TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.37K videos
198 files
3.64K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬆️

በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር #ታከለ_ኡማ ሰብሳቢነት የሚመራው እና የፌደራል ፖሊስ ፣ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽኖችን ያካተተው የፀጥታ ግብረሀይል ሳምንታዊ ውይይት አድርጎል። በተለይ በመዲናዋ የአዲስ አመት በዓል ያለምንም #የፀጥታ ችግር እንዲከበር በሚደረጉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ተወያይተዋል።

ህብረተሰቡ የሚመለከታቸውን #አጠራጣሪ ነገሮች #ለፖሊስ በማሳወቅ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ግብረሀይሉ #አሳስቧል

ግብረሀይሉ በህገወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ የገቡ 300 የሚሆኑ ሞተር ሳይክሎችን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጎል። በተመሳሳይ ከቀናት በፊት በርካታ ቁጥር ያለው ህገወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉ ይታወሳል።

©የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና📌

ከአዲስ አበባ ግጭቱ ጀርባ፦

በከተማዋ የሚታየዉ #የፀጥታ ችግር በቀን ጅቦች #ስፖንሰርነት ቅጥረኞች ያነሱት መሆኑ ታዉቋል። አለማዉ ህዝቡን በማባላት ወደ #ሥልጣን መመለስ ነዉ። ቅጥረኞች ሰልጥነዉ የተሰማሩ ከመሆናቸዉም በላይ በሞተር ሳይክል፣ በቤት መኪና እና በፕካፕ ገንዘብ እየተበተነላቸዉ መሆኑን የአይን እማኞች ገልፇል። ረብሻኞቹ ከሌላ ቦታ ተመልምሎ የመጡ ሲሆን የአዲስ አበባ ወጣት የለበትም። በብዙ ቦታዎች ደግሞ የአዲስ አበባ ህዝብ ግጭት እንዳይፈጠር ሲከላከል እንደነበር ታዉቋል። የግጭት ፕሮጄክቱ ሙሉ በሙሉ የፀረ-ለዉጥ ኃይሉ መሆኑ በተጨባጭ ማስረጃ ተረጋግጧል! ባንዲራ #ሽፋን እንጂ መነሻ አይደለም። ሁለቱንም ባንዲራ የማይወዱ ሰዎች አንዱን ደግፎ ሌላዉን የተቃወሙ ያስመስላል።

ማስታወሻ፦

1. የረብሻኞቹ ፎቶ እና ቪዲዮ ይቀረፅ
2. የመኪኖቹ ታርጋ ይመዝገብ
3. ማስረጃ ለፌዴራል እና ለአዲስ አበባ ፖሊስ አድርሱ።

Oduu Ammee📌

Jeequmsi #Finfinnee waraabeyyii guyyaatiin kan qindeeffame ta'uu barameera. Jeeqxoti bakka biraatii filatamanii leenjifamuun bobbaafaman. Makiinaan maallaqa hiraa akka jiranis barameera.

Bakka jeequmsi jirutti suuraa fi viidiyoo jeeqxotaa waraabuu fi taargaa konkolaataa qabuu hin dagatinaa!

ምንጭ፦ አቶ ታዬ ደንደአ(የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update "በሀገሪቱ ካለው #የፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመግቢያ ቀን ተራዘመ" እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍፁም ከእውነት የራቀና የሀገራችን ሰላም መሆን እንቅልፍ የሚነሳቸው ሰዎች የሚያስወሩት ነው።

🕊እኛ ሁላችንም የኢትዮጵያ ሀገራችን ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ነን። በሰላማችን ጉዳይ ከማንም ጋር አንደራደርም🕊
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን‼️

ትናንትና እና ዛሬ በአማራ ክልል በሁሉም ቦታዎች የከተራ እና የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከብሯል፡፡ በዓሉ ያለምንም #የፀጥታ_ችግር መጠናቀቁን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥቷል፡፡

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ሰይድ አህመድ በክልላችን በሁሉም ቦታዎች በዓሉ ያለምንም የፀጥታ ችግር ተጠናቋል ብለዋል፡፡

ፖሊስ እና የፀጥታ ኃይሉ ከሳምንት በፊት ዝግጅት እንዳደረጉ የተናገሩት ረዳት ኮሚሽነሩ በአንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ስጋቶች ቢኖሩም ያለምንም የፀጥታ ችግር መጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡

የፀጥታ ኃይሉ ወጣቶች የሃገር ሽማግሌዎች እና የሀይማኖት አባቶች ከፖሊስ ጋር እጅ እና ጓንት ሆነው በመስራታቸው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ማመስገን ይፈልጋል ብለዋል ረዳት ኮሚሽነሩ፡፡

ነገ የሚከናወነውን ቀሪ በዓልም በተመሳሳይ ዝግጅትና ጥበቃ ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የፀጥታ_ችግር

ሰሞኑን ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ አሶሳ ከተማ 96 ኪሜ ርቀት ላይ የምትገኘው ማና ሲቡ ፤ መንዲ ከተማ (ምዕራብ ወለጋ) እና አካባቢው ላይ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ መኖሩና ከፀጥታ ኃይሎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ሲደረግ እንደነበር ቤተሰቦቻችን ገልፀዋል።

አንድ በአካባቢው ላይ ቤተሰቦቹ የሚኖሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባል፤ ከትላንት ወዲያ ሰኞ  ታጣቂዎች ከማለዳ ጀምሮ ቶክስ በመክፈት ወደመንዲ ከተማ ድረስ ዘልቀው በመግባት በመንግስት መ/ቤቶችና ተቋማት ላይ ጥፋት ሲያደርሱ እንደነበር አመልክቷል።

ባንኮችም ተዘርፈዋል።

በከተማው የህዝብ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዝግ እንደሆኑና ከአሶሳ-መንዲ የህዝብ ትራንስፖርት ሙሉ ለሙሉ እንደተቋረጠ በክስተቱ ንፁሃን ሰዎች እየተገደሉ ገልጿል።

መንዲ እና አካባቢው ከባድ ሁኔታ ላይ ነው ያሉት ያለው የኸው የቤተሰባችን አባል "ቁጥራቸው እጅግ በጣም ብዛት ያላቸው የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው ወደ ከተማ ዘልቀው ገብተው ጥፋት ያደረሱት" ሲል አስረድቷል።

ከአሶሳ ጋር የሚያገናኘውን ዋናውን አስፓልት በመቆረጡ ነዋሪው ትልቅ ስጋት ላይ እንደሆነ ገልጾ " የንፁሃን ደም ከመፍሰሱ በፊት መንግስት ፈጣን መፍትሄ እንዲሰጥ  እንፈልጋለን " ብሏል።

"  ብዙ ዘመዶቼ እዛ ስላሉ እኔም ጨንቀት ላይ ነኝ " ሲል ሀሳቡን አጋርቷል።

የምዕራብ ወለጋ ዞን የአስተዳደርና የፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ደበላ ኦላና ደግሞ " ከሰኞ ጀምሮ እስከ ትላንት ማክሰኞ ድረስ የፀጥታ ኃይሉ እና ታጣቂዎች እየተዋጉ ነው " ሲሉ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ተናግረዋል።

አቶ ደበላ በአካባቢው ከሰኞ ጀምሮ ተኩስ እንደነበርና #ከተማው ውስጥም ተኩስ እንደነበር አመልክተዋል።

ታጣቂዎቹ ወደ ከተማ ዘልቀው ሳይገቡ እንዳልቀረ ጥርጣሬ እንዳላቸውም ለሬድዮ ጣቢያው በሰጡት ቃል ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
#የፀጥታ_ችግር

ዘላቂ ሰላም ያልተገኘለት እና ዛሬም ድረስ የሰዎችን ህይወት እየቀጠፈ ያለው ቀጠና መፍትሄው ምንድነው ?

• ከ2010 ዓ/ም አንስቶ የበርካታ ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ ንብረት ወድሟል። እርቅ ለመፈፀም ተሞክሮ ዘላቂ ሰላም አልመጣም።

• ከሰሞኑ በተፈፀሙ ጥቃቶች የበርካታ ሰዎች ህይወት አልፏል፤ ንብረት ወድሟል ፤ እርቅ ለመፈፀም ጥረት እየተደረገ ነው።

• ዛሬ ወደ ገበያ በሚያቀኑ ሰዎች ላይ በተፈፀመ ጥቃት በርካታ ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ ተጎድተዋል።

በደቡብ ክልል መን፤ በጉራጌ ዞን በመስቃን እና ማረቆ መካከል በተደጋጋሚ ጊዜ የፀጥታ ችግሮች እየተከሰቱ የበርካታ ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ፣ ንብረት ሲወድም ፣ ተማሪዎች ከትምህርት ሲስተጓጎሉ ፣ የመንግሥት ስራም ሲበደል በአጠቃላይ በቀጠናው ከፍተኛ ተፅእኖ ሲደርስ ቆይቷል።

በአካባቢው ያለውን ችግር ለመቅረፍ ከዚህ ቀደም የዕርቅ ጥረቶች ተደርገውም ያውቃሉ።

ከሰሞኑን ደግሞ በዚሁ አካባቢ በተፈጠረ የፀጥታ ችግር የበርካታ ሰዎች ህይወት አልፏል ፤ ጉዳትም ደርሷል።

አንድ ስለ ጉዳዩ አውቃለሁ ያሉ የቤተሰባችን አባል ፤ " መስቃን እና ማረቆ ባንተ ወረዳ ይሄን ያክል ቀበሌ አለኝ አንተ የለህም የኔነዉ ያለኝ ባንተ ወረዳ እየተባባሉ ግጭት ከተጀመረ ከ2010 ዓ.ም አንስቶ እስከ ዛሬዉ ቀን ሰዉ ከመሞትና ቤት ንብረት ከመቃጠልና ከመዘረፍ አልቆመም " ብለዋል።

እኚሁ የቤተሰባችን አባል ፤ በዞኑ እንዲሁም በክልሉ ያሉ አመራሮች ለችግሩ ምንም አይነት ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጡ እንዳልቻሉ ፤ ካቅማችን በላይ ነዉ ብለዉም ለከፍተኛ አካል ለፌደራል መንግስት የሰጡት / ያስረከቡት ነገር እንደሌለ አስረድተዋል።

ከሰሞኑንም በዚሁ ቀጠና ላይ የሰዎች ህይወት መቀጠፉን ንብረት መውደሙን አመልክተዋል።

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-07-29

@tikvahethiopia