The Christian News
5.37K subscribers
3.07K photos
27 videos
724 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
የሕብረት መሪዎች
ወቅታዊ ምላሽ ምን ይሁን?
-------------------
#የኮሮና_ቫይረስ ስርጭት ለመግታት መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ እየተከታተልን ነው። የእግዚአብሔር ምህረት እንዲበዛ፤ በፀሎት #የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ጀምረናል። እሱ ይራራልን!

ዩኒቨርሲቲና ኮሌጆች ባይዘጉም እንቅስቃሴዎችና ስብሰባዎች ተገተዋል።

ኢቫሱ፣ የሚያስተባብራቸው የተማሪ ሕብረቶች ምላሽ ምን መሆን እንዳለበት በደብዳቤ ለሁሉም ሕብረቶች እንዲያውቁት ተደርጓል፡፡ በዋናነት የተማሪ ሕብረት አገልግሎት #ሣይቋረጥ ነገር ግን #የስልት ለውጥ በማድረግ መቀጠልን የሚያበረታታ ውሳኔ ተላልፏል፡፡

በዚህ ወቅት በሕብረት ውስጥ በልዩ ልዩ የአገልግሎት ዘርፍ #የመሪነት_ድርሻ ያላችሁ ተማሪዎች ትልቅ ኃላፊነት ወድቆባችኋል።

* የተማሪ ሕብረት አገልግሎቱን በእንዴት ያለ ሁኔታ እናስቀጥለው?

* በዚህ ወቅት የአገልግሎት ትኩረታችን ምን መሆን አለበት?

* አማራጭ የአገልግሎት መንገዶች ምን ምን ናቸው?

* ስርጭቱን ለመግታት የሕብረት አባላት ድርሻቸው ምንድነው?

* በዚህ ወሳኝ ጊዜ የሕብረት ልዩ ልዩ መሪዎች [#ዋና እና #የዘርፍ አገልግሎት መሪዎች፣ የፀሎትና የወንጌል #ሞብላይዘርስ፣ የንዑስ ቡድን እና የባች #አስተባባሪዎች፣…ወዘተ] የሚጫወቱት ሚና ምን መምሰል አለበት?

* የዚህ ወቅት የሕበረቱ የአገልግሎት ተግዳሮቶች ምንድናቸው? እንዴት እንፍታቸው?

* በኮሮና ቫይረስ የተያዙ የሕብረት #አባላት ቢኖሩ ምላሻችን ምን ዐይነት ይሁን?

* በቫይረሱ የተጠቁ #አማኝ_ያልሆኑ ተማሪዎችና የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አካላትን በተመለከተ አተያያችንና ምላሾቻችን ምን መሆን ይኖርበታል?

እነዚህን የመሳሰሉ ጉዳዮችን በጥልቅተ በመመልከት መልስ መስጠት አለባችሁ። ጉዳዩ፣ የእግዚአብሔርን #ምሪት መከተል፣#ፀሎትና #ምክክር ይፈልጋል።
---------
በፀሎትና በምክር አብረናችሁ ነን!
ለበረከት ሁኑ!
-----
ኢቫሱን ይቀላቀሉ
@EvaSUE58

@TCNEW
#ኑ #የእግዚአብሔርን #ቤት በጋራ እንስራ!!!

ለብዙዎች መጠለያ የሆነችው እና ለአርሲ ዩንቨርስቲ አሰላ ካምፓስ ክርስቲያን ተማሪዎች ህብረት ማምለኪያ የሆነችው የአሰላ አርዱ ቁጥር 2 #ሙሉ #ወንጌል ቤተክርስትያን #ዛሬ የሁላችንን እገዛ ትፈልጋለች።

#አሁን የምትገኝበት የማምለኪያ አዳራሽ የአምልኮ ፕሮግራም ለመካፈል የሚመጡትን አማኞች መያዝ ስላልቻለ እና እንዲሁም የአሁኑ አዳራሽ እየፈረሠ ስለሚገኝ ከአጥቢያዋ በረከት የተካፈላችሁ በዓለም ዙሪያ እንዲሁም በሃገር ውስጥ የምትገኙ የአሰላ አርዱ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን ቤተሰቦች ወዳጆች እንዲሁም #የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ለዚህ ስራ እጆቻቸሁን እንድታበረቱ ስንል በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን።

ከዚህም ጋር ተያይዞ ከመጋቢት 6 እስከ 8/2016 ዓ.ም በአጥቢያዋ የተዘጋጀ #ልዩ ኮንፍራንስ ስላለ በቦታው በመገኘት በዚህ የወንጌል ስራ እንድትሳተፉ #በጌታ #ፍቅር እንጠይቃለን።

በተጨማሪም በቦታው መገኘት የማትችሉ ከታች በመተቀመጠው የቤተክርስቲያኒቷ አካውንት እጆቻችሁን ትዘረጉ ዘንድ በጌታ ፍቅር እንጠይቃለን።

1000515969962 ንግድ ባንክ
1600860054837 ብርሃን ባንክ

የአሰላ አርዱ ሙሉ ወንጌል #ቤተክርስቲያን