TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማሳሰቢያ፦ TIKVAH-ETH ከየትኛውም የመንግስትም ሆነ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ጋር ግንኙነት የለውም። TIKVAH-ETH ትክክለኛ የኢትዮጵያን ቀለም የያያዙ #የጀግና ሀገር ወዳድ ወጣቶች ስብስብ ነው።

በተለይ የStopHateSpeech ጉዞ ከየትኛውም ወገን ድጋፍ የለውም፦ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጡን #መኪና ብቻ ነው። አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎቻቸው ለጉዞ የሚሆን ጥቂት ገንዘብ/ለድንገተኛ ጉዳዮች/ የሚሰጡት ካልሆነ ምንም አይነት አበል የለውም/እስካሁን የተሰጠውንም በቀጣይ ሳምንት ይፋ አደርጋለሁ/። ተማሪዎች የሚመገቡት በዩኒቨርሲቲ ካፌ ነው። "አበላችን እና ክፍያችን #ፍቅር ነው" ይህ ነው ቃላቸው!!

ሌላው፦
√በራሪ ወረቀት፣ ባነር የሚያሳትምልን ድርጅት ባለመኖሩ በራሳችን ወጪ ነው የምንሰራው።
√ተማሪው በጉዞ መሃል ለሚያፈልግው ወጪ ከራሱ ከኪሱ ነው የሚጠቀመው።
√ቢታመም እንኳን ገንዘብ ሳይኖረው ነው ለእናት ሀገር ሰላም የሚጓዘው።

ወጣቶቹ ትምህርታቸውን ጥለው፣ በአካዳሚክ ጉዳዮች ተጎድተው፣ ተንገላተው፣ ተርበው፣ ለፍተው እየዞሩ ያሉት ለፍቅር ነው፤ ለትውልዱ ሰርቶ ለማለፍ ነው፤ ሀገር ሲበጠበጥ ቁጭ ብሎ ላለማውራት ነው፤ ከህሊና እዳ ነፃ ለመሆን ነው፤ ለሀገሬ ምን ልስራላት በማለት ነው፤ ለሀገር ሰላም እና አንድነት መምጣት ከወጣቶች ውጪ አማራጭ ስለሌለ ነው።

መላው የኢትዮጵያ ህዝብ እነዚህን #ወጣቶች የሚያስታውስበት ቀን እሩቅ አይደለም፤ ለምን እንደሚዞሩም የሚረዳበት ቀን ሩቅ አይሆንም፤ በሀገራችን ለተፈጠሩ እና እየተፈጠሩ ላሉ ግጭቶች ዋነኛው መንስኤ የጥላቻ ንግግር እና ጥላቻ ነው።

•ኦሮሚያ
•ትግራይ
•አማራ
•ደቡብ በፍቅር አቅፍችሁ #ስለተቀበላችሁን እናመሰግናለን!!

ኑ ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde