TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ምስጋና የሀረሪ ክልል ነዋሪዎች ከጅግጅጋ ለተፈናቀሉ ወገኖች እያደረጋችሁ ላላችሁት ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ እና እያሳያችሁ ላላችሁት #ፍቅር ምስጋና ይገባችኋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢንጂነር ታከለ ኡማ⬇️

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጀነር ታከለ ኡማ #በጎርፍ አደጋው ተከትሎ ህዝቡና ተቋማት ላደረጉት ህይወት የመታደግ ርብርብ #ምስጋና አቀረቡ፡፡

በአቃቂ ክፍለከተማ የደረሰው የጎርፍ አደጋ እጅግ ከባድና አሳዛኝ ነው ያሉት ምክትል ከንቲባው ሆኖም ግን በክቡራን ወገኖቻችን ህይወት ላይ ምንም አይነት የህይወት አደጋ አለመድረሱ ለሁላችንም እፎይታ ነው ብለዋል፡፡

በዚህ አጋጣሚ ክቡሩን የወገንን ህይወት ለማትረፍ ርብርብ ላደረጉት የኢ.ፌ.ድ.ሪ የአየር ሀይል፤ የኢ.ፌ.ድ.ሪ መከላከያ ሰራዊት፤ ለአዲስ አበባ አሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መቆጣጠር ባለስልጣን፤ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮምሽንና ከምንም በላይ ደግሞ ለአከባቢው ነዋሪና ህብረተሰብ ያላቸውን ጥልቅ የሆነ አክብሮትና ልባዊ ምስጋና ያቀረቡት ኢንጀነር ታከለ እንደ አስተዳደር ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳይከሰቱ የጥንቃቄና የመፍትሄ እርምጃዎችን ጨምሮ የከተማውን የወንዝና ተፋሰስ ስራዎችን #በማልማት ከችግር ምንጭነት ይልቅ የከተማው የውበት ምንጭ እንዲሆኑ እንደሚሰራም ተናግረዋል።

ምንጭ፦ አዲስ አበባ መገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አርባ ምንጭ⬆️

የኦሮሞ #አባገዳዎች በአርባምንጭ አቀባበል ተደረገላቸዋል። የኦሮሞ አባገዳዎች የጋሞ ሽማግሌዎች ጸቡን ለማብረድ ላደረጉት ጥረት #ምስጋና ለማቅረብ አርባምንጭ ገብተዋል፡፡

የጋሞ ሽማግሌዎች ጸቡን ለማብረድ ላደረጉት ጥረት በኦሮሞ አባገዳዎች ምስጋና ቀርቦላቸዋል፡፡

እንግዶቻቸውን የተቀበሉት #የጋሞ ሽማግሌዎችም ጸብን በጸብ የመመለስ ባህል እንዳሌላቸው ገልጸዋል፡፡

በቡራዩ በተፈጸመው ጥቃት ዙሪያ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚያደረግ etv ዘግቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሬቻ2011

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ #ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኦሮሞ ህዝቦች እንኳን በፍቅርና #በአንድነት ለሚከበር የኢሬቻ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን ብለዋል፡፡

ኢሬቻ የገዳ ስርዓት አካልና የምስጋና የሰላም ቀን ነው፣ የኦሮሞ ምኞት ፍቅር፣ ብልጽግና፣ ባህሉ ደግሞ አብሮነት ነው፤ ኦሮሞ ለምለም ይዞ ለፈጣሪ #ምስጋና ያቀርባል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

የኦሮሞ ህዝብ የሚተዳደርበት #የገዳ ስርዓት ለዘመናዊ ዴሞክራሲ መሰረት የሆነና ታናሽ ታላቅን አክብሮ ከተላቅ የሚመር፣ ታላቅ ደግሞ ታናሽን በማብቃት ስርዓትን የሚያስቀጥል ስርዓት መሆንም ዶ/ር ዐቢይ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘንድሮን የኢሬቻ በትግል የተገኘውን ለውጥ የሚናስቀጥልበት፣ በፍቅር፣ በአንድነትና በእኩልነት አገር የሚንመራበትና የገዳ ልምዶችን የሚንቀስምበት ጊዜ በመሆኑ ደስታችንን ድርብ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

ዶ/ር ዐቢይ የዘንድሮ ኢሬቻ ባህላችንንና አንድነታችንን የምናጠናክርበት፣ የአባገዳዎች መልዕክት #የምንሰማበትና የምንተገብርበት ይሆናል የሚል ተስፋም አለን ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘንድሮ የኢሬቻ በዓል በፖለቲካ አለላካከት #ልዩነቶቻቸን ሳይገድቡን በፍቅርና በአንድነት አብሮ ለመስራት የሚንመራረቅበት እንደሚሆን ተስፋ እንዳላቸውም ገልጸዋል፡፡

አሸናፊ ሀሳብ በመያዝ አንድነታችንን አጠንክረን፣ ለሰላም፣ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር፣ ለፌዴራሊዝምና ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ አብረን መስራት አለብን ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

ሰላማችንን ማስጠበቅ በእጃችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሰላማችንንና ባህላቸን በመጠበቅና በማስጠበቅ አገርን መገንባት አለብን፤ በኢሬቻ በዓል ላይ ሰላማችንን በማስጠበቅ ለዓለም ምሳሌ መሆን አለብንም ብለዋል፡፡

ዘመኑ በፍቅርን አቅፈን ጥላቻን የምናሸንፍበት ዘመን እንዲሆንልን እመኛለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ቢሾፍቱ⬆️

#የኢሬቻ በዓልን ለማክበር ከጋሞ ብሔረሰብ የመጡ አባቶችና ወጣቶች #ቢሸፍቱ ደረሱ። #የኦሮሞ አባ ጋዳዎችም እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ተቀብለዋቸዋል። የኢሬቻ በዓል የክረምቱ ወራት አልፎ የበጋው ወራት በመጀመሩ ለአምላክ #ምስጋና የሚቀርብበት በዓል በመሆኑ የሁላችንም በዓል ነው እንኳንም የኛን በዓል #በዓላቸሁ አድርጋችሁ ለማክበር በመምጣታችሁ እናመሰግናለን ብለዋል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደብረ ማርቆስ ዩነቨርሲቲ‼️

ከኦሮሚያ ክልል የመጡ ተማሪዎች ለከተማው የሀይማኖት አባቶች፣ የንግዱ ማህበረሰብ፣ የሀገር ሽማግሌዎች ያላቸውን #ምስጋና በቻናላችን በኩል አቅርበዋል። ተማሪዎቹ ከደቂቃዎች በፊት ከንግዱ ማህበረሰብ ከተወከሉ የከተማው ነዋሪዎች ጋር ውይይት አድርገዋል።

🔹ከግቢው ተማሪ ጋር በስልክ በነበረኝ ቆይታ፦ የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ለግቢው ሰላም መደፍረስ እጃቸው ያለበትን ሰዎች እንዲለይ እና በውስጡ ያለውን ችግር እንዲያጠራ ጠይቀዋል። ችግር ፈጣሪው ሀይልም ተለይቶ እንዲታወቅና፤ አስተማማኝ ሰላም በግቢው እስኪሰፍን ድረስ ቢያንስ ለ2 ሳምንት ወደቤታቸው እንዲሸኛቸው እንደሚፈልጉ ገልፀዋል። ከዩኒቨርሲቲው ግን የተሰጠ ምላሽ እስካሁን የለም።

🔹በሌላ በኩል ከግቢው ማህበረሰብ ውጭ የሆኑ አንዳንድ አካላት ወደግቢው እንደሚገቡ መረጃው ያላቸው ተማሪዎች ይህን ጉዳይ ተቋሙ እንዲመረምር እና ስለታም ነገሮች እንዴት ግቢ ውስጥ ሊገቡ እንደቻሉ ሊፈትሽ ይገባል ሲሉ ገልፀውልኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
መልካም ተግባር🔝

#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ ላይ ተጠምደዋል።


#TIKVAH_ETH ~ የመከላከያ ሰራዊት እና የልዩ ሀይል አባልት እየሰራችሁ ላለው መልካም ስራ ታላቅ #ምስጋና ያቀርባል!

ፎቶ፦ ሚኪያስ (ጅግጅጋ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተክለብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን🔝

በአዲስ መልክ በመሰራት ላይ ባለው የኮተቤ ካራ የመንገድ ፕሮጀክት በግንባታ ላይ ያለ ድልድይ አርማታ እየተሞላ ባለበት ወቅት ድልድዩን ለመስራት የሚያግዝ መወጣጫ የካቲት 11 ቀን 2011 ዓ.ም በመደርመሱ በሰራተኞች ላይ ከቀላል እስከ ከባድ ጉዳት እንዲደርስ #ምክንያት ሆኗል፡፡

የመንገድ ፕሮጀክቱ ስራ ተቋራጭ ተክለ ብርሀን አምባዬ ኮንስትራክሽን የተጎጂዎችን ህይወት ለማትረፍ የተሳተፉ አካላትን #ለማመስገን ባዘጋጀው ፕሮግራም በተጎጂዎቹ ላይ የሞትና ተጨማሪ ጉዳት እንዳይደርስ የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የፖሊስ አባላት፣ የእሳትና ድንገተኛ አደጋ ሰራተኞች፣ የህክምና ባለሙያዎች እና ሌሎች የህብረተሰብ አካላት ከፍተኛ ርብርብ በማድረጋቸው ከፍተኛ #ምስጋና አቅርቧል፡፡

በአደጋው በአንድም ሰው ላይ የሞት አደጋ እንዳልደረሰ እና የተጎዱ ሰራተኞች የህክምና እርዳታና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኙ ያሥታወቀው ስራ ተቋራጩ አደጋው ባጋጠመበት ወቅት የአካባቢው ነዋሪዎችና የተለያዩ አካላት አፋጣኝ ትብብር ማድረጋቸው የከፋ ችግር እንዳይፈጠር አስችሏል ብሏል፡፡

የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ #ሰይፉ_አምባዬ በአደጋው እና በደረሰው ጉዳት በጣም አዝነናል፤ የአደጋው ምንጭም በገለልተኛ አካል እየተጠና ይገኛል ብለዋል፡፡

በምስጋና ፕሮግራሙ ላይ የተገኙ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም በቀጣይ ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳይደገሙ ስራ ተቋራጮች ቅድመ ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሞገስ ጥበቡ በበኩላቸው የስራ ላይ አደጋዎች ባለስልጣኑን እንደሚያሳስበው ገልፀው መንገድ የምንገነባው ለህብረተሰቡ ልማትና ዕድገት በመሆኑ ስራዎች ሲከናወኑ የህብረተሰቡንና የሰራተኞችን ደህንነት ማዕከል አድርገው መሆን አለበት ብለዋል፡፡

ኢ/ር ሞገስ አክለውም የኮተቤ ካራ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ መጓተቱ በአካባቢው ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ጫና እየፈጠረ በመሆኑ የግንባታ ስራውን ማጠናቀቅ በሚቻልበት ዙሪያ ከስራ ተቋራጩ ጋር በልዩ ሁኔታ ተነጋግረን ስምምነት ላይ ደርሰናል ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ኢ/ር ሞገስ በድልድዩ ስራ ያጋጠመው አደጋ መንስኤ ጥናት እንደተጠናቀቀ ለህብረተሰቡ ይፋ የሚደረግ መሆኑን ገልፀው ጉዳት የደረሰባቸው ሰራተኞች ወደ ጤንነታቸው እንዲመለሱ አስፈላጊ የሚባለውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል፡፡

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሽኝት ተደረገላቸው...

በሰሜን ተራሮች ፓርክ ተከስቶ የነበረውን እሳት #ለማጥፋት ለመጡት #የእስራኤል የእሳት አደጋ መከላከል ቡድን እና #ለኬንያዊው አብራሪ ሽኝት ተደረገ። ሽኝቱን የሰሜን ጎንደር ከአካባቢው ባለሀብቶች ጋር በመሆን ሲሆን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ወርቁ ለምለሙ ለእሳት መከላከል ቡድኑ ለአብራሪው እንዲሁም እሳቱን ለማጥፋት ለተረባረበው ህብረተሰብ #ምስጋና አቅርበዋል።

Via Debark wereda communication
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#በወንጀል_ይፈለጋሉ #Wanted የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከላይ በፎቶ የሚታዩትን ተጠርጣሪዎች በወንጀል እየፈለጋቸው ይገኛል። የተጠርጣሪዎቹን አድራሻቸውን የሚያውቅ አልያም በአጋጣሚ የተመለከተ ማንኛውም ገለሰብ በስልክ ቁጥር ፦ 👉 0115309139 ዘውትር (በስራ ሰዓት ከ2:30 - 11:30) 👉 በ0111119475 / 0111711012 በማንኛውም ሰዓት ደውሎ እንዲያሳውቅ ተጠይቋል። ነፃ የስልክ…
#ምስጋና🙏

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ለህብረተሰቡ ምስጋና አቅርቧል !

ተደራጅተው ከወርቅ መሸጫ ጌጣጌጦች የዘረፉ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከዚህ ቀደም በማህበራዊ ሚዲያዎች በተሰራጨ ቪድዮን ተከትሎ ተጠርጣሪዎች እንዲያዙ ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርቦ ነበር።

እንደ ፌዴራል ፖሊስ መረጃ በቡድን ተደራጅተው ዝርፊያውን የፈፀሙት ግለሰቦች በሞጆ ከተማ ሲሆን በቲክቶክ ላይ የአዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ የተባለው ስህተት እንደነበር ገልጿል።

ግለሰቦቹ ከወርቅ መሸጫው ሱቅ 49 ግራም የሚመዝኑ የወርቅ ጌጣጌጦችን ዘርፈው ከአካባቢው ተሰውረው የነበር ቢሆንም በህብረተሰቡ ጥቆማና በፖሊስ ብርቱ ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል።

የዘረፋ በድኑ አባላት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ህብረተሰቡ ላሳየው ትብብር እና ፈጣን ምላሽ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ምክትል ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ አበበ  ፥ " በቡድን ተደራጅተው በተለያየ ጊዜ የፖሊስን የደንብ ልብስ በመልበስ ዘረፋ የሚያካሄዱ ግለሰቦች እየተበራከቱ መጥተዋል " ያሉ " ይህ ተግባር የፀጥታ ኃይሉን ስም ለማጠልሸትና የጠላትን ዓላማ ለማሳካት ሆን ተብሎ የተፈፀመ ነው " ብለዋል።

ረዳት ኮሚሽነር ብርሃኑ ፤ ፖሊስ ከህዝብ አብራክ የወጣና የህዝብ አገልጋይ በመሆኑ ለደንብ ልብሱና ለዓላማው ልዩ ክብርና ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ መሆኑን ገልፀው የማዕረግ የደንብ ልብሱን ለብሶ ማንም ሰው ስሙን ማጠልሸትና ማጉደፍ እንደሌለበት አስገንዝበዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#TikvahFamily በትላንትናው ዕለት የ2ኛው ዙር የመማሪያ መፅሀፍትና ቁሳቁስ የማሰባሰብ ዘመቻ መካሄድ ጀምሯል። በመጀመሪያው ዙር በጥቂት ቀናት 7 ሺህ በላይ መፅሀፍትና 3 ዴስክቶፕ ኮምፒዩተር መሰብሰቡና በአማራ ክልልና በደቡብ ክልል ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች፣ በአዲስ አበባ ላለ የህዝብ ቤተመፅሀፍ መከፋፈሉ ይታወሳል። በዚህኛው ዙር በመፅሀፍት ደረጃ ከ30 ሺህ በላይ ለመሰብሰብ ታስቧል። በዚህ ዙር…
#ምስጋና

በቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ በኩል በየዓመቱ የመማሪያ መፅሀፍት ሲሰባሰብ 5 ዓመታትን ደፍኗል። (በኮቪድ ወረርሽኝ እና ጦርነት ምክንያት የተቋረጡትን አይጨምርም)

ባለፈው ክረምት ላይ በጀመረው 5ኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ (በአዲስ አበባ) መፅሀፍት ተሰብስበው ለት/ቤቶች ተሰጥቷል።

የዚሁ ቀጣይ የሆነ ሁለተኛ ዙር የማሰባሰብ ስራ ከቅዳሜ አንስቶ እየተካሄደ ነው።

ስራው ከመፅሀፍ ባለፈ የትምህርት መሳሪያዎችን ያካተተ ሲሆን ዘመቻው ከተጀመረ ወዲህ #ከየቤተሰቦቻችን መኖሪያ አካባቢ በመሄድ የተሰበሰቡ ፦

ትላንት ቅዳሜ ፦

- አቶ ዳንኤል ቦጋለ ከልጃቸው ነብዩ ዳንኤልና ከመላ ቤተሰባቸው ጋር መደበኛ መፅሀፍት 58 ፣ አጋዥ 2 ፣ የህፃናት 2 ፣ ልብወለደ 1 ፣ የግል ት/ቤት 11 መፅሀፍት አበርክተዋል።

- ወ/ሮ ኑሪያ አደም ከልጆቻቸው ሲያ አህመዝ ፣ ሀናን አህመድ፣ ረምላ አህመድ ከመላው ቤተሰባቸው ጋር 9 አጋዥ መፅሀፍት ፣ መዝገበ ቃላት 3 ፣ መደበኛ 19 መፅሀፍት እና አንድ ሞኒተር አበርክተዋል።

- ወ/ሮ ሰብለ ተሾመ ከልጆቻቸው በረከት ፍስሃ፣ በእምነት ፍስሃ፣ በፍቅር ፍስሃ ከመላው ቤተሰባቸው ጋር 38 መደበኛ መፅሀፍ 5 አጋዥ መፅሀፍ አበርክተዋል።

- አንድ የቤተሰባችን አባል ስሙን መግለፅ ያልፈለገ የ5 ሺህ ብር 106 መፅሀፍ ገዝቶ አስረክቧል።

- ዶ/ር አለማየሁ ሀብተገብርኤል ከልጆቻቸው ቤተልሄም ፣ መክሊት፣ ዳግማዊት እና በመላው ቤተሰባቸው ስም አንድ #ከለር_ፕሪንተር እና #ሞኒተር አበርክተዋል።

#ይቀጥላል
TIKVAH-ETHIOPIA
ዕግዱ ተነሳ። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በማህበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ጥሎት የነበረውን #ጊዜያዊ ዕግድ ዛሬ አርብ ማንሳቱን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#ምስጋና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ፈጣን ምላሽ ምስጋና አቅርባለች።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በማኅበረ
ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ፣ ግንቦት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. ያስተላለፈውን ጊዜያዊ እገዳ እንዲያነሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣  ለባለሥልጣን መ/ቤቱ ያቀረበችውን ጥያቄ በመቀበል፣ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የተጻፈለት ደብዳቤ እንደደረሰው ሳይውል ሳያድር ጊዜያዊ እገዳውን አንስቷል።

በዚህም ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያቀረበችውን ጥያቄ በአዎንታ ተመልክቶ አፋጣኝ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ፣ ከፍ ያለ ምስጋናን ማቅረቧን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፅ/ቤቱ ፤ " ለወደፊቱም ተቋማዊ ግንኙነታችንን የበለጠ በማጠናከር በጋራ ለመሥራት ዝግጁ መኾናችንን እንገልጻለን " ብሏል።

@tikvahethiopia
በሀገራችን አንዳንድ መልካም የስራ ስነምግባር የጎደላቸው ፣ ከአሸከርካሪዎች ጉቦ ካልተቀበሉ ቀኑ መሽቶ የማይነጋ የሚመስላቸው ፣ አንዳንዴም ሆን ብለው ምክንያት ፈልገው የቅጣት ወረቀት ለመፃፍ በኃላም #ጉቦ ለመቀበል የማይፈነቅሉት ድንጋይ የሌላቸው ፣ ፀሀዩ በረታብኝ ፥ ዝናቡም አካፍብኝ ብለው የሚጠለሉ የትራፊክ የፖሊስ አባላት እንዳሉት ሁሉ ፦
- ለስራቸው ታማኝ
- ህግን አክባሪ
- ቅን አገልጋይ
- ፀሀይ ፣ ዝናብ ሳይሉ ህዝብን አክብረው የሚሰሩ በርካታ የትራፊክ ፖሊስ አባላት አሉ።

ለእነዚህ አይነት ህዝብን አክብረው ምንም አይነት ሁኔታ ሳይገድባቸው ለሚሰሩ የትራፊክ ፖሊስ አባላት #ምስጋና ይገባል።

በሀገራችን ካሉ ከተሞች አንዷ በሆነችው የሰላም ተምሳሌቷ #ድሬዳዋ ❤️ የትራፊክ ፖሊስ አባላቶቿ በተለያየ ጊዜ በመልካም ስነምግባራቸው ስማቸው ተደጋግሞ ይነሳል።

ትላንትና በከተማው ከባድ ዘናብ ዘንቦ በነበረበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ እንዳይከሰት አንድ የትራፊክ ፖሊስ አባል በዝናብ ውስጥ ሆኖ ስራውን ሲያከናውን የሚያሳይ የተቀረጹ ቪድዮዎች እና ፎቶዎች ብዙዎች በማህበራዊ ሚዲያ ሲያጋሩት ውለዋል።

@tikvahethiopia