ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
853 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
#ኦርቶዶክስ_መልስ_አላት
#ክፍል_3
#የይሖዋ_ምስክሮች /ጆቫ ዊትነስ/ *
የይሖዋ ምስክሮች የተባለው የሃይማኖት ተቋም በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በቻርልስ ራስል የተመሰረተ ሲሆን ራስል ቀደም ባሉት ጊዜያት ክርስቲያን የነበረ ሲሆን በኀለኛው የወጣትነት ዘመኑ በአርዮሳውያን የኑፉቄ ትምህርትና በሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት እንዲሁም በአንዳንድ የክህደት ትምህርት (Atheists) አራማጆች ተፅዕኖ ስር ወደቀ ። እ.ኤ.አ በ1872 አካባቢ ከነዚህ የተበረዙና የተዛቡ አስተምህሮዎች በመነሳት ራስል የራሱን አስተምህሮ (Doctrine) በመቅረፅ በአሜሪካ ውስጥ ለማሳተም ቻለ ።እስቲ ጥቂት እምነታቸውን እንመልከት #1ኛ .ጆቫዎች ቤተክርስቲያንና የአለም መንግስታት ሁሉ የሰይጣን ስራ ውጤቶች ናቸው ብለው ያምናሉ #2ኛ.ዜጎች በወታደራዊ ተቋማት እንዳይገቡ ያደርጋሉ ። ለሰንደቅ አላማ የክብር ሰላምታ መስጠትን እንደ ባዕድ አምልኮ አድርገው ይቆጥሩታል #3ኛ. የሰው ነብስ ትሞታለች ብለው ያምናሉ #4ኛ.የሰው ልጅ ከትንሳኤ ቡሃላ ገነት በምትሆነው ምድር ለዘላለም ይኖራል /ምድር ገነት ትሆናለች/ ብለው ያምናሉ #5ኛ.የይሖዋ ምስክሮች ክርስቶስን ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ ሳይሆን መለኮታዊ ባህሪ ያለው ንዑስ አምላክ ነው ብለው ያምናሉ #6ኛ.የይሖዋ ምስክሮች ሰብአ ሰገል በቤተልሔም በጌታችን ፊት ያደረጉት ስግደት የማይገባና የመራቸውም ኮከብ ከሰይጣን የተላከ እንደሆነ ያምናሉ ። #7ኛ.ጆቫዎች ክርስቶስ አስቀድሞ በሰማይ ከተፈጠረ በኀላ በዚያው ኗሯል ፡ ወደ ምድር እንዲመጣ ያስፈለገበት ዋነኛ ዓላማም ስለ ይሖዋ መንግስት ለመመስከር ነው ይላሉ ። #8ኛ.የይሖዋ ምስክሮች የዳግም ልደቱ መጀመሪያ በሚሆነው ጥምቀቱ ለእግዚአብሔር ልጅነት የተሾመ ነው በዚህም የአብ መንፈሳዊ ልጅ በመሆን የይሖዋ መንግስት ገዢ /ንጉስ/ ሆኗል ብለው ያምናሉ ። #9ኛ.የይሖዋ ምስክሮች ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ መላዕክት ሚካኤል ነው ብለውም ያምናሉ ። #10ኛ.የይሖዋ ምስክሮች የሰው ልጅ በስጋ ሲሞት ነፍሱም አብራ ትሞታለች። ዘላለማዊነት የይሖዋ ብቻ የተለየ ባህሪ ነው ብለው ያምናሉ ። #11ኛ. የይሖዋ ምስክሮች ኃጢያተኞች ከፃድቃን ተለይተው እንደሚጠፉ እንጂ በሲኦል የሚሰቃዩ መሆናቸውን አይቀበሉም ። ሌላው ቀርቶ ሰይጣን ይጠፉል እንጂ አይሰቃይም አባታችን አዳምም አንዴ ስለሞተ ትንሳኤ አያገኝም ይላሉ ። #12ኛ .መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ አንዱ አካል ሳይሆን የይሖዋ ሀይል ነው ብለው ያምናሉ ። #13ኛ. በብዙ ትንሳኤ ያምናሉ ።ማለትም የታናሽ መንጋ ትንሳኤ ፣ምድራዊ ትንሳኤ ፣ የይሖዋ ምስክሮች አባል ላልሆኑትና ፃድቅ ለሆኑት የሚደረግ ትንሳኤ ብለው ትንሳኤን ከፉፍለው ያምናሉ። ወስብሀት ለእግዚአብሔር ።የአብ ፀጋ ፡ የወልድ ቸርነት የመንፈስቅዱስ ህብረት አንድነት ከኛ ጋር ይሁን ለዘለአለሙ አሜን
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#በመንፈሳዊ ሕይወትህ ለውጥ እንዲኖሮት ከፈለጉ


1ኛ የፀሎትን ህይወት ተለማመድ ተጠቀምበትም፣
#2ኛ ከመንፈሳዊ አባቶችና ሊቃውንት መ/ራን ምክርና ትምህርት አትራቅ
#3ኛ ከቅዱሳት መፃህፍት ጋር ያለህን ግንኙነት አዘውትር፣
#4ኛ የምትውልባቸውን ቦታዎች ፥የምታነባቸውን
መፃህፍት፥የምትመርጣቸውን ባልጀሮችህን ምረጥ፤ለመንፈሳዊ ህይወትህና ለሌሎች ወንድሞችህና እህቶችህ የሚያሰናክሉ እንዳይሆኑ ተጠንቀቅ፣

#5ኛ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ መሆንህን ዘወትር አትዘንጋ፣
#6ኛ አግባብ ያልሆነ ሃፍረትንና ፍርሃትን አስወግድ፥በራስህ ማስተዋልም
አትደገፍ፣
#7ኛ አላዋቂነትህን ተቀበል 'እኔ ብቻ' አትበል ውዳሴ ከንቱንም
አትፈልግ፣
#8ኛ ለሰራሃው ሃጢአት ሳትዘገይ ንስሃ ግባ፣
#9ኛ ልበ ደንዳናነትንና አመፀኛነትን ከአንተ አርቃቸው፣
#10ኛ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመኖርና የቃሉ ሙላት
በውስጥህ ኖሮ ከክርስቶስ ጋር መኖርን ተለማመድ በቃሉም
ፀንተህ ተገኝ፣
#11ኛ የቅዱሳንን ተጋድሎና ፍቅር በመመልከት እነርሱን
ለመምሰል ትጋ፣

#12ኛ ከዚህ በፊት የነበርክበትን የሃጢአት ህይወት ኮንነው
#13ኛ ሰዎችን/ባልንጀራህን አፍቅር ከጥላቻም ራቅ፣
#14ኛ ነገርን ሁሉ ለበጎነው ብለህ ተቀበል። ጌታ ሆይ ይህን
እንድናደርግ እርዳን አሜን
ይቆየን::
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_6
#12ቱ_የፍቅር_አይነቶች
እንደሚታወቀው ባለፉት ክፍሎቻችን ከ12ቱ 9ኙን ማየታችን ይታወሳል ። እነሆ ዛሬ ደሞ የቀሩትን 3ቱን እናያለን ።
#10ኛ_ሰልፊሽ_ላቭ (Selfish Love) ፦ ይሄኛው "ራስ ወዳድ ፍቅር " ይባላል ። እነዚህኞቹ ደግሞ ፍቅርን የሚጀምሩት የሚፈልጉትን ነገር ለማግኘት ሲሉ ብቻ ነው ። ለምሳሌ ገንዘብ ቸግሯቸው ከሆነ ገንዘብ ለማግኘት ፣ ሌላም ችግር ካለባቸው የገጠማቸውን ክፍተት ለመድፈን ሲሉ የሚጀምሩት የፍቅር አይነት ነው ። ይህ ፍቅር እራስን ከመውደድ የመነጨ ፍቅር አይደለም ። በውስጡ እውነተኛ ስሜትም ቅርበትም የለውም ።እነዚህ ሰዎች የሚፈልጉትን ካላገኙ ደግሞ ግንኙነቱን ለማቋረጥ ዐይናቸውን አያሹም
#11ኛ_ኮምፒኒየን_ላቭ (Companion Love ) ፦ ብዙ ጊዜ በዚህኛው ፍቅር ውስጥ የሚገቡ ሰዎች እድሜያቸው ከትዳር ክልል ውጭ ወጣ ያለባቸው ሰዎች ናቸው ። እንዲህ አይነት ሰዎች በአብዛኛው ብቻቸውን በነበሩበት ዘመን የሌሎችን የትዳር ሕይወት እየተመለከቱ መቅናት ይጀምራሉ ። እናም ብዙ ነገር ያምራቸዋል ። በዚህ አምሮታቸው ውስጥ ትዳርን ይናፍቃሉ ። ታዲያ እነዚህ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ከእድሜያቸው ጋር እሩጫ ስለሚይዙ ሲያገቡ ለእነሱ የሚሆናቸውን መርጠው ፣ ባህርይን አጥንተው ፣ እረጋ ብለው አይደለም የሚያገቡት ። ያገኙትን አጋጣሚ ተጠቅመው ብቻ ያገባሉ ። ምክንያቱም እነርሱ አሁን ፊታቸው ያለውን የትዳር አምሮት ፣ ልጅ ማሳደግ ፣ አብሮ መኖር ... ይሄ ብቻ ነው የሚታያቸው
#12ኛ_ኮንሲዮሜት_ላቭ (Consummate Love ) ፦ እውነተኛ ፍቅር ! ይህ እውነተኛ ፍቅር ነው ወይንም ደግሞ ዘለቄታው ያማረና የተስተካከለ ነው የሚያሰኘው #በ3 ነገሮች ላይ ሲዋቀር ነው ። እነሱም ቅርበት (Intimacy) ፣ ስሜት (Passion) ፣ ቁርጠኝነት (Commitment) ። በእነዚህ 3 ነገሮች ላይ የተዋቀረ ፍቅር አስተማማኝ፣ እውነተኛና ሕይወት ያለው የማይሞት ፍቅር ነው ። በዚህ ዓይነት ፍቅር ውስጥ ያሉ ሰዎች መሰለቻቸት የሚባል ነገር አያውቃቸውም ። ፍቅራቸው ልዩና ጣዕም ያለው ፍቅር ነው ። በመካከላቸው #ስሜት አለ ። በስሜት ይጣጣማሉ ፣ ይግባባሉ ፣ በዚህም ተደስተው ይኖራሉ ። #ቁረጠኝነትም አለ ። እርሷ ከእርሱ ጋር እርሱም ከእርሷ ጋር አብሮ ለመኖር ቁርጠኞች ናቸው ። ይሄም ወደ ትዳር የሚያመራ ጥሩ መንገድ ነው ። በመቀጠልም #ቅርበት በመካከላቸው አለ ። ጥልቅ መቀራረብ በእነሱ መካከል ከመኖሩ የተነሳ ባህርይ ለባህርይ በደንብ ይተዋወቃሉ ። ከመተዋወቃቸውም የተነሳ በጣም ይዋደዳሉ ።ብዙ ጊዜ የባህርይ ለባህርይ መተዋወቅና በባህሪም የሚመሳሰሉ ባልና ሚስቶች በትዳራቸው ደስተኛም የሚሆኑት ከዚህ የተነሳ ነው ። #በ3ቱ ነገሮች ላይ የተዋቀረ ፍቅር ቀስ እያለ እስከመጨረሻው የሚያድግ እንጂ የሚከስም አይደለም ። በመከራ ሰዓትም ቢሆንም እንኳን አይበገርም።ፍፁም ቅርበት ስላላቸው አይለያዩም። ምንም ነገር ቢፈጠር እንኳን መከራ አራርቋቸው ከዓላማቸው ፈቀቅ አያደርጋቸውም ። ይሄኛው የፍቅር አይነት በጣም ጥሩ እና እውነተኛ ፍቅር ነው ። በዚህ ዓይነቱ የተያዘ በእውነተኛ ፍቅር እንደተያዘ እርግጠኛ መሆን ይችላል። 12ቱን የፍቅር አይነቶች ጨርሰናል ቀጣይ ደሞ #ቃልኪዳንን እናያለን ።

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ፍኖተ_ቅዱሳን
#የመጨረሻው_ክፍል
... ከባለፈው የቀጠለ ...
ከላይ ሁለቱን ደረጃዎች ተመልክተናል ። ወጣኒነትና ማዕከላዊነትን። አሁን ደግሞ የመጨረሻውን ደረጃ ፍፁምነትን እንመልከት ። ይህ የመጨረሻ ደረጃ እንደ መሆኑ መጠን በ2ቱ ደረጃዎች ሰባቱን መዓርጋት ገንዘብ አድርገው ወደዚህ ለመሸጋገር የሚጋደሉትን ሰይጣን በገሃድ ተገልጦ መዋጋት የሚጀምርበት ጊዜ ነው ።ዘንዶና እባብ ፣ አንበሳና ነብር እየሆነ በመምጣት ለማስፈራራት ቢሞክር ያልደነገጡለትን ሽፍታ እየመሰለ መደብደብ ሁሉ ይጀምራል ። መዝ 90 እና መሰል ፀሎትን በመፀለይ ድል ይነሱታል ።መደ ሚቀጥሉት ማዕረጋትም ይሻገራሉ ።
#8ኛ #ንፃሬ_መላዕክት ፦ እዚ ደረጃ ሲደርሱ እነሱን የሚረዷቸውን መላዕክት በየነገዳቸውና በየአለቆቻቸው በሚኖሩባቸው ዓለማተ መላዕክት (በኢዮር ፣ በኤረር ፣ በራማ ) እንዳሉ በዓይነ ስጋ በዐፀደ ስጋ ለመመልከት መብቃት ፣ ምስጋናቸውንም መስማትና ከዚህ ዓለም ፈፅሞ ተለይቶ ከሰማያውያን ጋር መኖርን መጀመር ነው ።
#9ኛ #ተሰጥሞ_ብርሃን ፦ ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር የባሕሪ ገንዘብ በሆነው በሚያስደንቀው ብርሃን ውስጥ መዋኘት ነው ። ይህ ብርሃን ፍፁም ልዩ ነው ።ይህም እነርሱ በዛ ብርሃን ውስጥ እያሉ ሌላ ለዚህ ማዕረግ ያልበቃ ሊያየው የማይችል ብርሃን ነው ።ጨለማ የማይሰለጥንበት ፣ እንደዚህ ዓለም ብርሃን የማያቃጥል ፣ በጨረሩ አይንን የማይበዘብዝ ፣ ነፍስን ከስጋ መለየት የሚያስችል ደስታ እስኪሰማ ድረስ ልዩ መዓዛ ያለው ነው ። እነዚህን ፀጋዎች የሚያውቁት የኖሩባቸው ቅዱሳን ናቸው ። እኛ ደሞ ከመፃህፍት ብቻ እንረዳቸዋለን ።
#10ኛ #ከዊነ_እሳት (ነፅሮተ ስሉስ ቅዱስ) ፦ ይህ የመጨረሻው ማዕረግ ነው ። ወደዚ ደረጃ የደረሱ ቅዱሳን ሰውነታቸው ለአጋንንት የሚያቃጥልና የማያስቀርብ ይሆናል ።እነዚህን አጠቃለው የያዙ የልብ ንፅህናን ገንዘብ አድርገዋልና ለነጽሮተ ስሉስ ቅዱስ ይበቃሉ ።ለዚህ መብቃትም ታላቅ ብቃትና ማዕረግ ነው ። በባሕሪው የማይታየውን እግዚአብሔርን ለባሕሪያቸው በሚስማማ መልኩ እስከ ማየት በቅተዋልና።
❖ ተፈፀመ ❖

👉ለመቀላቀል 👇👇👇 @zekidanemeheret @zekidanemeheret @zekidanemeheret