ስንክሳር ወግጻዌ ዘተዋሕዶ
853 subscribers
3.46K photos
103 videos
194 files
1.2K links
የየዕለቱ ስንክሳር እና ግጻዌ የሚቀርብበት ቻናል ነው፡፡

ለማንኛውም አስተያየት እና እርማት
@zetaodokos ላይ ይላኩልን።

👇👇የYoutube Channel ይቀላቀሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCupqpIYe_mMpSM7jMT3Njhw
Download Telegram
#ኦርቶዶክስ_መልስ_አላት
#ክፍል_2
#ፕሮቴስታንት /ጴንጤ /
ፕሮቴስታንት ተቃዋሚ ከሚለው የእንግሊዘኛ ቃል የተወሰደ ነው ። ይህም ሊሆን የቻለው የካቶሊክ ፓፓ የነበረው አቡነ ሊዎ አስረኛ የቅ/ጴጥሮስን ትልቅ ቤተክርስቲያን ለማሰራት በማሰቡ መንግስተ ሰማያት መግቢያ ብሎ ካርድ መሸጥ ጀመረ ። ማርቲን ሉተር ግን መንግስተ ሰማያት በክርስቶስ እንጂ በካርድ አይገባም ብሎ ተነሳ ።ይባስ ብሎም 90 ነጥቦችን ነቅሶ አውጥቶ ለጠፈላቸው ። ተቃዋሚ ሲሉትም ፕሮቴስት አሉት እሱን የተከተሉትን ደግሞ ፕሮቴስታንት አሏቸው ። አሁን ደሞ እስቲ ልዩነታችንን እንያቸው #1ኛ.ፕሮቴስታንት የንስሀ አባት አያስፈልግም ይላሉ ። ኦርቶዶክስ ግን ከ7ቱ ሚስጥራተ ቤተክርስቲያን አንዱ በመሆኑ ከታላቅ አክብሮት ጋር ትገለገልበታለች ። ጌታችን በወንጌል "ኃጢያቱን የተዋቹለት ቀረችለት ፡ "የያዛችሁበትም ተያዘችበት " በማለት አስተምሯልና ። (ዮሀ 20:23 ማቴ 16:19)። ደሞ በፕሮቴስታንት ሴቶች ስልጣነ ክህነት ሊኖራቸው ይችላል ። በኦርቶዶክስ ግን አይቻልም ። ጌታ የመረጣቸውና ስልጣነ ክህነትን የሰጣቸው ለወንዶች እንጂ ለሴቶች አይደለም ። #2ኛ. ፕሮቴስታንቶች የእምነት መሰረቱ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው ይላሉ ። ይህም ማለት በቤተክርስቲያን ሊቃውንት መፃህፍትና ሲወርድ በመጣው ቤተክርስቲያናዊ ትውፊትና አዋልድ መፃህፍት ላይ እምነት የላቸውም #3ኛ.ፕሮቴስታንቶች የቅዱሳን አማላጅነት አያስፈልግም ይላሉ ። ኦርቶዶክስ ግን ቅዱሳንን በተሰጣቸው ቃልኪዳን መሰረት ያማልዳሉ ብላ ታምናለች ። #4ኛ.ፕሮቴስታንቶች ጥምቀት እግዚአብሔርን ለማምለክ ምልክት እንጂ ድኀነት አያስገኝም ይላሉ ። በኦርቶዶክስ ግን በክርስቲያናዊ ህይወት የመጀመሪያ መግቢያ በር በመሆኑ ወደ ቤተክርስቲያን ለመግባትና ሚስጥራትን ለመካፈል አስፈላጊ መሆኑን ታምናለች #5ኛ.ፕሮቴስታንቶች ቁርባን መታሰቢያ እንጂ የክርስቶስ ሥጋና ደም አይደለም ይላሉ ።ኦርቶዶክስ ግን መለኮት የተዋሀደው ነብስ የተለየው ቁርባን አማናዊ የክርስቶስ ሥጋና ደም ነው ትላለች #6ኛ.ፕሮቴስታንቶች ለመዳን ማመን ብቻ በቂ ነው ስራ አያስፈልግም ይላሉ ።ኦርቶዶክስ ግን እምነትና ምግባርን ነጣጥላ አትመለከትም ። ስራ የሌለው እምነት ነብስ የተለየው ስጋ ነው የሞተ ነው ትላለች ። #7ኛ.ፕሮቴስታንቶች መፅሀፍ ቅዱስን ሁሉም በሚገባው መልኩ መተርጎም ይችላል ይላሉ ። ኦርቶዶክስ ግን ማንም እንደፈለገውና እንደመሰለው እንዲተረጉም አትፈቅድም ።ወስብሀት ለእግዚአብሔር ። የአባቶቻችን የተባረከች በረከታቸው ፡ ርትዕት ሀይማኖታቸው ፡ ጥርጥር የሌላት ድል የማትነሳ እምነታቸው ከኛ ትሁን ለዘለአለሙ አሜን ።

ምንጭ= ኰኲሕ ሐይማኖት
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክስ_መልስ_አላት
#ክፍል_3
#የይሖዋ_ምስክሮች /ጆቫ ዊትነስ/ *
የይሖዋ ምስክሮች የተባለው የሃይማኖት ተቋም በ19ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ በቻርልስ ራስል የተመሰረተ ሲሆን ራስል ቀደም ባሉት ጊዜያት ክርስቲያን የነበረ ሲሆን በኀለኛው የወጣትነት ዘመኑ በአርዮሳውያን የኑፉቄ ትምህርትና በሰባተኛው ቀን አድቬንቲስት እንዲሁም በአንዳንድ የክህደት ትምህርት (Atheists) አራማጆች ተፅዕኖ ስር ወደቀ ። እ.ኤ.አ በ1872 አካባቢ ከነዚህ የተበረዙና የተዛቡ አስተምህሮዎች በመነሳት ራስል የራሱን አስተምህሮ (Doctrine) በመቅረፅ በአሜሪካ ውስጥ ለማሳተም ቻለ ።እስቲ ጥቂት እምነታቸውን እንመልከት #1ኛ .ጆቫዎች ቤተክርስቲያንና የአለም መንግስታት ሁሉ የሰይጣን ስራ ውጤቶች ናቸው ብለው ያምናሉ #2ኛ.ዜጎች በወታደራዊ ተቋማት እንዳይገቡ ያደርጋሉ ። ለሰንደቅ አላማ የክብር ሰላምታ መስጠትን እንደ ባዕድ አምልኮ አድርገው ይቆጥሩታል #3ኛ. የሰው ነብስ ትሞታለች ብለው ያምናሉ #4ኛ.የሰው ልጅ ከትንሳኤ ቡሃላ ገነት በምትሆነው ምድር ለዘላለም ይኖራል /ምድር ገነት ትሆናለች/ ብለው ያምናሉ #5ኛ.የይሖዋ ምስክሮች ክርስቶስን ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ ሳይሆን መለኮታዊ ባህሪ ያለው ንዑስ አምላክ ነው ብለው ያምናሉ #6ኛ.የይሖዋ ምስክሮች ሰብአ ሰገል በቤተልሔም በጌታችን ፊት ያደረጉት ስግደት የማይገባና የመራቸውም ኮከብ ከሰይጣን የተላከ እንደሆነ ያምናሉ ። #7ኛ.ጆቫዎች ክርስቶስ አስቀድሞ በሰማይ ከተፈጠረ በኀላ በዚያው ኗሯል ፡ ወደ ምድር እንዲመጣ ያስፈለገበት ዋነኛ ዓላማም ስለ ይሖዋ መንግስት ለመመስከር ነው ይላሉ ። #8ኛ.የይሖዋ ምስክሮች የዳግም ልደቱ መጀመሪያ በሚሆነው ጥምቀቱ ለእግዚአብሔር ልጅነት የተሾመ ነው በዚህም የአብ መንፈሳዊ ልጅ በመሆን የይሖዋ መንግስት ገዢ /ንጉስ/ ሆኗል ብለው ያምናሉ ። #9ኛ.የይሖዋ ምስክሮች ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ መላዕክት ሚካኤል ነው ብለውም ያምናሉ ። #10ኛ.የይሖዋ ምስክሮች የሰው ልጅ በስጋ ሲሞት ነፍሱም አብራ ትሞታለች። ዘላለማዊነት የይሖዋ ብቻ የተለየ ባህሪ ነው ብለው ያምናሉ ። #11ኛ. የይሖዋ ምስክሮች ኃጢያተኞች ከፃድቃን ተለይተው እንደሚጠፉ እንጂ በሲኦል የሚሰቃዩ መሆናቸውን አይቀበሉም ። ሌላው ቀርቶ ሰይጣን ይጠፉል እንጂ አይሰቃይም አባታችን አዳምም አንዴ ስለሞተ ትንሳኤ አያገኝም ይላሉ ። #12ኛ .መንፈስ ቅዱስ የሥላሴ አንዱ አካል ሳይሆን የይሖዋ ሀይል ነው ብለው ያምናሉ ። #13ኛ. በብዙ ትንሳኤ ያምናሉ ።ማለትም የታናሽ መንጋ ትንሳኤ ፣ምድራዊ ትንሳኤ ፣ የይሖዋ ምስክሮች አባል ላልሆኑትና ፃድቅ ለሆኑት የሚደረግ ትንሳኤ ብለው ትንሳኤን ከፉፍለው ያምናሉ። ወስብሀት ለእግዚአብሔር ።የአብ ፀጋ ፡ የወልድ ቸርነት የመንፈስቅዱስ ህብረት አንድነት ከኛ ጋር ይሁን ለዘለአለሙ አሜን
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#በመንፈሳዊ ሕይወትህ ለውጥ እንዲኖሮት ከፈለጉ


1ኛ የፀሎትን ህይወት ተለማመድ ተጠቀምበትም፣
#2ኛ ከመንፈሳዊ አባቶችና ሊቃውንት መ/ራን ምክርና ትምህርት አትራቅ
#3ኛ ከቅዱሳት መፃህፍት ጋር ያለህን ግንኙነት አዘውትር፣
#4ኛ የምትውልባቸውን ቦታዎች ፥የምታነባቸውን
መፃህፍት፥የምትመርጣቸውን ባልጀሮችህን ምረጥ፤ለመንፈሳዊ ህይወትህና ለሌሎች ወንድሞችህና እህቶችህ የሚያሰናክሉ እንዳይሆኑ ተጠንቀቅ፣

#5ኛ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ መሆንህን ዘወትር አትዘንጋ፣
#6ኛ አግባብ ያልሆነ ሃፍረትንና ፍርሃትን አስወግድ፥በራስህ ማስተዋልም
አትደገፍ፣
#7ኛ አላዋቂነትህን ተቀበል 'እኔ ብቻ' አትበል ውዳሴ ከንቱንም
አትፈልግ፣
#8ኛ ለሰራሃው ሃጢአት ሳትዘገይ ንስሃ ግባ፣
#9ኛ ልበ ደንዳናነትንና አመፀኛነትን ከአንተ አርቃቸው፣
#10ኛ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመኖርና የቃሉ ሙላት
በውስጥህ ኖሮ ከክርስቶስ ጋር መኖርን ተለማመድ በቃሉም
ፀንተህ ተገኝ፣
#11ኛ የቅዱሳንን ተጋድሎና ፍቅር በመመልከት እነርሱን
ለመምሰል ትጋ፣

#12ኛ ከዚህ በፊት የነበርክበትን የሃጢአት ህይወት ኮንነው
#13ኛ ሰዎችን/ባልንጀራህን አፍቅር ከጥላቻም ራቅ፣
#14ኛ ነገርን ሁሉ ለበጎነው ብለህ ተቀበል። ጌታ ሆይ ይህን
እንድናደርግ እርዳን አሜን
ይቆየን::
ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_1
#ፍቅር_ምንድነው_?
ፍቅር እውር ነው ?
አንድ ፈላስፋ ሲናገር ምን አለ በመጀመሪያ ፈጣሪ ሰውን ከመፍጠሩ በፊት ስሜቶችን ፈጠረ ፍቅር ፣ እብደት ፣ ቅናትና ውሸትን ከዛ ከፈጠራቸው ቡሃላ ተሰወረባቸው ። ስሜቶችም ኩኩሉ መጫወት ጀመሩ ። እብደት ቆጣሪ ነበር ። መጀመሪያ ውሸት ከዛ ቅናት ተያዘ ፍቅር ግን ከፅጌሬዳ አበባ ጀርባ ነበርና የተደበቀው ቢፈልገው ቢፈልገው አጣው ። ከዛ ቅናት ተናደደና ከአበባው ጀርባ እንደተደበቀ ነገረው ። እብደትም ቀስ ብሎ ሊያይ ፅጌሬዳውን ሳብ አርጎ ቢለቀው እሾሁ ሄዶ የፍቅርን አይን ወጋው ።ፍቅርም በከፍተኛ ድምፅ ጮኸ ፈጣሪም ተገለጠ በተፈጠረው ነገርም አዘነ ። የፍቅር ሁለቱም አይኖቹም እንደ ጠፉ አየ ። ፈጣሪም እብደትን አይኑን አጥፍተኸዋልና ከአሁን ቡሃላ ፍቅርን እጁን ይዘህ ወደ ሚሄድበት ቦታ ትመራዋለህ ብሎ አዘዘው። ከዛን ጊዜ ጀምሮ ፍቅርን ወደ ሚሄድበት ቦታ እጁን ይዞት የሚመራው እብደት ሆነ። እናማ ይሄ ታውሯል እንዴ ከዚች ጋር ፡ ይቺ አብዳለች እንዴ ከሱ ጋ አትበሉ ። ፍቅር ታውሯል የሚመራውም በእብደት ነውና ይላል ። እኔ ግን ፍቅር እውር ሳይሆን እንደውም ማየት ያለብንን ነገር የሚያሳየን አይናማ ነው እላለው። የፍቅር መገኛውና ምንጩ እግዚአብሔር ሲሆን የህግ ሁሉ ፍፃሜም ነው ።ለዚህ ነው ጳውሎስ የትእዛዝ ፍፃሜ ግን "በንፁህ ልብ ፣ በመልካም ጠባይ ፣ ጥርጥር በሌለበት ሃይማኖት መዋደድ ነው " ። ባለሙያዎች ፍቅር 3 ደረጃዎች አሉት ይላሉ #1ኛ.Relationship ይባላል። relat ማለት መገናኘት ሲሆን ship ደሞ ካርጎ በሚለው እንተርጉመው ። ማንኛውም ሰው የራሱ የሆነ አስተሳሰብ ፀባይና ባህሪ አለው ።ይሄንን ጭነቱን ይዞ ከአንድ ሰው ጋር ሲገናኝ ሲተዋወቅ ሪሌት አደረገ ወይም relationship ጀመረ ይባላል ። #2ኛ.ደረጃው ደሞ Friendship ይባላል። ይሄን ደሞ flow በሚለው እንተርጉመው ። የአንዱ አስተሳሰብ ወደ አንዷ የአንዷ ፀባይ ወደ አንዱ ሲፈስ freindship ይመሰረታል ። #3ኛ.ደረጃው ደሞ Intermacy ይባላል ። ይህም in to see me በሚለው ይተረጎማል ። ሪሌት አርገን ሀሳብ ፍሎው ካደረግን ቡሃላ ወደ ኢንቱ ሲ ሚ ወይም ውስጥን ወደ ማሳየት ያድጋል። አላማችንን ግባችንን የልባችንን ነገር ምናሳየው እዚህ ደረጃ ላይ ስንደርስ ነው ።በዚህ ውስጥ ያለፈ ፍቅር ጠንካራ ይሆናል ግቡም ልብ እንጂ የወሲብ ስሜት አይደለም። ፍፃሜውም በቃልኪዳን የታሰረ ጋብቻ ይሆናል ይላሉ ። #ሊቃውንቶች ደሞ በትዳር ጓደኞች መካከል ሊኖር የሚገባ ፍቅርን በደረጃ መለየት ይከብዳል ። ባልና ሚስት በ1 አካል ላይ ያሉ 2 አይኖች ናቸውና ይላሉ ። ሰው ለ2ቱ አይኖቹ የተለያየ ግምትና የፍቅር ሚዛን እንደማይኖረው ሁሉ በትዳር ጓደኞችም መካከል የሚኖር ፍቅርም ገደብና መጠን የሌለው ፍጹም #ፍቅር ነው ። የክርስቲያናዊ ጋብቻ ፍቅር መሰረቱ #ፍትወት አይደለም ። #ትዳር መሰረቱን ፍቅር ሲያደርግ ትዕግስት ይኖረዋል ፣ አንዱ ለአንዱ እንዲያዝን ያደርጋል ፣ አያቀናናም ፣ አያበሳጭም ፣ መተማመንን ያሰፍናል ፣ ይጸናል። በ1ኛ ቆሮ 13 ላይ ጳውሎስ የፍቅርን ባህርያት ነግሮናል ። "ፍቅር ይታገሳል ቸርነትንም ያደርጋል ፡ ፍቅር አይቀናም ፍቅር አይመካም አይታበይም ፡ የማይገባውን አያደርግም ፡ የራሱንም አይፈልግም ፡አይበሳጭም በደልንም አይቆጥርም ፡ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ አመፃ ደስ አይለውም ፡ ሁሉን ያምናል ፡ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል ፡ በሁሉ ይፀናል ፡ ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም ፡ ትንቢት ቢሆን ይሻራል ፡ ልሳንም ቢሆን ይቀራል ፡ እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሶስቱ ፀንተው ይኖራሉ ከነዚህም የሚበልጠው #ፍቅር ነው " ይላል። ም/ቱም ብናምን እግዚአብሔርን ነው ተስፋም ብናደርግ በእግዚአብሔር ነው #ፍቅር ግን እራሱ እግዚአብሔር ነውና ።

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_3
#የፍቅር_አይነቶች(Types of Love)
ብዙ ጊዜ ሰዎች ፍቅር ያዘኝ አፈቀርኩ ሲሉ ይሰማሉ ። እንደ ባለሙያዎች አገላለፅ ከሆነ 12 አይነት ፍቅር አለ ። እነሱን አንድ በአንድ እናያለን ከዛም የተያዘ ሰው የትኛው ፍቅር እንደያዘው እራሱን ያይበታል ። #1ኛ_ሮማንቲክ_ላቭ (Romantic Love ) ፦ ይሄኛው የፍቅር ዓይነት የሚይዛቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ የሰውነትን ቅርፅ ብቻ አይተው የሚያፈቅሩ ሰዎች ናቸው ። ሌሎቹን መሰረታዊ ነገሮች ግምት ውስጥ አያስገቡም ። ለምሳሌ ጥሩ ጸባይ እና ባህሪን፣ የአመለካከት ጥራትን ፣ ሃይማኖትን ፣ ስነምግባርን የመሳሰሉትን ነገሮች አያዩም ።የሚያዩት ተክለ ሰውነትን ብቻ ነው ። ነገር ግን ፍቅር እንደያዛቸው ይናገራሉ ። እንደዚህ አይነት ሰዎች ብዙ ጊዜ ቀናተኛ ናቸው ። ያፈቀሩትን ሰው ከእነሱ ውጭ ከሌላ ሰው ጋር ምንም ዓይነት ጤነኛ (Normal) ግንኙነት እንዲኖረው እንኳን አይፈልጉም ። ይህ ፍቅር ትኩረቱ ብዙ ጊዜ #በሩካቤ ሥጋ መውደቅ እንጂ #ትዳር አይደለም ። ስለዚህ እንደዚህ አይነቱ ፍቅር አይዘልቅም ።
#2ኛ_ፖሽኔት_ላቭ(Possinate Love) ፦ ይህ ፍቅር ስሜታዊ ፍቅር ነው ። ፖሽኔት ላቭ በጣም አስቸጋሪና ከባዱ የፍቅር ዓይነት ነው ። ሕይወትን የመመሰቃቀልና በጣም የማጨናነቅ ባህርይ አለው። ህሊናን እረፍት ከመንሳቱ ጎን ለጎን የወጣቶችን የወደፊትን የሕይወት ምዕራፍ የማጨለም ጉልበት አለው ። ለምሳሌ በስሜታዊ ፍቅር የተያዘ ሰው ትምህርት መማር ሁላ ሊያስጠላው ይችላል ። ከሰው ጋር ተደባልቆ ጊዜውን ከማሳለፍ ይልቅ ያፈቀረውን ሰው እያብሰለሰለ ለብቻው መሆን ይፈልጋል ፤ ምግብ እንኳን ይዘጋዋል አይምሮው ከፍቅር ውጪ ምንም ነገር ማሰብ አይፈልግም ። በመፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ በዚህ አይነቱ ስሜታዊ ፍቅር ተይዞ የተሰቃየ ሰው አምኖንን እናውቃለን ። /2ኛ ሳሙ 13/ በዚህ ፍቅር የተያዙ ሰዎች ለጊዜው እውነተኛ ፍቅር እንደያዛቸው ሊያስቡ ይችላሉ ። ማስተዋልን ሳይቀር የሚጋረድበት የፍቅር ዓይነት ነውና። የሚገርመው ደሞ ኀላ ላይ ያስጨነቀውን ያህል ከልብ ውስጥ መጥፋቱ አይቀርም ። እንዲህ አይነቱም ፍቅር ቆይታው ሩካቤ ስጋ እስኪፈፀም ድረስ ብቻ ነው ። ፍቅሩም ከዛች ቅፅበት ጀምሮ ይቆማል ። ይህን በዳዊት ልጅ በአምኖን ላይ ማየቱ ብቻ በቂ ነው ።
#3ኛ_ሎጂካል_ላቭ(Logical Love)፦ በዚህ አይነት ፍቅር የተያዙ ደግሞ የፍቅር መነሻቸው #መመሳሰል ነው ። ብዙ ጊዜ በሎጂክ ሕግ ነው የሚመሩት ። ሲያፈቅሩ በህይወታቸው ውስጥ ከዛ ሰው ጋር የሚያመሳስላቸው አንድ ነገር ስላዩ ነው ። ለምሳሌ እሷ ዲግሪ ካላት የምትመርጠው ዲግሪ ያለውን ነው ። እሷ ስራ አስኪያጅ ከሆነች የምትመርጠው ማናጀር ነው ። እነዚ ከነሱ ጋር የሚያመሳስላቸውን አቻቸውን ማፍቀር የሚፈልጉ ሰዎች ናቸው ። እንዲህ ሲባል ደግሞ በስራ ጠባይና በት/ት ማዕረግ የተመሳሰሉ ተጋቢዎች ሁሉ እዚህ ፍቅር ውስጥ ናቸው ማለት ግን አንችልም ። ይህ ፍቅር እንደሌሎቹ ሁሉ ዘላቂ አይደለም ። ምክንያቱም ያፈቀረችው ሰው ከእለታት 1 ቀን ያንን ስራ ሊለቅና ሊቀይር ይችላልና ። በዚህ ጊዜ እርሷ የፈለገችው የተመሳሰሉበት መስመር ተቀየረ ማለት ነው ። በተጨማሪም ያቺ ሴት ሥራውን እንጂ ሌሎች ነገሮቹን ስለማታውቅለትና በሕይወቱም ሳትማረክለት የጀመረችው ብዙ ነገር ስላለ ፍቅሩም ላይዘልቅ ይችላል፡፡
🌼🌼🌼ይቆየን

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret
#ኦርቶዶክሳዊ_የጾታ_ትምህርት
#ክፍል_8
#የእጮኝነት_ጊዜ
መሰረቱ ጠንካራ የሆነ ህንፃ አስተማማኝ ኩራት ነው ። መሰረቱ የተስተካከለና ጠንካራ የሆነ የፍቅር ጅማሬም እንደዚያው ነው ። ትዳር ከእጮኝነት ጊዜ መሠረቱ ጥሩ ካልሆነ መልካም ጎኑ ደምቆ አይታይም ። እና ይህ ጊዜ በጣም ጥንቃቄን ይፈልጋል። አስበን አውጥተን ፣ አውርደን ፣ በተለይም እግዚአብሔር ለሚወድልን ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ትርፍና ኪሳራውን አመዛዝነን ፣ የምንጀምረው የፍቅር ውጥን ነው ። መተጫጨት በራሱ ለነገው ሕይወታችን የዛሬ መሰረት ነው ። ከሁሉ በፊት ግን ፍቃድን ለእግዚአብሔር መስጠት ያስፈልጋል ። #የክርስትና_ሕይወት ማለት ከራስ ፍቃድና ጥበብ ውጪ ሆኖ #በእግዚአብሔር_ፈቃድ ውስጥ መኖር ማለት ነው ። ጥበብ ፣ ፍልስፍና ፣ ሊቅነትና ሰፊ የእውቀት አድማስ እንኳን በውስጣችን ስፍራ ቢኖራቸውም በእግዚአብሔር ፍቃድ ውስጥ ካልዋሉና በመንፈስቅዱስ ኃይል ካልታገዙ በራስ መደገፍ ብቻውን ትርጉም አይኖረውም ። ሰለሞን ለዚህ ነው "በራስህ ማስተዋል አትደገፍ" ያለው ምሳ 3÷5
#ከማጨት_በፊት_ምን_ያስፈልጋል_?
#1ኛ #አካላዊ_ብቃት (Physical Maturity) ፦ አንድ ሰው ከማጨቱ በፊት ማሰብ ከሚገባቸው ነገሮች መካከል ለአካላዊ ብቃት መድረሱን ነው ።ለዚህ ነው ቅዱስ ጳውሎስ "ዳሩ ግን ማግባት ወደሚገባው ዕድሜ በደረሰ ጊዜ ..." ብሎ ለፍቅር ሕይወት የእድሜን ወሳኝነት የነገረን ። (1ኛ ቆሮ7÷36) ሠሎሞንም "ለመውደድም ጊዜ አለው "ያለው ቃል ይህንን ሃሳብ የሚያጠናክርልን
#2ኛ #መንፈሳዊ_ብስለት (Spritual Maturitey )
በመንፈሳዊ ሕይወት መብሰል ለምናደርጋቸው ነገሮች ሁሉ ስኬት ውበት ነው ። በመንፈሳዊው ነገር የበሰለ ሰው ቤቱን በዓለት ላይ የሠራን ሰው ይመስላል ። ከማጨት አስቀድሞ ራስን ማየት ያስፈልጋል ። ያልበሰለ ሰው ያየው ሁሉ ያምረዋል ። ዐይኖቹ ላረፈበት ነገር ሁሉ ቶሎ ይሸነፋል ። እንደ ዮሴፍ በሩን ሰብሮ መውጣት ቢያቅተው እንኳን ቢያንስ እንደ ትዕማር "ይህ በእስራኤል ዘንድ ኃጢአት ነው " (2ሳሙ 13÷12)እንኳን አይልም ።
#3ኛ #የኢኮኖሚ_ብቃት (Economical Maturation ) ፦የፍቅር ሕይወት አላማ #ጋብቻ ነው ። በጋብቻ ሕይወት ለመኖር ደግሞ ኢኮኖሚ አንዱ ነገር ነው ። ለትዳር ጣራ የነካ ኢኮኖሚ ባያስፈልግም የተወሰነ የኢኮኖሚ አቅም ግን ያስፈልጋል ። በቀጣይ ደሞ የተሳሳቱ የማጫ (የፍቅር ጓደኛን) መምረጫ መንገዶችን እናያለን ይቆየን

ፍኖተ መንግስተ ሰማያት
ይህ ቻናል ብሂለ አበው፣እራሳችንን እንድንፈትሽ የሚያደርጉ ጽሑፎች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች የሚተላለፉበት መንፈሳዊ ቻናል ነው፡፡
ለሚኖራችሁ ማንኛውም ሀሳብ ጥያቄና አስተያየት

👉 ኢዮአታም

ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ፡፡
https://t.me/zekidanemeheret