TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬇️

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ለ1439ኛው የአረፋ በዓል በሰላም እንዲከበር አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን አስታውቋል።

ሕብረተሰቡ በበዓሉ ላይ በአዲስ አበባ ስቴድየም እና በዙሪያው #ፍተሻ መኖሩን ተገንዝቦ ለፍተሻ እንዲተባበር፣ የእምነቱ ተከታዮች ለሶላት ሲመጡ የስለት መሳሪያዎችንና ሌሎች አዋኪ ነገሮችን ይዘው ባለመምጣት የተለመደ ትብብር እንዲያደርጉ ኮሚሽኑ ጥሪውን አስተላልፏል።

ኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ስቴድየም የሚደረገውን የሶላት ስነስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችንምይፋ አድርጓል:-

➢ ከቦሌ- ኦሎምፒያ -ፍላሚንጎ ወደ መስቀል አደባባይ

➢ ከኡራኤል-ባምቢስ ወደ ምስቀል አደባባይ

➢ ከአራት ኪሎ - ብሔራዊ ቤተመንግስት ወደ እስጢፋኖስ ቤተክርስትያ

➢ ካሳንችስ -ብሔራዊ ቤተመንግስት -ፍልውሀ

➢ ከንግድ ማተሚያ ቤት -ኦርማ ጋራዥ- ፍል ውሃ -ሐራምቤ ሆቴል

➢ ከቴድሮስ አደባባይ -ኢምግሬሽን- ሀራምቤ ሆቴል - ስቴድየም

➢ ከጎማ ቁጠባ- ብሄራዊ ትያትር- ስቴድየም

➢ ከሰንጋ ተራ - በድሉ ህንጻ -ስቴድየም

➢ ከሰንጋ ተራ - በለጋሀር- ስቴድየም

➢ ከሜክሲኮ አደባባይ- በለገሀር -ስቴድየም

➢ በቂርቆስ አዲሱ መንገድ -በለገሀር -ስቴድየም

➢ በሀራምቤ ሆቴል -ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ

➢ ከጎተራ - በአራተኛ ክፍለ ጦር ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለጊዜው ለተሽከርካሪ ዝግ ሲሆኑ:-

ከቦሌ ወደ አራት ኪሎ መሄድ የሚፈልጉ ተሽከርካሪዎች

➢ በኡራኤል -በካሳንችስ-አራት ኪሎ
ከመገናኛ ወደ ጦር ሀይሎች መሄድ የሚፈልጉ አሽከርካሪዎች

➢ በኡራኤል -ካሳንችስ -ታላቁ ቤተመንግስት -እሪበከንቱ -ቴዎድሮስ አደባባይ- ኤክስትሪም ሆቴል- ተክለሀይማኖት- ጦር ሀይሎች ከሳሪስ አቅጣጫ ወደ አራትኪሎ እና ፒያሳ መሄድ የሚፈልጉ አሽከርካሪዎች

➢ ጎተራ -ወሎ ሰፈር - አትላስ ሆቴል - ኡራኤል - ካሳንችስ -አራት ኪሎ ያሉ መንገዶች በአማራጭነት መጠቀም እንደሚችሉ ኮሚሽኑ ገልጿል።

ከዛሬ ነሀሴ 14/2010 ማታ ጀምሮ የሶላት ስነስርዓቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በስታድየም ዙሪያ እና አከባቢው በግራና ቀኝ ለረጅም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍጹም #የተከለከለ መሆኑንም ኮሚሽኑ አስታውቋል።

ሕብረትሰቡ ለጸጥታ #አጠራጣሪ የሆኑ ነገሮች ሲያጋጥሙት ይሁን የፖሊስ አገልግሎትን ለማግኘት ከፈለገ በስልክ ቁጥሮች

• 011-5- 52-63-03
• 0115-5- 52- 40-77
• 011-5- 52- 63-02
• 011-1- 11-01-11 ወይም በነጻ ስልክ መስመር 991 እና 987 መጠቀም እንደሚችል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

©EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

በምክትል ከንቲባ ኢንጂነር #ታከለ_ኡማ ሰብሳቢነት የሚመራው እና የፌደራል ፖሊስ ፣ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽኖችን ያካተተው የፀጥታ ግብረሀይል ሳምንታዊ ውይይት አድርጎል። በተለይ በመዲናዋ የአዲስ አመት በዓል ያለምንም #የፀጥታ ችግር እንዲከበር በሚደረጉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ላይ ተወያይተዋል።

ህብረተሰቡ የሚመለከታቸውን #አጠራጣሪ ነገሮች #ለፖሊስ በማሳወቅ አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ግብረሀይሉ #አሳስቧል

ግብረሀይሉ በህገወጥ መንገድ ወደ አዲስ አበባ የገቡ 300 የሚሆኑ ሞተር ሳይክሎችን በቁጥጥር ስር እንዲውሉ አድርጎል። በተመሳሳይ ከቀናት በፊት በርካታ ቁጥር ያለው ህገወጥ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉ ይታወሳል።

©የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲስ አበባ ፖሊ ስ‼️

በዓሉ በሰላም እንዲከበር የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለጸጥታ አካላቱ የተለመደ #ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪ አስተላልፏል።

ህብረተሰቡ የፖሊስ አገልግሎትን ለማግኘትም ሆነ #አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ጥቆማ ለመስጠት በ991 ወይም 816 ነፃ የስልክ መስመሮችን እና 011-1-11 01 11፤011-1-26 43 59 011-1 01 02 97 ፤011-8-69 88 23፤011-8-69 90 15 መጠቀም እንደሚቻል ኮሚሽኑ አሰታቋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia