግጅት እያደረጋችሁ ነው ?

“ ከምርጫ ጋር በተገናኘ ትኩረት ተደርጎ የሚሰራው፣ አጀንዳውም የሚያዘው ከሚደረገው #የፓርላማ እና #የክልል_ምክር_ቤቶች ጋር በተገናኘ ነው። 

ይሄ ስርዓቱን ለመቀየር የሚያስችል ብቸኛው መንገድ አይደለም። ከዚህ ይልቅ ምርጫ በየአካባቢው ማድረግ ያስፈልጋል። የአካባቢ ምርጫ የተደረገው ከ8 ዓመታት በፊት ነው።

የአካባቢ ምርጫ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል።

አሁን ባለንበት ሁኔታ ላይ #ምርጫ ሊደረግ ይችላል ብሎ ማለት ትንሽ አዳጋች ነው። ”

◾️በቀጣዩ የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ፓርቲ የሰጠው ቃል ይቀርባል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia