The Christian News
5.38K subscribers
3.07K photos
27 videos
725 links
ይህ The Christian News ነዉ። ከመላዉ አለም ተዓማኒነት ያላቸዉ የክርስትያን ዜናዎች ይቀርቡበታል ከወደዱት ይቀላቀሉት።

@TCNEW
Download Telegram
"በዉጪ #ሀገር ሆናችሁ የጥላቻን #ንግግር የምትዘሩ ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ አሳስባለሁ" ፖስተር ፃዲቁ አብዶ

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ፓስተር ጻዲቁ አብዶ ይህንን ያሉት በአዲስ አበባ እስታዲየም እየተካሄደ ባለው የአዲስ አመት #ልዩ ፕሮግራም #ላይ ነው።

ፓሰተር ጻዲቁ በመልዕክታቸው 2016 #ሰላም የምንሆንበት አንዳችን ሌላውን የምናንጽበት ፤ የምንገነባበት ለሌላው ውድቀት የማንሰራበት ፤ ወጥመድ የማንዘረጋበት ፤ ድልድይ የምንገነባበት ድልድይ የምንሰራበት #ዘመን እንዲሆንልን #እግዚአብሔር በሉዓላዊነቱ ይርዳን ብለዋል።

ሰላም ለማንም #ሰው እጅግ አስፈላጊ ነው ያሉት መጋቢ ጻዲቁ ከሰላም ውጪ የሚገኝ ምንም ነገር የለም ቢገኝም አይቆይም ስለዚህ ለሁላችንም ሰላም እንዲሆን እለምናለሁ።

እኛ ክርስቲያኖች እንደ አማኝ ሀገራችን ሰላም እንድትሆን እንጸልያለን ምንም #እንኳን እንድምንፈልገው ባይሆንም እግዚአብሔር በሚያውቀው በዘላለማዊ እውቀቱ #ወደ #መልካም ነገር እንደምናልፍ እናምናለን።

እኛ እንደ ሰው ድርሻ ሰላም የሚቀጥልበትን እና የምንተናነጽበትን እንፈልግ ፤ ጥላቻን ከመዝራት እንቆጠብ ፤ ጥላቻ ከልባችን ይወገድ ፤ የቂም በቀል ፍላጎት ከውስጣችን ይጥፋ።

በውጪ ሀገር ሆነው የጥላቻን አረፋ በማሕበራዊ ሚዲያ የሚደፍቁ ሰዎች #ስለ እግዚአብሔር ብለው ጥላቻቸውን ከመዝራት እንዲቆጠቡ በዚህ አጋጣሚ በዚህ ጉባኤ በይፋ መልዕክት አስተላልፋለሁ ብለዋል።

Photo 📷 Hossana Photo & Video Production