STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
40.8K subscribers
11K photos
271 videos
452 files
1.93K links
የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ከሰዓታት በፊት #በድሬደዋ ረዘም ላለ ጊዜ የጣለው ዝናብ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ጎርፍ አስከትሏል❗️

ቁጥሩ በውል አይታውቅ እንጂ የተወሰኑ መኖርያ ቤቶችን ማፍረሱን እና አንዳንድ ንብረቶችንም ማበላሸቱን የድሬደዋ አስተዳደር ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን ዲቪዥን ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ባንታለም ግርማ ለዶይቼ ቬለ ገልፀዋል። በጎርፍ ሊወሰድ የነበረ አንድ ሰው ህይወት በፖሊስ መትረፉን አስታውቀዋል።

ከተማዋን ሁለት ከፍሎ የሚያልፈው የአሸዋ መውረጃም መጠኑ ከፍ ያለ ጎርፍ መጥቶበታል። ለአንድ ሰዓት ያህል የቆየው ዝናብ ጋብ ባለበት ጊዜ የተወሰደ ቪድዮ ተያይዟል።

#ማሳሰቢያ ❗️
⚠️ ከሰሞንኛው የአየር ትንበያ ጋር በተገናኘ ዛሬ የጣለው ዝናብ እና ያስከተለው ጎርፍ እንደ ማንቂያ ደውል ሊወሰድ እንደሚገባው ተገልፃ።


Via-ThinkAbyssinia

#SHARE
ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
@NATIONALEXAMSRESULT
#ማሳሰቢያ_ለቦንጋ_ዩኒቨርሲቲ_ተመራቂዎች_በሙሉ‼️

በቅርቡ ቦንጋ ዩንቨርሲቲያ ተመራቂ ተማሪዎችን ለመቀበል የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁ ይታወቃል። ሆኖም ግን ብዙ ተማሪዎች በስልክ እና በተለያዩ መንገዶች ስለ መግቢያ ቀን እየጠየቃችሁን ይገኛል።

በመሆኑም ማንኛውም ዩኒቨርሲቲ ያለ ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እውቅና መጥራት አይችልም። ይህም ማለት ሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እውቅና የሚሰጠው ጥቅምት 05/2013 ዓ.ም በሀዋሳ በሚካሄደው ጉባኤ ላይ ይሆናል። በሀዋሳ ከሚካሄደው ስብሰባ በኋላ ከጥቅምት 08/2013 ጀምሮ መጥራት እንደሚችሉ ተገልጿል።

ነገር ግን ከዚህ ቀደም በሰማችሁት የድምፅ መልዕክት የተገለፀው የተማሪዎች የመግቢያ ቀን ሳይሆን የዩኒቨርስቲው ጊዜያዊ ቅድመ-ዝግጅት እቅድ ፕሮግራም ነው። ስለዚህ ዩኒቨርስቲው ምንም አይነት ጥሪ አላደረገም።

በመጨረሻም ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ትክክለኛ የተማሪዎች የመግቢያ ቀን ሲያሳውቅ በሚዲያ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው እና የተማሪዎች ህብረት የፌስቡክ እና የቴሌግራም ቻናል ብቻ የሚገለፅ ይሆናል።

It is known that our university has recently completed the preparation work to receive the graduating students. However, many students are asking us about admission by calling phone and in various ways.

Therefore, any university can't be registered without the approval of the Ministry of Science and Higher Education. This means the Ministry of Science and Higher Education will be recognized at the conference to be held in Hawassa on October 05/2013 E.C. It is stated that after the meeting in Hawassa, all university can registered students from October 08/2013 E.C

However, the voice message you heard is not the student admission date. It is the university's pre-planning Scheduled. So the university did not make any admission announce.

Finally, when Bonga University announces the exact date of registration, it will be announced only by the media as well as the university and the student union's Facebook and Telegram channel.

መረጃው እንዲዳረስ ለሌሎች ያጋሩ!
Share the information with others!

ምንጭ:- የቦንጋ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ህብረት | Bonga University Student's Union |

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
 የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቅያ (12ኛ ክፍል) ብሄራዊ ፈተና መደበኛና የማታ ተማሪዎች የሚመዘገቡት በ2012 ዓ.ም በመማር ላይ ባሉበት ትምህርት ቤት ይሆናል፡፡

 የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቅያ (12ኛ ክፍል) ብሄራዊ ፈተና የግል አመልካቾች እና በርቀት ትምህርት የሚከታተሉ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው በሚኖሩበት አካባቢ በሚገኘው የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሲሆን፤ በአዲስ አበባ የሚገኙት ግን በሚኖሩበት ክፍለ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች ባሉባቸው የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች ወይም ጽ/ቤቱ በሚያዘጋጀው የምዝገባ ጣቢያ ይሆናል፡፡

#ማሳሰቢያ፡-
 ምዝገባው የሚካሄደው በኦንላይ (Online) ሲሆን መደበኛና የማታ ተፈታኝ ተማሪዎች የሚመዘገቡት በ2012 ዓ.ም በመማር ላይ ባሉበት ትምህርት ቤት ይሆናል፡፡

 በተጨማሪም የኤጀንሲውን ዌብሳይት www.neaea.gov.et ወይም የኤጀንሲው ማህበራዊ ገጽ National Educational Assessment And Examinations Agency Government Organization ይጎብኙ፡፡

©ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና የፈተናዎች ኤጀንሲ

#SHARE
ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
የጥሪ ማስታወቂያ ለደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ!

በኮቪድ-19 ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርት ለማስቀጠል፣ በ2012 ዓ.ም ትመረቁ ለነበራችሁ የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ከታህሳስ 1 እስከ 2 መሆኑን እንገልፃለን።

ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞ ወይም ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑንም እናሳውቃለን።

#ማሳሰቢያ :- ተመራቂ ያልሆናችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜያችሁን በሌላ የጥሪ ማስታወቂያ እስክናሳውቃችሁ ድረስ በትዕግስት ትጠብቁን ዘንድ እናሳስባለን።

#SHARE
ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
#ይፋዊ

በ2013 የትምህርት ዘመን በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራም መደበኛ መርሃግብር ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀን ሰኔ 23 እና 24 /2013 ነው።

ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ስትሄዱ ፦

- ከ9-12 ትራንስሪፕት ኦርጂናል እና ፎቶ ኮፒ
- የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርተፊኬህ ኦርጂናል እና ኮፒ
- በቅርብ ጊዜ የተነሳችሁት 3በ4 ጉርድ ፎቶግራፍ (6 ብዛት)
- አንሶላ ፣ ብርድልብስ፣ የትራስ ጨርቅ
- የስፖርት ትጥቅ

በዘመናዊ የተማሪዎች መረጃ አያያዝ (SIS) ለመመዝገብ የሚያስፈልጉ softcopy መረጃዎች ፦

- ከ9-12 ትራንስክሪፕት በPDF ፎርማት
- የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ስረተፊኬት በPDF ፎርማት
- በቅርብ ጊዜ የተነሳችሁት ፎቶግራፍ በJPEG ፎርማት ሁሉም ከ2 MB መብለጥ የለበትም።

SIS ኦንላይ እንዴት መመዝገብ እንዳለባችሁ የቪድዮ ቲቶሪያ uog.edu.et./registrar/online-registration-vedio-tutorial/ የሚለውን ሊንክ ተጠቀሙ።

የኦንላንይ ምዘግባ የሚካሄደው ከላይ በተገለፁት ቀናት ነው።

#ማሳሰቢያ : ከላይ ከተገለፀው ቀናት ቀድሞ ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ ዩኒቨርሲቲው አያስተናግድም።

ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
#ማስታወቂያ ❗️

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ለ2013 የትምህርት ዘመን በመደበኛ የዲግሪ ትምህርት መርሃ-ግብር በትምህርት ሚ/ር መስፈርት መሠረት አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ ሰኔ 01 ቀን 2013 ዓ.ም እና ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም በ http://portal .aau.edu.et በመጠቀም የኦንላየን ምዝገባ እንድታከናውኑ እያሳሰብን፡

1. በተመደባችሁበት የዩኒቨርስቲው ካምፓስ ሪፖርት የምታደርጉት ሰኔ 19 እና ሰኔ 20 2013 ዓ.ም

2. የገጽ ለገጽ ትምህርት የሚጀመረው ሰኞ ሰኔ 21 ቀን 2013 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

#ማሳሰቢያ
የሚከተሉትን መረጃዎች በ www. aau.edu.et ስለሚገኙ ከወዲሁ እንድትጠቀሙባቸውና አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን፡፡

1. ምዝገባችሁን ከወዲሁ እንዴት ማከናወን እንዳለባችሁ፤

2. የተመደባችሁበትን የዩኒቨርሲቲ ካምፓስ መኝታ ቤት ቁጥር እንዴት ማወቅ እንደምትችሉ፤

3. ለአንደኛ ሰሚስተር ትምህታችሁ የምትጠቀሙባቸው በዩኒቨርስቲው የተዘጋጁ ሞዱሎችን ለማግኘት፤

4. በዩኒቨርሲቲዉ ዉስጥ በምትቆዩበት ግዜ ማወቅ ስላለባችሁ የአካዳሚክ እና ሌሎች ደንቦችና መመሪያዎች፤

©አዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ


ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
የጥሪ ማስታወቂያ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2013 ዓ.ም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች ምዝገባ በበየነመረብ ”Online” ከሰኔ 15-20/2013 ዓ.ም ድረስ የሚከናወን ሲሆን የተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ #የመግቢያ_ጊዜ ሰኔ 21-22/2013 ዓ.ም መሆኑን ይገልጻል፡፡

#ማሳሰቢያ
ስለ ምዝገባ ሂደቱ ዝርዝር መረጃዎችን ከዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ ፌስቡክና ቴሌግራም አካውንት ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡

ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ የሚከተሉትን ይዘው መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡

1ኛ. የመስናዶና 10ኛ ክፍል ያለፋችሁበት ሰርተፍኬት
2ኛ. ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክርቢት
3ኛ. የሌሊት አልባሳት
4ኛ. 8 ጉርድ ፎቶግራፍ
5ኛ. የስፖርት ትጥቅ

ተማሪዎች በጉዞ ወቅት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል በመጠቀም እራሳቸውን ከኮቪድ በሽታ መጠበቅ እንዳለባቸው እያሳሰብን ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኋላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡

© የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር እና አልሙኒ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት


ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
#DebreBirhanUniversity

ለደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መደበኛ የመጀመሪያና የድህረምረቃ ተማሪዎች በሙሉ

1. ከአዲግራት ዩኒቨርስቲ በጊዜያዊነት ወደ ደብረ ብርሃን ዩነቨርስቲ በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች

2. በ2013 ዓ.ም. የ1ኛ መንፈቅ ዓመት ትምህርታችሁን አጠናቃችሁ የነበራችሁ የ3ኛ ዓመች የዩኒቨርስቲያችን ተማሪዎች በሙሉ

3. በ2014 ዓ.ም. በምህንድስና ኮሌጅ ስር Intemship የምትወጡ ተማሪዎች

4. በ2014 ዓ.ም. በተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ ስር ለመስክ ትምህርት የምትወጡ
➢ የ4ኛ ዓመት የጂኦሎጂ ተማሪዎች እና
➢ የ4ኛ ዓመት የባዮ ቴክኖሎጂ ተማሪዎች በሙሉ 👉 የምዝገባ ቀን #የካቲት 14 እና 15 2014 ዓ.ም መሆኑን እየገለጽን፤

5. ከላይ ከተገለጹት ውጭ ያላችሁ የ3ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች እንዲሁም አዲስና ነባር የድህረ ምረቃ ተማሪዎች በሙሉ የምዝገባ ቀናት #የካቲት 19 እና 20 2014 ዓ.ም መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

#ማሳሰቢያ

የመመዝገቢያ ቦታ በዋናው ግቢ በየኮሌጃችሁ ሬጂስትራር ክፍል ይሆናል።
• ከአዲግራት ዩኒቨርስቲ ወደ ዩኒቨርስቲያችን የተመደባችሁ ተማሪዎች የ8ኛ፣ የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን ዋና እና ፎቶ ኮፒውን ! በአዲግራት ዩኒቨርስቲ ቆይታችሁ በእጃችሁ የሚገኙ ማንኛውንም የግል የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን (ግሬድ ሪፖርትና የተማሪ መታወቂያ) ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኋል።

የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሬጂስተራር እና
አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#UPDATE

