TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.82K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጄነራል ብርሃኑ ጁላ‼️

በምዕራብ ኦሮሚያ ከፍተኛ የፀጥታ ችግር መከሰቱን እና አሁን ግን #በቁጥጥር_ሥር እየዋለ መሆኑን የጦር ኃይሎች ምክትል ኤታማዦር ሹም አስታወቁ። ጀነራል #ብርሃኑ_ጁላ ዛሬ ከቀትር በኋላ አዲስ አበባ ላይ በሰጡት መግለጫ በተጠቀሰው አካባቢ ተስፋ ሰንቆ ከውጭ የገቡ አካላትን የተቀበለው ሕዝብ መልሶ ለከፍተኛ ጉዳት መዳረጉን አመልክተዋል። አሁን እየተወሰደ ባለው #ጠንካራ_እርምጃ አማካኝትም የተዘጉ መንገዶች እና አደጋ ላይ የወደቁ የመንግሥት የመዋቅር ሥፍራዎች መከፈታቸውንም ዘርዝረዋል።

ከተማዎቹን እየዞሩ ያተራምሱ ነበር ያሏቸው አባ ቶርቤ በሚል መጠሪያ የሚታወቁ ኃይሎችም በመንግስት ቁጥጥር ሥር መግባታቸውንም ምክትል ኤታማዦር ሹሙ ገልጸዋል።

«አሁን #ትጥቅ_ማስፈታት ጀምረናል፤ እነዚያ የተዘጉ ከተሞች ነጻ አውጥተናቸዋል። የተዘጉ መንገዶች ተከፍተዋል፤ ሰዎች እንደተዘረፉ አውቃለሁ፤ ሸሽተው አዲስ አበባ የገቡ እንዳሉ አውቃለሁ፤ አባ ቶርቤ የሚባል በየከተማው እየዞረ ነፍስ የሚገድል ፤ የሚያስፈራራ ይሄን ለቅመነዋል።» ብለዋል።

በምዕራብ ጎንደር ዞን ከሰሞኑ በተከሰተው ወቅታዊ ሁኔታ መከላከያ ሰው አልገደለም ያሉት ጀነራሉ ክስተቱ #እንዲጣራ መወሰኑን፤ ድርጊቱ ተፈፅሞም ከሆነ መከላከያ ይቅርታ እንደሚጠይቅ #ካሳም እንደሚከፍል አመልክተዋል። ባለሥልጣኑ በተለያዩ አካባቢዎች ስለደረሰዉ ጉዳት ምንም አይነት አሃዛዊ መረጃ መስጠት እንደማይፈልጉ ገልፀዋል።

ምንጭ፦ DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia