The Christian News
5.15K subscribers
3.04K photos
25 videos
714 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
የሕብረት መሪዎች
ወቅታዊ ምላሽ ምን ይሁን?
-------------------
#የኮሮና_ቫይረስ ስርጭት ለመግታት መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እየተከታተልን ነው። የእግዚአብሔር ምህረት እንዲበዛ፤ በፀሎት #የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ጀምረናል። እሱ ይራራልን!

ዩኒቨርሲቲና ኮሌጆች ባይዘጉም እንቅስቃሴዎችና ስብሰባዎች ተገተዋል።

ኢቫሱ፣ የሚያስተባብራቸው የተማሪ ሕብረቶች ምላሽ ምን መሆን እንዳለበት በደብዳቤ ለሁሉም ሕብረቶች እንዲያውቁት ተደርጓል፡፡ በዋናነት የተማሪ ሕብረት አገልግሎት #ሣይቋረጥ ነገር ግን #የስልት ለውጥ በማድረግ መቀጠልን የሚያበረታታ ውሳኔ ተላልፏል፡፡

በዚህ ወቅት በሕብረት ውስጥ በልዩ ልዩ የአገልግሎት ዘርፍ #የመሪነት_ድርሻ ያላችሁ ተማሪዎች ትልቅ ኃላፊነት ወድቆባችኋል።

* የተማሪ ሕብረት አገልግሎቱን በእንዴት ያለ ሁኔታ እናስቀጥለው?

* በዚህ ወቅት የአገልግሎት ትኩረታችን ምን መሆን አለበት?

* አማራጭ የአገልግሎት መንገዶች ምን ምን ናቸው?

* ስርጭቱን ለመግታት የሕብረት አባላት ድርሻቸው ምንድነው?

* በዚህ ወሳኝ ጊዜ የሕብረት ልዩ ልዩ መሪዎች [#ዋና እና #የዘርፍ አገልግሎት መሪዎች፣ የፀሎትና የወንጌል #ሞብላይዘርስ፣ የንዑስ ቡድን እና የባች #አስተባባሪዎች፣…ወዘተ] የሚጫወቱት ሚና ምን መምሰል አለበት?

* የዚህ ወቅት የሕበረቱ የአገልግሎት ተግዳሮቶች ምንድናቸው? እንዴት እንፍታቸው?

* በኮሮና ቫይረስ የተያዙ የሕብረት #አባላት ቢኖሩ ምላሻችን ምን ዐይነት ይሁን?

* በቫይረሱ የተጠቁ #አማኝ_ያልሆኑ ተማሪዎችና የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አካላትን በተመለከተ አተያያችንና ምላሾቻችን ምን መሆን ይኖርበታል?

እነዚህን የመሳሰሉ ጉዳዮችን በጥልቅተ በመመልከት መልስ መስጠት አለባችሁ። ጉዳዩ፣ የእግዚአብሔርን #ምሪት መከተል፣#ፀሎትና #ምክክር ይፈልጋል።
---------
በፀሎትና በምክር አብረናችሁ ነን!
ለበረከት ሁኑ!
-----
ኢቫሱን ይቀላቀሉ
@EvaSUE58

@TCNEW
የመዘምራን የጋራ የምክክር #ጊዜ ተካሄደ፡፡

#በኢትዮጵያ #ሙሉ ወንጌል አማኞች #ቤተክርስቲያን #በአዲስ #አበባ እና አከባቢው ሶስት ክልሎች ውስጥ ከሚገኙ አጥቢያዎች የተሳተፉበት የጋራ የምክክር ጊዜ ተከናወነ።

በቀጠና ሁለት ሙሉወንጌል ቤተክርስቲያን በተካሔደዉ መረሀ ግብር መዘምራን፣ የሙዚቃ ተጫዋቾች እና የሶሎ ዘማርያን የተገኙ ሲሆን አገልግሎት የበለጠ ፍሬያማ ለማድረግ እንዲሁም በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ካሉ የቀድሞና አሁን በማገልገል ላይ ካሉ የሙሉ #ወንጌል መዘምራን #አባላት ጋር ሕብረትን ለማጠናከርና ያሉንን ጠንካራ እሴቶች ለማስቀጠል ቃል ተገብቷል ፡፡

በፕሮግራሙ የጎተራ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ D መዘምራን እና የስድስት ኪሎ ሙሉ ወንጌል አጥቢያ አሳፍ መዘምራን ያገለገሉ ሲሆን ፓስተር ደበበ ለማ ( ጋሽ ደቤ )፣ ፓስተር ሳሙኤል ወንድሙ ከአትላንታ እና ፓስተር ኤርሚያስ ገ/መድህን ልዩ ልዩ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