TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የሰኔ 16 የቦምብ ጥቃትን በመሩ፣ ባቀነባበሩና የፋይናንስ ድጋፍ ባደረጉ ግለሰቦች ላይ ሲያካሂድ የቆየውን ምርመራ #አጠናቋል። በዚህም መሰረት ጥቃቱን በማቀነባበር፣ በመምራትና በፋይናንስ በመደገፍ የተሳተፉ ግለሰቦች ማንነትና የምርመራ #ውጤቱን አስመልክቶ ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ በሚቀጥለው ሳምንት #መግለጫ እንደሚሰጥ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ #ብርሃኑ_ጸጋዬ ተናግረዋል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሶማሌ ክልል‼️

መጋቢት 29 ቀን 2011 ዓ.ም የሚጀመረው #ሦስተኛው_ዙር የህዝብና ቤት ቆጠራ በተሳካ መልኩ እንዲከናወን ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሶማሌ ክልል ገለጸ፡፡ የህዝቦች አንድነትንም ሆነ የሕግ የበላይነትን የማይፈልጉ #የመገንጠል አጀንዳ ያላቸው ኃይሎች ክልሉን መጠቀሚያ ለማድረግ ፍላጎት ያላቸው መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ #ሙስጠፋ_ሙሐመድ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት፤ የህዝብና ቤት ቆጠራው ዋና ዓላማ ህዝብ እንዲቆጠር ማድረግ ነው፡፡ የፌዴራል መንግስቱም ከዚህ የተለየ ዓላማ እንደሌለው ስለሚታወቅ ለቆጠራ መሳካት እንደ ክልል ከፌዴራል መንግስት ጋር በትብብር እንሰራለን፡፡ ለዚህም በድንበር አከባቢ ሊፈጠሩ ይችላሉ የሚባሉ ችግሮችን በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ እያስቀመጥን እንገኛለን፡፡

ይሁን እንጂ ቆጠራውን አጀንዳ ማድረግ የሚፈልጉ፤ ገና ምንም ሳይቆጠር ቁጥራችን ሊቀነስ ነው፤ እንዲህ ታስቧል፤ እንዲህ ተደርጓል፤ እያሉ #ውጤቱን ከአሁኑ ለመወሰንና የክልሉን አስተዳደር አጣብቂኝ ውስጥ ለመክተት የሚሞክሩ ሃይሎች አሉ፡፡ ክልሉ ግን አስተማማኝና ሊታመንበት የሚችል ሂደትን በመከተል፤ ምክንያታዊ የሆነ ውጤት እንዲመጣ ለማስቻል እየሰራ ይገኛል፡፡

በሌላ በኩል፣ በክልሉ ያለው አዲስ አመራር ለህዝቡ የላቀ ተሳትፎና ተጠቃሚነት እየሰራና #ለውጡንም የህዝብ ጥቅም ማስጠበቂያ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የጠቆሙት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ፤ አንዳንድ ሃይሎች ግን ክልሉን የመጥፎ ሀሳባቸው ማስፈጸሚያ ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ እነዚህ ሃይሎች ደግሞ የዚህን ክልል ህዝብ ሲገድሉና ሲጨፈጭፉ፤ የክልሉን በጀት ከክልሉ አመራር ጋር ሲመዘብሩ የነበሩ ጥቂት ጄኔራሎች እና የእነርሱ የፖለቲካ ነፍስ አባቶች ሲሆኑ፤ ይሄ ተግባር ደግሞ የመገንጠል ዓላማቸው ምዕራፍ ነው፡፡ የሶማሌ ክልል ሲረበሽ ‹ኢትዮጵያ ስለፈረሰች ምንም ማድረግ አይቻልም እኛም እንሂድ› የሚል አመለካከት ስላላቸውም የሚፈጽሙት ተግባር ነው ብለዋል፡፡

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን
@tsegawolde @tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ውጤትን የተመለከተ መግለጫ!

የ12ኛ ክፍል ውጤትን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስትሩ ሚኒስቴር ዶክተር ጥላዬ ጌቴ፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገ/እግዚአብሔር ምክትል ዳይሬክተሮች ዶ/ር ዘሪሁን ዱሬሳ እና አቶ መሳይ ደምሴ፣ እንዲሁም የየክልሎች የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች የሆኑት ዶክተር ጌታሁን ጋረደው የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ፣ ዶ/ር ቶላ ባሪሶ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም ዶክተር ይልቃል የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በተከታታይ #ውጤቱን በተመለከተ በጋራ በተላለፈው #ውሳኔ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚሁም መሰረት በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና ያጋጠመ ችግር መኖሩን በተለይ በደንብ ጥሰት ዙሪያ #በማረጋገጫ የተያዘባቸው ተማሪዎች ውጤት መሰረዙ እና በደንብ ጥሰቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በየደረጃው ተጠያቂ የሆኑበት ሁኔታን እንዳለ ሆኖ፤ ፈተናዎቹ ከሰጡባቸው ቀናት ሀሙስና አርብ ማለትም በ6 እና 7/10/2011ዓ.ም ከተሰጡት ፈተና ውጤቶች በተለየ ከቅዳሜና እሁድ በኋላ ሰኞ እና ማክሰኞ ማለትም በ10 እና 11 10/2011ዓ.ም በተሰጡት ፈተናዎች በግልጽ የታየ የውጤት ግሽበት መኖሩ በመረጋገጡ የዩንቨርስቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥቡ በአራቱ የትምህርት ዓይነቶች ላይ መሰረት ያደረገ እንደሚሆን መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ እነዚህም እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ አፕቲቲዩድና ፊዚክስ ለተፈጥሮ ሳይንስ ሲሆኑ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ አፕቲቲዩድና ጂኦግራፊ ለማህበራዊ ሳይንስ ይሆናሉ፡፡

ይህም ሲሆን ተማሪዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ሊገነዘቡ የሚገባቸው ተማሪዎቹ ያስመዘገቡት ውጤት በመምህርነት ሙያ ለመማር ከመረጡ ተማሪዎች ውጪ ለዩንቨርስቲ መግቢያ ብቻ የሚያገለግልና የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ተብለው ዩንቨርስቲ እንደሚገቡና ከአንድ ዓመት የፍሬሽማን ኮርሶች በኋላም በሚያስመዘግቡት ውጤት መሰረት የፈለጉትን የትምህርት ፊልድ መርጠው መማር የሚችሉ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የተከሰተውን #ግሽበት በተመለከተም የማጣራት ሂደቱን የሚያካሂድ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩ የሆነ ኮሚቴ መቋቋሙን የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር #ጌታሁን_ጋረደው ያሳወቁ ሲሆን ተጠያቂው አካል አስተማሪና የማያዳግም እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑን አሳውቀዋል፡፡

በመግለጫው ማጠቃለያም የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶክተር #ጥላዬ_ጌቴ እንደገለጹት የመቁረጫ ነጥቡን በተመለከተ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ችግር የነበረባቸው አካባቢዎች የተፈተኑ ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ የሚታይላቸው መሆኑንና በጥቂት ቀናት ውስጥ በኤጀንሲው የሚገለጽ መሆኑን እንዲሁም በታየው የውጤት ግሽበት ምክንያት የተያዙት የተማሪዎች ውጤቶች #እንደሚለቀቅ ጨምረው አሳውቀዋል።

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia