TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዳማ⬆️

በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ "ሕገወጥ ነው" ያለውን አካባቢ ለማፍረስ በሄደበት ወቅት ከነዋሪዎች ጋር በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች #መቁሰላቸው ተገልጿል።

በተፈጠረው ችግር እጃቸው አለበት ያላቸውን ሰዎች ፖሊስ #በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል።

©voa amharic
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአማራ ክልል፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን፤ ደዋ ጨፋ ወረዳ በታጠቁ ሰዎችና በጸጥታ አካላት በተካሄደ ግጭት የሰው ሕይወት ማለፉ ተገለጸ። በኢንቨስትመንት የተያዘ መሬት በአግባቡ ልማት ላይ አልዋለም በሚል ቅሬታ ግጭቱ ነሐሴ 25 እና 26 ቀን 2010 ዓም መከሰቱን ነው የወረዳው ጸጥታ ኃላፊ የተናገሩት፤ በድርጊቱ ተሳታፊ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩ #በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

©ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

ከ40 በላይ የሚሆኑ የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ከፍተኛ አመራሮችና የደኅንነት አባላት #በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተጠቆመ፡፡

የሜቴክ ከፍተኛ አመራሮችና የደኅንነት አባላት ትናንትና ጥቅምት 30 ቀን 2011 ዓ.ም. ለስብሰባ ከተጠሩበት ስፍራ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የሪፖርተር ምንጮች ገልጸዋል፡፡

እንደ ምንጮቹ ገለጻ፣ ከፍተኛ አመራሩና የደኅንነት አባላት በቁጥጥር ሥር የዋሉት ገርጂ አካባቢ በሚገኘውና ቀድሞ ኢምፔሪያል ሆቴል ተብሎ ይጠራ በነበረውና አሁን የኮርፖሬሽኑ ንብረት በሆነው አሞራው ሕንፃ ውስጥ መሆኑ ተገልጿል፡፡

አመራሮቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉበት ምክንያት ባይነለጽም፣ የፌዴራል ፖሊስ ጌዜያዊ እስር ቤት በሆነው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ማቆያ ቤት መታሰራቸውን ምንጮቹ አክለዋል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሜቴክ‼️

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) አመራሮች በቁጥጥር ሥር እየዋሉ መሆናቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከ20 በላይ የሜቴክ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች ናቸው #በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ ያስታወቀው፡፡

ፖሊስ ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እንዳስታወቀው ሌሎች ተጠርጣሪዎችን የመያዙ ሥራም እንደቀጠለ ነው የተገለጸው፡፡ አመራሮቹ እና ሰራተኞቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉበት #ምክንያት በይፋ #አልተገለጸም፡፡

በጉዳዩ ላይ የፊታችን ሰኞ ፖሊስ ዝርዝር #መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጾልናል፡፡

ምንጭ፦ የአማራ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

የሜቴክ እና የኢንሳ ኃላፊዎች #በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰማ።
.
.
የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) እና የብሔራዊ መረጃ እና ደሕንነት (ኢንሳ) ኃላፊዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአማራ ብዙሀን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሶሳ🔝

በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ግጭት የተጠረጠረን  አንድ ግለሰብ #በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር #ሰይፈዲን_ሃሩን ዛሬ ለኢዜአ እንዳስታወቁት ፖሊስ ሰሞኑን በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በተከሰተው ግጭት ለሶስት ተማሪዎች ሞትና በሌሎችም ለደረሰው ጉዳት የጠረጠረውን አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር አውሏል፡፡

ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ከዋለ በኋላ “ታምሚያለሁ “ በሚል መድኃኒት ለመውሰድ በጸጥታ ሃይሎች ታጅቦ ወደ መኖሪያ ቤቱ ከሄደ በኋላ በመኖሪያ ቤቱ ያስቀመጠውን መሣሪያ በማቀባበል በጸጥታ ኃይሎች ላይ #ጥቃት ለመፈጸም ሙከራ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡

የግለሰቡ መኖሪያ ቤት ሲፈተሽ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎች መገኘታቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነር ሰይፈዲን የሚጠቀምበትን ኮምፒዩተር ጨምሮ የጸጥታ ሃይሎች ላይ ጥቃት ለማድረስ የሞከረበት ክለሽንኮብ መሣሪያም በቁጥጥር ሥር መዋሉን አስረድተዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው ግጭት በተጠረጠሩ ሌሎች ግለሰቦች ላይ ፖሊስ ምርመራውን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቀዋል፡፡

በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ባለፈው ማክሰኞ ተፈጥሮ በነበረው ግጭት የሶስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉና በሌሎች ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
ፎቶ፦ TIKVAH-ETH(AB)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳማ‼️

በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 10ሺህ 200 የአሜሪካን ዶላር  በአዳማ ከተማ  #በቁጥጥር ሥር  ማዋሉን የከተማው ፖሊስ መመምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ሳጅን ወርቅነሽ ገልሜቻ እንደገለጹት ዶላሩ በህገወጥ መንገድ በግለሰቦች ሲዘዋወር  ትናንት ማታ 3፡30 ላይ ሕብረተሰቡ ባደረገው ጥቆማ  ሊያዝ ችሏል።

ገንዘቡ የሰሌዳ ቁጥሩ 2-17781 (አ.አ) በሆነ የቤት አውቶሞቢል ተሽከርካሪ ተጭኖ ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ ከተማ በፍጥነት በመጓዝ ላይ እያለ በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ ልዩ ስሙ “ናማልድ” በተባለ አካባቢ በቁጥጥር ስር ውሏል።

ከመኪናው ጋር በተያዙ ሁለት ግለሰቦች ላይ በፖሊስ በኩል ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ሳጅን ወርቅነሽ አመልክተዋል።

ህገወጥ የገንዘብ ዝውውሩን በተቀናጀ መልኩ ለመከላከልና ለመቆጣጠር ህብረተሰቡ እያደረገ ያለውን ትብብር በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ምንጭ:- የኢትዮጵያን ዜና አገልግሎት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኮማንድ ፖስት‼️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝና በኦሮሚያ አጎራባች አካባቢዎች ተከስቶ በነበረው የጸጥታ መደፍረስ ችግር #የተጠረጠሩ 171 ሰዎች #በቁጥጥር ሥር ዋሉ።

በርካታ የጦር መሳሪያዎችና ገንዘብም በቁጥጥር ሥር እንዲውል መደረጉ ተመልክቷል፡፡

የአካባቢውን ሠላም ለመመለስ የተቋቋመው ኮማን ፖስት አባል እና በሀገር መከላከያ ሠራዊት የምዕራብ ዕዝ ኢንዶክትሪኔሽንና ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል #ጌትነት_አዳነ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ኮማንድ ፖስቱ ታህሳስ 11 ቀን 2011 ዓ.ም ከተቋቋመበት ጊዜ አንሰቶ ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ እየሰራ ነው።  

በእዚህም በክልሎቹ አጎራባች አካባቢዎች በታጠቀ ኃይል ተፈጥሮ በነበረ የጸጥታ መደፍረስ ጋር ተያይዞ በጠፋው የሰው ህይወትና በወደመው ንብረት የተጠረጠሩ 171 ሰዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስረድተዋል፡፡

ተጠርጣሪዎች የተያዙት ግጭት ከተከሰተባቸው ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሽ ዞን እና ቶንጎ ልዩ ወረዳ እንዲሁም ከኦሮሚያ ክልል ደግሞ ምዕራብ ፣ ምስራቅና ቄለም ወለጋ፣ ሆሩ ጉድሩ፣ ኢሉአባቦራ እና ቡኖ በደሌ ዞኖች መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል በየደረጃው የሚገኙ #አመራሮች እንደሚገኙበት ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡

የታጠቀው ኃይል ለግድያ እና ሌሎች #ጥፋቶች ሲጠቀምባቸው የነበሩ 49 ክላሽንኮብ ጠመንጃዎችና 1 ሺህ 31 የተለያዩ ጥይቶች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ኮሎኔል ጌትነት ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ግለሰቦቹ በህገ-ወጥ መንገድ ሲያንቀሳቀሱት የነበረ 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር እና 12 ሺህ ዶላር ኮማንድ ፖስቱ መያዙን ነው ያስረዱት።

እንደ ኮሎኔል ጌትነት ገለጻ የጥፋት ኃይሎቹ ተጨማሪ ጥቃት ለመፈጸም ያዘጋጁት ሰባት ጸረ-ተሸከርካሪ ፈንጂዎች፣ 215 ቀስቶች እና የተለያዩ ኮምፒዩተሮችም ተይዘዋል፡፡

ታጣቂ ኃይሉ ከመንግስት መዋቅሮች እና ከግለሰቦች አስገድዶ በመውሰድ ለጥፋት ሲጠቀምባቸው የነበሩ ዘጠኝ አምቡላንሶች፣ አራት አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪዎች፣ ሦስት ቶዮታ ፒክአፕ መኪኖችም ኮማንድ ፖስቱ ማስመለሱን ነው የገለጹት፡፡

ቡድኑ ለጥፋት ሲጠቀምባቸው የነበረውን ንብረት ከማስመለስ ጎን ለጎን በጉዳዩ ላይ ሕብረተሰቡን የማወያየት ሥራ በስፋት እየተካሄደ መሆኑን ኮሎኔል ጌትነት አስረድተዋል፡፡

የጸጥታ ችግር ሲከሰትባቸው በነበረባቸው ዞኖች በአሁኑ ወቅት ግጭት ሙሉ ለሙሉ ቆሞ ወደ ሠላማዊ እንቅስቃሴ መመለሱን ጠቅሰዋል፡፡

ህብረተሰቡ ያደረገው እገዛ ከፍተኛ መሆኑን ኮሎኔል ጌትነት ጠቁመው ኮማንድ ፖስቱ በቀጣይ ችግሩ እንዳይደገም አደረጃጀቱን ከህብረተሰቡ ጋር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል፡፡

በሁለቱ ክልሎች አጎራባች አካባቢ የደፈረሰውን ሠላም ለመመለስ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ከፌደራልና ከሁለቱ ክልሎች መንግስታት እንዲሁም ከሀገር መከላከያ እና ከፌደራል ፖሊስ ሠራዊት የተውጣጡ አባላትን ያቀፈ ነው፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvqhethiopia
ጄነራል ብርሃኑ ጁላ‼️

በምዕራብ ኦሮሚያ ከፍተኛ የፀጥታ ችግር መከሰቱን እና አሁን ግን #በቁጥጥር_ሥር እየዋለ መሆኑን የጦር ኃይሎች ምክትል ኤታማዦር ሹም አስታወቁ። ጀነራል #ብርሃኑ_ጁላ ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ በተጠቀሰው አካባቢ ተስፋ ሰንቆ ከውጭ የገቡ አካላትን የተቀበለው ሕዝብ መልሶ ለከፍተኛ ጉዳት መዳረጉን አመልክተዋል። አሁን እየተወሰደ ባለው #ጠንካራ_እርምጃ አማካኝትም የተዘጉ መንገዶች እና አደጋ ላይ የወደቁ የመንግሥት የመዋቅር ሥፍራዎች መከፈታቸውንም ዘርዝረዋል።

ከተማዎቹን እየዞሩ ያተራምሱ ነበር ያሏቸው አባ ቶርቤ በሚል መጠሪያ የሚታወቁ ኃይሎችም በመንግስት ቁጥጥር ሥር መግባታቸውንም ምክትል ኤታማዦር ሹሙ ገልጸዋል።

«አሁን #ትጥቅ_ማስፈታት ጀምረናል፤ እነዚያ የተዘጉ ከተሞች ነጻ አውጥተናቸዋል። የተዘጉ መንገዶች ተከፍተዋል፤ ሰዎች እንደተዘረፉ አውቃለሁ፤ ሸሽተው አዲስ አበባ የገቡ እንዳሉ አውቃለሁ፤ አባ ቶርቤ የሚባል በየከተማው እየዞረ ነፍስ የሚገድል ፤ የሚያስፈራራ ይሄን ለቅመነዋል።» ብለዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ከሰሞኑ በተከሰተው ወቅታዊ ሁኔታ መከላከያ ሰው አልገደለም ያሉት ጀነራሉ ክስተቱ #እንዲጣራ መወሰኑን፤ ድርጊቱ ተፈፅሞም ከሆነ መከላከያ ይቅርታ እንደሚጠይቅ #ካሳም እንደሚከፍል አመልክተዋል። ባለሥልጣኑ በተለያዩ አካባቢዎች ስለደረሰዉ ጉዳት ምንም አይነት አሃዛዊ መረጃ መስጠት እንደማይፈልጉ ገልፀዋል።

ምንጭ፦ DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

ሰባት ኪሎግራም ወርቅና ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ሃገራት ገንዘብ #መያዙን ገቢዎች ሚኒስቴር ገለፀ። አራት ተጠርጣሪዎችም #በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

የገቢዎች ሚኒስቴር #ቶጎ_ውጫሌ ኬላ ላይ ሰባት ኪሎ ግራም ወርቅና ከፍተኛ መጠን ያለው የውጪ አገር ገንዘብ መያዙን ገልጿል።

የአሜሪካ፣ የካናዳና የአውስትራሊያ ዶላር፣ ዩሮ፣ ድርሃምና የሌሎች ሃገራት ገንዘብ ነው የተያዘው ብሏል ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ።

ትናንት ምሽት ሰባት ኪሎ ግራም ወርቅና መጠኑ ከፍተኛ የሆነ የውጪ አገር ገንዘብ ከአራት ተጠርጣሪ ኮንትሮባንዲስቶች ጋር በቶጎ ዉጫሌ ኬላ በጉምሩክ ሰራተኞች ተይዟል።

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምስራቅ ጎጃም‼️

በምስራቅ ጎጃም ዞን #ነዳጅና #ሲሚንቶ ጭነው ይጓዙ የነበሩ ሁለት ተሽከርካሪዎች ተገልብጠው ንብረት መውደሙን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የህዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ ኢንስፔክተር #ጎበዜ_ይርሳው ለኢዜአ እንደተናገሩት አደጋው የደረሰው ከሱዳን አዲስ አበባ ነዳጅ ጭኖ በመጓዝ ላይ የነበረ ተሽከርካሪ ትናንት በመገልበጡ ነው፡፡

በአደጋው ቦቲው 47ሺህ 950 ሊትር ቤንዚን ጭኖ ከነተሽከርካሪው ሙሉ በሙሉ በእሳት መጋየቱን አስታውቀዋል፡፡

የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 7139 ተሳቢ 10704 ኢትዮጵያ የሆነ መኪና የመገልበጥ አደጋው የደረሰው በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ትግዳር ቀበሌ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሽከርካሪው #በቁጥጥር ሥር ውሎ  የአደጋው መንስዔ እየተጣራ መሆኑንም ኢንስፔክተር ጎበዜ አስረድተዋል።

በተመሳሳይ ከአዲስ አባባ ወደ ቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክ  ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 75260 ተሳቢ 18 029 ኢትዮጵያ የሆነ ተሽከርካሪ መኪና 400 ኩንታል ሲሚንቶ እንደጫነ በማቻከል ወረዳ በአማሬ ቀበሌ በመገልበጡ ጉዳት ደርሶበታል፡፡

የካቲት 6/2011 ከሌሊቱ ሰባት ስአት በደረሰው የመገልበጥ አደጋም በተሽከርካሪውና በተጫነው ሲሚንቶ   ምርት ጉዳት ደርሷል፡፡

አሽከርካሪውም የመቁሰል አደጋ ደርሶበት በደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል ብለዋል።

የሁለቱም ተሽከርካሪዎች አደጋ ምክንያት እየተጣራ መሆኑን የቡድን መሪው አስታውቀዋል። 

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ባለፈው ሳምንት በምዕራብ ጎንደር የታገቱ ሰዎች #መለቀቃቸውን የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ዘለዓለም ልጅዓለም በዛሬው ዕለት በባሕር ዳር ከተማ በሚገኘው ጽሕፈት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ታጋቾቹ መለቀቃቸውን አረጋግጠዋል። ኃላፊው «የታገቱ ሰዎች ነበሩ ሙሉ በሙሉ ተለቅቀዋል» ሲሉ አረጋግጠዋል።
ከጎንደር ወደ ገንዳውሐ በመጓዝ ላይ የነበሩ መንገደኞች በምዕራብ ጎንደር ዞን መቃ በተባለች አነስተኛ ከተማ የታገቱት ባለፈው የካቲት 12 ቀን፣ 2011 ዓ.ም. ነበር። የምዕራብ ጎንደር ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የሰላምና የሕዝብ ደኅንነት መምሪያ ኃላፊ አቶ ደሳለኝ ጣሰዉ «በአጠቃላይ የታገቱ ሰዎች ከሰባት እስከ ስምንት ሊሆኑ ይችላሉ» ብለው ነበር። የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዘለዓለም ልጅዓለም በዛሬው መግለጫቸው አጋቾቹን #በቁጥጥር ሥር ለማዋል ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል ማንዱራ ወረዳ በፀጥታ ችግር ቀያቸውን #ትተው የሄዱ ሰዎችን #ንብረት የፀጥታ አካላት ሲዘርፉ #በቁጥጥር_ሥር መዋላቸው ተሰምቷል።

ተጨማሪ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/BGU-07-10
TIKVAH-ETHIOPIA
ቅሬታ ! የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ደርሷቸው እንደሆነ ለማወቅ የሚጠባበቁ ነዋሪዎች የስም ዝርዝር ይፋ ባለመደረጉ ቅሬታ እንዳላቸው ገለፁ። የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት ዕጣ ዓርብ ቢወጣም እስካሁን የቤት ዕጣ የደረሳቸው ሰዎች ስም ዝርዝር በይፋ አልተገለፀም። ይህም የቤት ዕጣ ደርሷቸው እንደሆን ለማወቅ እየተጠባበቁ ባሉ ነዋሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል። የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት…
#ማብራሪያ የ20/80 እና 40/60 ጉዳይ 👆

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፦

" ... ከዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት በኋላ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ ስንጀምር በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች ተግኝተዋል።

በመሆኑም በእስካሁኑ የማጠራት ስራ ላልቆጠቡ ሰዎች እጣ መውጣትን ጨምሮ የተለያዩ የተዓማኒነት ጉድለቶች ታይተዋል፡፡

ከዚህ በመነሳትም የቤት ማስተላለፉን ሂደት ግልፅነት ለማስፈን ሲባል እና ውጤቱን የሚያዛባ ተግባር ሲያጋጥም መልሰን ኦዲት እንዲደረግ በገባነው ቃል መሰረት የተፈጠረውን ችግር ከጉዳዩ ገለልተኛ በሆኑ በሚመለከታቸው ተቋማት የማጣራት ስራ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በጉዳዩ የተጠረጠሩ ባለሙያዎች እና አመራር #በቁጥጥር_ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገ ይገኛል።

ስለሆነም ሂደቱን በአጭር ጊዜ አጠናቀን ለቤት ተመዝጋቢዎችና ለመላው የከተማችን ነዋሪ የምናሳውቅ መሆኑን ስንገለጽ ተመዝጋቢዎች እንደተለመደው በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡

ለተፈጠረው ስህተት የከተማ አስተዳደሩ በዚህ አጋጣሚ ይቅርታ ይጠይቃል። "

@tikvahethiopia