ዝውውር በላኪና ተቀባይ ዩንቨርሲቲዎች የጋራ ስምምነት ይፈፀም ዘንድ ትምህርት ሚኒስቴር ወሰነ።

ትምህርት ሚኒስቴር ዝውውርን በተመለከተ ያለፉትን ጥቂት አመታት ሲጠቀምበት የነበረውን ማለትም ዝውውር የሚጠይቁ ተማሪዎች ከመንግስት ሆስፒታሎች በህክምና ቦርዶ የተረጋገጠ ማስረጃ ይዘው ለመስሪያ ቤቱ በማቅረብ ዝውውር ይፈፅም የነበረውን ስርዓት የተማሪዎችን ጊዜ እና ገንዘብ ወጪ እያስደረገ መሆኑን በማየት ዝውውርን በተቀባይና በላኪ ዩንቨርሲቲዎች የጋራ ስምምነት ይፈፀም ዘንድ ውሳኔ አስተላልፏል።

#ማሳሰቢያ

ዝውውር የሚጠይቁ ተማሪዎች ከመንግስት የህክምና ተቋማት የህክምና ቦርድ ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
#የጥሪ ማስታወቂያ
#GambellaUniversity

በ2014 ዓ.ም በጋምቤላ ዩኒቨርስቲ የተመደባችሁ የቅድመ ምረቃ መደበኛ መርሃ-ግብር ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄደው #ከግንቦት_29 30/2014 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ቀን በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ውድ ተማሪዎቻችን ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ፡

1ኛ. የ8ኛ፣ 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ክልላዊና ብሔራዊ ፈተና ውጤት ሰርተፊኬቶች ዋና እና የማይመለስ 1 ኮፒ፣

2ኛ. ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ዋና ትራንስክሪፕት ከማይመለስ 1 ኮፒ ጋር እንዲሁም ስድስት 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣

3ኛ. አንሶላ፣ የትራስ ጨርቅና የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡

#ማሳሰቢያ፡ከተጠቀሰው ቀን ቀድመውም ሆነ ዘግይተው የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ለበለጠ መረጃ የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገፅ WWW.gmu.edu.et ይጎብኙ፡፡

ተማሪ ነክ መረጃዎችን እንዘግባለን
@NATIONALEXAMSRESULT
STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
🎯ለአዲስ አበባ ተማሪዎች የመፈተኛ ጣቢያ ምደባ 🧧 Share ይደረግ ተማሪ ነክ መረጃዎች ያግኙ @NATIONALEXAMSRESULT
#ማሳሰቢያ

ኢንትራንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ይዘው መሄድ የማይፈቀድላቸው ነገሮች

ማንኛውም ድምፅ የሚቀዳ፣ፎቶ የሚያነሳ ፣ ቪድዮ የሚቀርፅ ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጅታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ/የቴክኖሎጂ ውጤት ፣ ስልክ ፣ አይ-ፓድ፣ታብሌት፣ኮምፒውተር፣ላፕቶፕ፣ስማርት ሰዓት ፣ ማጂክ ብዕር፣ማጂክ ጃኬት እና ሌሎች ማናቸውም ፎቶ፣ምስል እና ድምፅ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን በዩንቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ክልክል ነው።

በዩንቨርሲቲ ውስጥ ማንኛውም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ሃርድ ዲስክ፣ሲዲ፣ሚሞሪ ካርድ ፣ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ ቲጂ፣ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ክልክል ነው

ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣የፀጉር ጌጥ፣የጆሮ ጌጥ፣የጣት ቀለበት፣የእጅ አንባር አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት ክልክል ነው (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀር)

○ A.T.C

ተማሪ ነክ መረጃዎች ያግኙ
@NATIONALEXAMSRESULT
#ማሳሰቢያ

የማካካሻ ትምህርት ለመውሰድ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፦

እንጅባራ የካቲት 27 እና 28/2015 ዓ.ም ያደረገው የተማሪዎች ቅበላ 50% እና ከዚያ በላይ ላመጡ በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎች ብቻ ነው።

የማካካሻ ትምህርት ለመውሰድ የተመደባችሁ ተማሪዎች በአሁኑ ጥሪ ያልተካተታችሁ መሆኑን አውቃችሁ ወደ ፊት በማስታወቂያ እስከሚገለጽ ድረስ ባላችሁበት ሆናችሁ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ዩኒቨርሲቲው ያሳውቃል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ማሳሰቢያ

ለሁሉም የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት !
በ2015 ዓ.ም ከሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚመረቁ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና (Exite Exame) የሚሰጥ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ሁሉም የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመራቂ ተማሪዎቻችሁን መረጃ በተላከላችሁ የመረጃ መላኪያ ቅጽ መሠረት እስከ ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ለኢፊዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን እንድታቀርቡ እያሳሰብን እስከ ተጠቀሰው ቀን መረጃውን የማያቀርብ ተቋም ኃላፊነቱን የሚወስድ መሆኑን እንገልጻለን፡፡


የኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ማሳሰቢያ

ሁሉም የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመማር ላይ ያሉ ተማሪዎቻቸውን መረጃ እንዲያስገቡ የከፍተኛ ትምህርት ሥነ-ሥርዓት መመሪያ አንቀፅ 12 እና በመማር ላይ ያሉ ተማሪዎችን መረጃ እንዲልኩ ለሁሉም የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለማሳሰብ በቁጥር በደብዳቤ ቁጥር 11/7-1/594/15 እና በቀን 27/03/15 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ማሳሰባችን ይታወሳል፡፡ በተሰጠው ማሳሰቢያ መሠረት ከላይ #በምስሉ ስማቸው የተገለጸው የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መረጃውን የላኩ መሆኑን እየገለጽን ከባለስልጣኑ አገልግሎት የሚያገኙት እነዚህ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብቻ መሆናቸውን እንገልጻለን፡፡


የኢፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
Nifa silk.xlsx
558.6 KB
የ 2015 የ12 ክፍል ፈተና መፈተኛ ዩንቨርስቲዎች ምድባ

የሁሉም ክልሎች እንዲሁም ሁለቱ የከተማ መስተዳድሮች በውስጣቸው ባላቸው ወረዶች ተከፋፍለው ምደባው ተከናውኗል

አዲስ አበባ 2491-2502,2517-2526,2562-2620,2643-2662
ኦሮሚያ
621-1017,1029-1627,1818-1833,2252-2278,2503-2516,2527-2561,2662-2714,2730-2742
አማራ
45-311,326-380,401-620
አፋር5-44
ትግራይ 311-322
ሲዳማ 2743-2841
ቤ.ጉምዝ 385-400,1779-1816
ደቡብ 1834-2251
ጋምቤላ 2446-2502
ድሬዳዋ 2663-2671
ሀረሪ 1020-1026
ሱማሊያ 1628-1778,2715-2729
ከአገር ውጭ 2985-2987

#ማሳሰቢያ ከላይ ባለው ቁጥር መሠረት ወረዳቹን ስትፈልጉ (fx) ባለበት ተርታ ነው ሚጀመረው 5 አፋር ላይ ነው


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
#ማስታወቂያ!!

ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የመደበኛ ሁለተኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ተማሪዎች በሙሉ!!

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም ተማሪዎች ቅበላ ከመስከረም 21- 22/ 2016 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን ከወዲሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳዉቃለን።

Date of Online registration (Meskerem 19 - 22/2016 L.C) ባላችሁበት ሆናችሁ ከመስከረም 19 ጀምሮ መመዝገብ እንደምትችሉ እና ወደ ግቢ መግቢያ ከ21–22/01/2016 ዓ.ም. መሆኑን እያሳሰብን ትምህርት የሚጀምረዉ (DOCO) በ23/01/2016 ዓ.ም መሆኑንም ጭምር እናሳስባለን፡፡

#ማሳሰቢያ፡-

➢ ስትመጡ የስፖርት ትጥቅ አንሶላና የትራስ ጨርቅ ይዛችሁ እንድትመጡ፤

➢ ከተጠቀሰዉ ጊዜ ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪ ዩኒቨርሲቲዉ የማያስተናግድ መሆኑን፣

➢ የአንደኛ ዓመት ተማሪዎችን (ማለትም ከራመድያል ያለፉ፤ “ADR and Withidraw ያደረጉ እንዲሁም ድህረ-ምረቃ (MS MA/PHD ተማሪዎችን) በቀጣይ ማስታወቂያ የምንጠራችሁ መሆኑን እናሳስባለን።

ከወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት!

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
ለዲላ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ አመትና ከዚያ በላይ ያላችሁ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ!
................
የምዝገባ ቀን መስከረም 24 እና 25 ቀን 2016 ዓ.ም
ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን ዝርዝሩን ከዚህ በተያያዘው ማስታወቂያ ተመልከቱ።

#ማሳሰቢያ፦ ሁሉም የቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ተማሪዎች ምዝገባችሁ የሚከናወነው በሀሴዴላ ግቢ ስለሆነ ይህንኑ አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት በሀሴዴላ ግቢ ተገኝታችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን!

       ሬጅስትራርና አሉምናይ ጽ/ቤት

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot