TIKVAH-ETHIOPIA
1.43M subscribers
55.4K photos
1.39K videos
199 files
3.72K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢንጂነር ስመኘው በቀለ⬇️

ኢንጅነር #ስመኘው_በቀለ ራሳቸውን ማጥፋታቸውን የፖሊስ የምርመራ ውጤት እንደሚያሳይ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። ኢንጅነር ስመኘው ራሱን ካጠፋ በኃላ በወቅቱ ህይወቱ ሳትወጣ እያጣጣረ ፖሊሶች በቦታው መድረሳቸውንም ገልጸዋል፡፡

በፖስታው ውስጥ የተገኘው መልዕክት ስለ ቤተሰባቸው #አደራና ያለባቸውን #ጫና የሚገልፅ ፣ እንዲሁም ወደ ውጭ ለመውጣት ፍላጎት እንደነበራቸው ቢወጡም ለህዝቡ የሚሰጡት ምላሽ እንዳሳሰባቸው የሚገልጽ እንደነበረም ተናግረዋል፡፡

የሚሞቱበትን #ምክንያት ግን በፖስታው መልዕክት አሳማኝ ሆኖ #አለመጠቀሱን ፖሊስ ገልጿል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሜቴክ‼️

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) አመራሮች በቁጥጥር ሥር እየዋሉ መሆናቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከ20 በላይ የሜቴክ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች ናቸው #በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ፖሊስ ያስታወቀው፡፡

ፖሊስ ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እንዳስታወቀው ሌሎች ተጠርጣሪዎችን የመያዙ ሥራም እንደቀጠለ ነው የተገለጸው፡፡ አመራሮቹ እና ሰራተኞቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉበት #ምክንያት በይፋ #አልተገለጸም፡፡

በጉዳዩ ላይ የፊታችን ሰኞ ፖሊስ ዝርዝር #መግለጫ እንደሚሰጥ ገልጾልናል፡፡

ምንጭ፦ የአማራ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን ዳንሻ ከተማ አካባቢ ያረፈች የአየር ሀይል ሊኮፍተር በአካባቢው ወጣቶች ታግታ ነበር ወጣቶቹ ሂሊኮፍተሯ በአካባቢው ያረፈችበት #ምክንያት እንዲነገራቸው በመጠየቃቸው ነው ሂሊኮፍተሯ የታገተችው። ነገር ግን ከአካባቢው ባለስልጣናት ጋር ውይይት ከተደረገ በኅላ ሂሊኮፍተሯ በሰላም ተለቃለች።

ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ላይቭ ሀፕዴት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተክለብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን🔝

በአዲስ መልክ በመሰራት ላይ ባለው የኮተቤ ካራ የመንገድ ፕሮጀክት በግንባታ ላይ ያለ ድልድይ አርማታ እየተሞላ ባለበት ወቅት ድልድዩን ለመስራት የሚያግዝ መወጣጫ የካቲት 11 ቀን 2011 ዓ.ም በመደርመሱ በሰራተኞች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ ጉዳት እንዲደርስ #ምክንያት ሆኗል፡፡

የመንገድ ፕሮጀክቱ ስራ ተቋራጭ ተክለ ብርሀን አምባዬ ኮንስትራክሽን የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ የተሳተፉ አካላትን #ለማመስገን ባዘጋጀው ፕሮግራም በተጎጂዎቹ ላይ የሞትና ተጨማሪ ጉዳት እንዳይደርስ የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የፖሊስ አባላት፣ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች፣ የህክምና ባለሙያዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ አካላት ከፍተኛ ርብርብ በማድረጋቸው ከፍተኛ #ምስጋና አቅርቧል፡፡

በአደጋው በአንድም ሰው ላይ የሞት አደጋ እንዳልደረሰ እና የተጎዱ ሰራተኞች የህክምና እርዳታና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኙ ያሥታወቀው ስራ ተቋራጩ አደጋው ባጋጠመበት ወቅት የአካባቢው ነዋሪዎችና የተለያዩ አካላት አፋጣኝ ትብብር ማድረጋቸው የከፋ ችግር እንዳይፈጠር አስችሏል ብሏል፡፡

የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ #ሰይፉ_አምባዬ በአደጋው እና በደረሰው ጉዳት በጣም አዝነናል፤ የአደጋው ምንጭም በገለልተኛ አካል እየተጠና ይገኛል ብለዋል፡፡

በምስጋና ፕሮግራሙ ላይ የተገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም በቀጣይ ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳይደገሙ ስራ ተቋራጮች ቅድመ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሞገስ ጥበቡ በበኩላቸው የስራ ላይ አደጋዎች ባለስልጣኑን እንደሚያሳስበው ገልፀው መንገድ የምንገነባው ለህብረተሰቡ ልማትና ዕድገት በመሆኑ ስራዎች ሲከናወኑ የህብረተሰቡንና የሰራተኞችን ደህንነት ማዕከል አድርገው መሆን አለበት ብለዋል፡፡

ኢ/ር ሞገስ አክለውም የኮተቤ ካራ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ መጓተቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ የግንባታ ስራውን ማጠናቀቅ በሚቻልበት ዙሪያ ከስራ ተቋራጩ ጋር በልዩ ሁኔታ ተነጋግረን ስምምነት ላይ ደርሰናል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ኢ/ር ሞገስ በድልድዩ ስራ ያጋጠመው አደጋ መንስኤ ጥናት እንደተጠናቀቀ ለህብረተሰቡ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ገልፀው ጉዳት የደረሰባቸው ሰራተኞች ወደ ጤንነታቸው እንዲመለሱ አስፈላጊ የሚባለውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
(የካቲት 27/2011 ዓ.ም.)

#የሀዋሳ_ኢንዱስትሪ_ፓርክ ሠራተኞች ሥራ የማቆም አድማ መትተዋል። ሠራተኞች አድማ የመቱበት #ምክንያት በተደጋጋሚ ጊዜ አቅርበናል ያሉት #የደመወዝ ጥያቄ ምላሽ ባለማግኘቱ መሆኑን ተናግረዋል። ሠራተኞቹ #ደኅንነታቸው እንደማይጠበቅና ለፆታዊ ጥቃትና ለዝርፊያም እንደሚጋለጡ ገልፀዋል።

በኢንቨስትመንት ኮሚሽን የሃዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥራ አስኪያጅ አቶ #በላይ_ኃይለሚካኤል “ችግሩ የአንዳንድ ኩባንያዎችና የአስተዳደር በደል ነው” ብለዋል።

ምንጭ፦ VOA አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ለተማሪ ሞት እና ለግጭት #ምክንያት ናቸው ከተባሉት ውስጥ 10 ተጠርጣሪዎች እንደተያዙ ተገልጿል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የትምህርት ሚኒስቴር ለተወሰነ ጊዜ ትምህርት ተዘግቶ የዘማቾች ሰብል እንዲሰበሰብ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ከክልል የትምህርት ጽ/ቤቶች ጋር በመወያየት ውሳኔ በተሰጠባቸው ሀሳቦች ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ሀገሪቱ አሁን ያለችበት ሁኔታ የሁሉንም ዜጋ ኀላፊነት እና ትብበር የምትፈልግበት በመሆኑ ከህዳር 27 እስከ ታህሳስ 3 ቀን 2014 ዓ.ም የመማር ማስተማሩ ተግባር ለተወሰነ…
ትምህርት ሚኒስቴር ፦

በመላው ሀገሪቱ የሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለአንድ ሳምንት ይዘጋሉ።

ዝግ የሚሆኑት ከህዳር 27 እስከ ታህሳስ 3 ቀን 2014 ዓ/ም ድረስ ነው።

#ምክንያት ፦ መምህራን ፣ ተማሪዎች፣ ሰራተኞች ለሀገራዊ ትግል እንደየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ነው። ት/ቤቶች ዝግ ሆነው በሚቆዩባቸው ቀናት ያልተሰበሰቡ የዘመች ሰብል መሰብሰብ እና ቤተሰብን የመርዳት ዘመቻዎች በስፋት ይካሄዳል።

NB : ትምህርት ቤቶች ዝግ ሆነው በሚቆዩባቸው ቀናቶች በሙሉ ትምህርት ቤቶች በሚያወጡት የማካካሻ መርሀ ግብር መሰረት እንዲካካስ ይደረጋል።

መረጃውን ከትምህርት ሚኒስቴር ነው ያገኘነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሩስያ ሩስያ ላልተወሰነ ጊዜ ነዳጅ (ቤንዚን እና ናፍጣ) ወደ ውጭ መላክ አቆመች ፤ ይህ ተከትሎ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ላይ ተፅእኖ ይኖራል ተብሎ ተሰግቷል። ሩስያ ፤ " የሀገር ውስጥ ገበያን ለማረጋጋት እንዲሁም የሀገር ውስጥ የነዳጅ ፍላጎትን ለማሻሻል " በሚል ከአራት የቀድሞ የሶቪየት ሕብረት አባላት ውጭ ወደ #ሁሉም_ሀገራት የነዳጅ ምርቶችን ቤንዚን እና ናፍጣ መላክን ለጊዜው አግዳለች። እገዳው…
#የነዳጅ_ዋጋ !

በዓለም ገበያ 1 በርሜል ብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ3 ወራት በፊት 74 የአሜሪካ ዶላር የነበረ ሲሆን አሁን 94.8 የአሜሪካ ዶላር ገብቷል።

የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከቀን ወደ ቀን እያሻቀበ ይገኛል። ትላንት 97 ዶላር ደርሶም ነበር። ይህም እኤአ ከህዳር 2022 ወዲህ ከፍተኛው ጭማሪ ሆኖ ተመዝግቧል።

የዚህ ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ጭማሪ #ምክንያት የፍላጎት መጨመር እና የድፍድፍ ዘይት አቅርቦቶች በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነሱ ነው ተብሏል።

ለአቅርቦት መቀነሱና ለዋጋ ንረቱ ደግሞ የ " OPEC+ " አባላት የሆኑት ሳዑዲ አረቢያና ሩስያ ከዚህ ቀደም ያሳለፏቸው ውሳኔዎች ትልቁን ድርሻ ይይዛል ተብሏል።

በርካታ በዘርፉ ላይ ያሉ ተንታኞች ዋጋው በቅርብ ጊዜ ከ100 ዶላር በላይ ሊደርስ እንደሚችል እየገለፁ ናቸው።

@tikvahethiopia