TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.8K photos
1.37K videos
198 files
3.65K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ምስራቅ ጎጃም‼️

በምስራቅ ጎጃም ዞን #ነዳጅና #ሲሚንቶ ጭነው ይጓዙ የነበሩ ሁለት ተሽከርካሪዎች ተገልብጠው ንብረት መውደሙን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የህዝብ ግንኙነት ቡድን መሪ ኢንስፔክተር #ጎበዜ_ይርሳው ለኢዜአ እንደተናገሩት አደጋው የደረሰው ከሱዳን አዲስ አበባ ነዳጅ ጭኖ በመጓዝ ላይ የነበረ ተሽከርካሪ ትናንት በመገልበጡ ነው፡፡

በአደጋው ቦቲው 47ሺህ 950 ሊትር ቤንዚን ጭኖ ከነተሽከርካሪው ሙሉ በሙሉ በእሳት መጋየቱን አስታውቀዋል፡፡

የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 7139 ተሳቢ 10704 ኢትዮጵያ የሆነ መኪና የመገልበጥ አደጋው የደረሰው በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ትግዳር ቀበሌ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አሽከርካሪው #በቁጥጥር ሥር ውሎ  የአደጋው መንስዔ እየተጣራ መሆኑንም ኢንስፔክተር ጎበዜ አስረድተዋል።

በተመሳሳይ ከአዲስ አባባ ወደ ቡሬ ኢንዱስትሪያል ፓርክ  ይጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 75260 ተሳቢ 18 029 ኢትዮጵያ የሆነ ተሽከርካሪ መኪና 400 ኩንታል ሲሚንቶ እንደጫነ በማቻከል ወረዳ በአማሬ ቀበሌ በመገልበጡ ጉዳት ደርሶበታል፡፡

የካቲት 6/2011 ከሌሊቱ ሰባት ስአት በደረሰው የመገልበጥ አደጋም በተሽከርካሪውና በተጫነው ሲሚንቶ   ምርት ጉዳት ደርሷል፡፡

አሽከርካሪውም የመቁሰል አደጋ ደርሶበት በደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት ይገኛል ብለዋል።

የሁለቱም ተሽከርካሪዎች አደጋ ምክንያት እየተጣራ መሆኑን የቡድን መሪው አስታውቀዋል። 

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert " ከዛሬ ጀምሮም ሲሚንቶ በየትኛውም ቦታ ቁጥጥር እና ክትትል ሳይደረግበት በነጻ ገበያ ይካሄዳል " - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሲሚንቶ በነጻ ገበያ እንዲሸጥ ተወሰነ። የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከዚህ በፊት የነበረው የሲሚንቶ ሽያጭ መመሪያ መቀየሩን ገለፀ። መመሪያው የሲሚንቶ ዋጋ በመንግሥት ተወስኖ እንዲሸጥ መደረጉ በርካታ ቅሬታዎች ሲነሳበት እንደነበር ገልጾ…
#ሲሚንቶ

ፋብሪካዎች ያቀረቡት የመሸጫ ዋጋና የተወሰነው መሸጫ ዋጋ !

👉 ዳንጎቴ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 549.49
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 811.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤795.93

👉 ደርባ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.59
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 779.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 761.55

👉 ሙገር

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 643.95
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 802.73
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 755.70

👉 ናሽናል

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል➤ 561.00
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 779.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 756.50

👉 ሀበሻ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 683.44
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 947.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 754.48

👉 PIONEER

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 510.04
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1783.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 753.95

👉 ኢትዮ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 595.66
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 973.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 753.60

👉 INCHINI

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 0
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1298.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤750.21

👉 KUYU

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 628.10
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤1019.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 752.50

👉 ኢስት

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 506.99
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1064.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤753.82

👉 ካፒታል

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 633.38
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 905.00
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤751.34

#አማካይ

- በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.3
- አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 1014.6
- የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 758.1

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሲሚንቶ ፋብሪካዎች ያቀረቡት የመሸጫ ዋጋና የተወሰነው መሸጫ ዋጋ ! 👉 ዳንጎቴ - በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 549.49 - አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 811.00 - የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤795.93 👉 ደርባ - በስራ ላይ ያለ የመሸጫ ዋጋ በኩ/ል ➤ 590.59 - አሁን ያስገቡት መሸጫ ዋጋ ➤ 779.00 - የተወሰነው የመሸጫ ዋጋ ➤ 761.55 👉 ሙገር - በስራ ላይ…
#ሲሚንቶ

የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በልሁ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ስለሆነው የሲሚንቶ ስርጭትና ግብይት መመሪያ ምንድነው ያሉት ?

አቶ ተሻለ በልሁ ፦

" ... አዲሱ መመሪያ አንደኛ የቀየረው ሲሚንቶ በገበያ ስርዓት ይመራ ነው። በገበያ የሚመራ ሲባል ምን ማለት ነው አከፋፋዮቻቸውን ፤ ቸርቻሪዎቻቸውን የመምረጥ ነፃነት #የፋብሪካዎች ነው። እስከዛሬ ማን ነበር የሚመርጥላቸው ? ሁለቱ ከተሞች እና ክልሎች ነበሩ። ስለዚህ ይሄ መመሪያ ከዛሬ ጀምሮ #የመንግስት_አካል አከፋፋይ እና ቸርቻሪ አይመርጥም።

ለተወሰነ ጊዜ ምርታማነት እስከሚጨምር በገበያ የሚፈለገውን ያህል መጠን ፋብሪካዎቻችን አምርተው ማሰራጨት እስከሚችሉ ድረስ የፋብሪካ የብር ዋጋ ብቻ በሚኒስቴሩ ይተመናል ይሄም በ6 ወር አንዴ ብቻ ነው እንደ አስፈላጊነቱ ፤ አላስፈላጊ ከሆነ ገበያው እራሱ የሚመራው ከሆነ የዋጋ ተመን አይኖርም።

ሌሎቹን ማን ይተምናቸዋል ? መመሪያው ያስቀመጠው የትራንስፖርት ዋጋን ፣የወራጅ እና አውጪ ዋጋን፣ ውስን ትርፍ ህዳግን መነሻ በማድረግ የፋብሪካ ብር መሸጫ ዋጋን እንደ ቤንች ማርክ ወስደው ፋብሪካዎቹ እያንዳንዳቸው ያሳውቃሉ። ስለዚህ መንግስት ከፋብሪካ ውጭ ያለውን ዋጋ አይተምንላቸውም የሚተምነው ማነው ? ፋብሪካዎች ናቸው ። "

@tikvahethiopia