TIKVAH-ETHIOPIA
1.5M subscribers
56.7K photos
1.41K videos
203 files
3.87K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update "...ጉባኤተኛው ገና ያላፀደቀውና በተለይም የድርጅቱ ሊቀመንበር ጓድ ደመቀ መኮነን በክብር #ይሰናበቱ አይሰናበቱ የሚለው በጉባኤተኛው ሰፊ ክርክር እየተካሄደበት ያልተጠናቀቀ በመሆኑ ገና #ውሳኔ ላይ አልተደረሰም፡፡ ጉባኤው #በዛሬው ውሎ በእንጥልጥል ያደሩ በክብር በትምህርትና በአንባሰደርነት ለማእከላዊ ኮሚቴነት በማይወዳደሩ አመራሮች ዙሪያ
የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከዚህም በተጨማሪ አዲስ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላትንና የድርጅቱን ስራአስፈፃሚ ኮሚቴ አባላትን የድርጅቱን ሊቀመንበርና ም/ሊቀመንበር እንዲሁም የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን አመራር አካላትን ይመርጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡"

ምንጭ፦ANDM CC office
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢህአዴግ ጉባኤ ሀዋሳ⬇️

የኢህአዴግ አጋር ድርጅቶች በድርጅቱ ስራ አስፈፃሚና ምክር ቤት ውስጥ እንዲሳተፉ በ11ኛው የኢህአዴግ ጉባዔ ላይ ተወሰነ።

የአጋር ድርጅቶች ሊቀመናብርትና ምክትል ሊቀመናብርት በቀጥታ በኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እንዲሳተፉ ተወስኗል።

እንዲሁም የአጋር ድርጅቶቹ አምስት የስራ አስፈፃሚ አባላት በኢህአዴግ ምክር ቤት እንዲሳተፉም ነው ጉባዔው #ውሳኔ ያስተላለፈው።

የጉባዔውን መጠናቀቅ አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት አቶ ፍቃዱ ተሰማ፥ የአጋር ድርጅቶቹ የሚሳተፉት #ያለድምፅ መሆኑን ተናግረዋል።

አጋር ድርጅቶቹን ወደ ሀገራዊ መድረክ ለማምጣትና አንድ ሀገራዊ ፓርቲ ለመመስረት በጥናትና እውቀት ላይ ተመስርቶ ውይይት በማድረግ ወደ ኢህአዴግ የመቀላቀሉ ሂደት እንዲጠናቀቅ ጉባዔው ለኢህአዴግ ምክር ቤት ውክልና ሰጥቷል።

ጉባዔው በህግ የበላይነት መከበር ፣ በልማት ስራዎች፣ በወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይም ከመቼውም ጊዜ በተሻለ እንዲሰራ አቅጣጫ ማስቀመጡ ተገልጿል።

ከጎረቤት ሀገራት ጋር የተጀመረው የዲፕሎማሲ ስራም ብሄራዊ ጥቅምን በሚያስጠብቅ መልኩ ተጠናከሮ ይቀጥላል ተብሏል።

በየአካባቢው አየተስተዋለ ያለው መፈናቀልና ሰብዓዊ መብት ጥሰት በምንም መልኩ ድርጀቱ እንደማይታገስም አቶ ፍቃዱ በመግለጫቸው አመልክተዋል።

ለዚህም የፀጥታ አካላት ተገቢውን #እርምጃ እንዲወስድ አቅጣጫ እንደተቀመጠም ነው የጠቆሙት።

የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ለማስቀጠል የመንግስት ተቋማት ሪፎርም እንዲደረግ ስምምነት ላይ መደረሱ ተነግሯል።

በተለይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን የሚያሰፉ ገለልተኛና ወገንተኝነታቸው ለህዝብ የሆኑ ተቋማት ለመገንባት የሪፎርም ስራዎች በአፋጣኝ
ተግባራዊ እንዲሆኑ ጉባዔው አሳስቧል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መከላከያ ሰራዊት‼️

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ትላንት ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ የመከላከያ ሰራዊት ማሻሻያ አዋጅን ጨምሮ በአራት ጉዳዮች ላይ #ውሳኔ አሳለፈ።

ውሳኔ ከተላለፈባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የአገር መከላከያ ሰራዊቱን የሚመለከት ሲሆን የአገር መከላከያ ሚኒስቴር የመከላከያ ሰራዊት አዋጅ ቁጥር 809/2006ን ለማሻሻል የሚያስችል ረቂቅ አዋጅ አዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አቅርቧል።

በአገሪቷ የተፈጠረውን ለውጥ ተከትሎ መከላከያ ሰራዊቱ አገራዊ ተልዕኮውን በተሻለ ብቃት እንዲወጣ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የማሻሻያ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የጠቀሰው ምክር ቤቱ የሰራዊቱን የግዳጅ አፈጻጸም ብቃት ለማጠናከርም የህግ ማዕቀፍ አስፈላጊ መሆኑን አመልክቷል።

በመሆኑም ምክር ቤቱ በጉዳዩ ላይ ከተወያየ በኋላ ማሻሻያዎችን በማከል ረቂቅ አዋጁ እንዲጸድቅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ልኳል።

ምክር ቤቱ በሌላ በኩል የስራ ዕድል ፈጠራ ኮሚሽን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የተዘጋጀውን ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ደንቡ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል።

ምክር ቤቱ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት እንዲሁም የፌዴራል ዓቃቢያን ህግ መተዳደሪያ ረቂቅ ደንብ ተግባርና ሃላፊነትን ለመሰወን በተዘጋጀው ረቂቅ ደንብ ላይም ተወያይቶ ደንቡ ስራ ላይ እንዲውል ወስኗል።

የኢትዮጵያ ልማት ምርምር ኢንስቲትዩትና የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል በቅርቡ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ተብሎ መቋቋሙ ይታወሳል።

የኢንስቲትዩቱን ስልጣን፣ ተግባርና አደረጃጀት ለመወሰን የፕላንና ልማት ኮሚሽን ረቂቅ ደንብ አዘጋጅቶ ባቀረበው መሰረት ነው ምክር ቤቱ ዛሬ ውሳኔ ያሳለፈው።

በተመሳሳይ በስራ ላይ ያለው የፌዴራል ዓቃቢያን ህግ መተዳደሪያ ደንብ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ፀድቆ ስራ ላይ ከዋለ ረጅም ዓመታት ያሳለፈ በመሆኑ በአሰራር የታዩ ክፍተቶችና ሎላዊነት ያስከተላቸው ለውጦችን ከግምት ውስጥ በማስገባት ደንቡን መለወጥ እንዳስፈለገ ተመልክቷል።

ምንጭ፡ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት‼️

ፓርላማው ነገ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢን ሹመት ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

• የቀድሞ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ወ/ት #ብርቱካን_ሚደቅሳ ሰብሳቢ ይሆናሉ ተብሏል

• የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጉዳይ #ውሳኔ ላይ #አልተደረሰም

በነገው ዕለት አራተኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሰባተኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል ተብሎ የሚጠበቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት በጠቅላይ ሚኒስትር #አብይ_አሕመድ ዕጩ ሆነው የሚቀርቡትን የቀድሞዋ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪና የሕግ ባለሞያ ወ/ት ብርቱካን ሚደቀሳ ሹመት ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሞያው አቶ ዳንኤል በቀለ (እጩ ዶክተር) ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነርነት በዕጩነት ቀርበው በመንግሥትና በእርሳቸው በኩል የተጀመረ ንግግር ቢኖርም እስካሁን የመጨረሻ ውሳኔ ላይ አለመደረሱን ምንጮች ጠቁመዋል።

በመንግሥትና በአቶ #ዳንኤል_በቀለ መካከል ንግግር መጀመሩንና ነገር ግን ውሳኔው አለመጠናቀቁን ለማወቅ ተችሏል።

🔹አቶ ዳንኤል በቀለ (እጩ ዶክተር) ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪና በዲቨሎፕመንት ስተዲስ በሁለተኛ ዲግሪ ተመርቀዋል። እንግሊዝ ከሚገኘው ኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ በዓለም አቀፍና የሰብዓዊ መብቶች ሕግ በማስተርስ ተመርቀዋል። በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ሕግ ከዚያው ከኦክስፎርድ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ለመጨረስ የአንድ ወር ጊዜ ብቻ ይቀራቸዋል።

አቶ ዳንኤል በቀለ በኢትዮጵያ የሕግ አማካሪና ጠበቃ ሆነው ሠርተዋል፣ በሕብረት ኢንሹራንስ የሕግ ዳይሬክተረ ነበሩ። መንግሥታዊ ባልሆነው ግብረ ሰናይ ድርጅት (Actionaid- Ethiopia ) አክሽን ኤድ ኢትዮጵያ የፖሊሲ ዳይሬክተር ሆነው አገልግለዋል። በምርጫ 97 ከቅንጅት አመራሮች ጋር ታስረው ነበር። ከእስር ከተለቀቁ በኋላ በዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ዲቪዥን ዳይሬክተር ነበሩ።

ምንጮች እንደገለፁት አቶ ዳንኤል በቀለ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽንን በኮሚሽነርነት እዲመሩት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለና በቅርቡ ውሳኔ ላይ እንደሚደረስ ነው። በዚህ መሰረት በነገው ዕለት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚቀርበው ሹመት የብሔራዊ ምራጫ ቦርድ እጩ ሰብሳቢ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ብቻ ነው።

🔹ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሕግ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቀዋል። ከረዳት ዳኛነት እስከ ፌደራል ፍርድ ቤት በዳኛነት አገልግለዋል። በጥብቅና ሞያና በሕግ አማካሪነት ሠርተዋል። በ1992 ዓ.ም ተወልደው ያደጉበትን (ፈረንሳይ ለጋሲዮን) አካባቢ በመወከል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግል ተወዳዳሪ ነበሩ። የቅንጅት ፓርቲ ተቀዳሚ ም/ሊቀመንበር ሆነው ሠርተዋል። በእዚህ ወቅትም ለእስር ተዳርገዋል። ከእስር ከተፈቱ በኋላ አንድነት ፓርቲን በሊቀመንበርነት መርተዋል። በመጨረሻም ለሁለተኛ ጊዜ ታስረዋል። ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ ተጉዛ National Endowment for Democracy (NED) ኔድ በተሰኘ የታወቀ የዴሞክራሲ የምርምር ተቋም ውስጥ ተመራማሪ ፌሎ በመሆን ለአንድ ዓመት በዴሞክራሲ ላይ ምርምር አድርገዋል። በሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ውስጥም (Scholars at Risk) በተሰኘ ፕሮግራም ለአንድ ዓመት ሰልጥነዋል።

በዚሁ በሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ የሕዝብ አስደዳደር (Public Administration) በሁለተኛ ዲግሪ ተመረቀዋል። ምክር ቤቱ ነገ አምባሳደር ሳሚያ ዘካሪያን በወ/ት ብርቱካን ተክቶ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም ያልተሟሉ የምክር ቤቱን የቋሚ ኮሚቴ ሊቀ መናብርት ሹመትን ለማፅደቅ የውሳኔ ሐሳብ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ፂዮን ግርማ(ቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሚኒስትሮች ም/ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው #63ኛ_መደበኛ_ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ #ውሳኔ አሳልፏል፡፡

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
40/60...

ዛሬ የዋለው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 8ኛ ፍ/ብሄር ችሎት የ40/60 እቤት እድለኞች(61ሰዎች) ባቀረቡት የጣልቃ መግባት አቤቱታ ላይ በከሳሽ ወገን ሆነው ጣልቃ እንግባ የሚል አቤቱታ ባቀረቡ ሰዎች አቤቱታ ላይና በ3ኛ ተከሳሽ (የአዲስ አበባ ከተማ የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ) የእግድ ይነሳልኝ (ወይም የኪሳራ ገንዘብ ከሳሾች ያስይዙልኝ) አቤቱታ ተመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።

#ውሳኔ_1. በ98 ሰዎች (መቶ ፐርሰንት የከፈሉ ተመስጋቢዎች) ክስ የ2ኛ ዙር የ40/60 እድለኞች ላይ የተጣለው እግድ እንዲነሳ ተወስኗል። ነገር ግን በ98 ከሳሾች ልክ 98 ቤቶች ብቻ ታግደው እንዲቆዮ ተወስኗል።

#ውሳኔ_2. በ61 (የ2ኛ ዙር የ40/60 እድለኞች) በክሱ ጣልቃ የእንግባ ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ተቀብሏል

#ውሳኔ_3. ሌሎች በከሳሽ ወገን የጣልቃ እንግባ ጥያቄን ውድቅ አድርጓል

#ውሳኔ_4. የከሳሽ ክስ የማሻሻል ጥያቄን ተቀብሏል

Via Housing in Addis Ababa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክሱም ዩኒቨርሲቲ...

ተማሪዎች በከፍተኛ ሁኔታ የዋስትና ጥይቄ አንስተዋል፤ አሁን ባለው ሁኔታ ትምህርት ለመቀጠል እንደማይችሉ አንስተዋል፦

በዩኒቨርሲቲው አመራሮች የቀረቡ የመፍትሄ ሀሳቦች፦

√የቀረውን ጊዜ በፌደራል እና በመከላከያ ሰራዊት አማካኝነት ደህንነታችሁ ተጠብቆ ትምህርታችሁን ጨርሱ

√እዚህ ካሉ አባቶች፣ የሃይማኖት መሪዎች እንዲሁም ከሀገር መከላከያ ሰራዊት አመራሮች ጋር ተወያይተን ወደየመጣችሁበት እንላካችሁ

• ተማሪው ከላይ ባሉት ሁለት ሀሳቦች ላይ ያዋጣኛል በሚለው ሀሳብ ላይ ውይይት አድርጓል።

• የተማሪው ውሳኔ ወደየመጣንበት እንመለስ የሚል ሲሆን አመራሮች ውሳኔ ነገ ጥዋት ይሰጣል ብለው ስብሰባውን ዘግተውት ነበር፤ ተማሪው በበኩሉ ዛሬ ውሳኔ ካልተሰጠን ከአዳራሽ አንወጣም በማለት ውሳኔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። የተቋረጠውም ስብሰባ በተማሪዎች ጥይቄ እንዲቀጥል ሆኗል። የሀይማኖት አባቶች ተማሪውን ቆመው ተመማፅነዋል።

√ተቋርጦ የቀጠለው ስብሰባ አሁንም ቢሆን ለተማሪው #ውሳኔ ሳይሰጥ #ለነገ ተዘዋዉሯል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ውጤትን የተመለከተ መግለጫ!

የ12ኛ ክፍል ውጤትን በተመለከተ በትምህርት ሚኒስትሩ ሚኒስቴር ዶክተር ጥላዬ ጌቴ፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገ/እግዚአብሔር ምክትል ዳይሬክተሮች ዶ/ር ዘሪሁን ዱሬሳ እና አቶ መሳይ ደምሴ፣ እንዲሁም የየክልሎች የትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች የሆኑት ዶክተር ጌታሁን ጋረደው የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ፣ ዶ/ር ቶላ ባሪሶ የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም ዶክተር ይልቃል የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች በተከታታይ #ውጤቱን በተመለከተ በጋራ በተላለፈው #ውሳኔ ላይ መግለጫ ሰጥተዋል።

በዚሁም መሰረት በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና ያጋጠመ ችግር መኖሩን በተለይ በደንብ ጥሰት ዙሪያ #በማረጋገጫ የተያዘባቸው ተማሪዎች ውጤት መሰረዙ እና በደንብ ጥሰቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በየደረጃው ተጠያቂ የሆኑበት ሁኔታን እንዳለ ሆኖ፤ ፈተናዎቹ ከሰጡባቸው ቀናት ሀሙስና አርብ ማለትም በ6 እና 7/10/2011ዓ.ም ከተሰጡት ፈተና ውጤቶች በተለየ ከቅዳሜና እሁድ በኋላ ሰኞ እና ማክሰኞ ማለትም በ10 እና 11 10/2011ዓ.ም በተሰጡት ፈተናዎች በግልጽ የታየ የውጤት ግሽበት መኖሩ በመረጋገጡ የዩንቨርስቲ መግቢያ መቁረጫ ነጥቡ በአራቱ የትምህርት ዓይነቶች ላይ መሰረት ያደረገ እንደሚሆን መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ እነዚህም እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ አፕቲቲዩድና ፊዚክስ ለተፈጥሮ ሳይንስ ሲሆኑ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ አፕቲቲዩድና ጂኦግራፊ ለማህበራዊ ሳይንስ ይሆናሉ፡፡

ይህም ሲሆን ተማሪዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ሊገነዘቡ የሚገባቸው ተማሪዎቹ ያስመዘገቡት ውጤት በመምህርነት ሙያ ለመማር ከመረጡ ተማሪዎች ውጪ ለዩንቨርስቲ መግቢያ ብቻ የሚያገለግልና የተፈጥሮና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ተብለው ዩንቨርስቲ እንደሚገቡና ከአንድ ዓመት የፍሬሽማን ኮርሶች በኋላም በሚያስመዘግቡት ውጤት መሰረት የፈለጉትን የትምህርት ፊልድ መርጠው መማር የሚችሉ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

የተከሰተውን #ግሽበት በተመለከተም የማጣራት ሂደቱን የሚያካሂድ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስቴሩ የሆነ ኮሚቴ መቋቋሙን የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር #ጌታሁን_ጋረደው ያሳወቁ ሲሆን ተጠያቂው አካል አስተማሪና የማያዳግም እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑን አሳውቀዋል፡፡

በመግለጫው ማጠቃለያም የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ዶክተር #ጥላዬ_ጌቴ እንደገለጹት የመቁረጫ ነጥቡን በተመለከተ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ችግር የነበረባቸው አካባቢዎች የተፈተኑ ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ የሚታይላቸው መሆኑንና በጥቂት ቀናት ውስጥ በኤጀንሲው የሚገለጽ መሆኑን እንዲሁም በታየው የውጤት ግሽበት ምክንያት የተያዙት የተማሪዎች ውጤቶች #እንደሚለቀቅ ጨምረው አሳውቀዋል።

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 83ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ #ውሳኔ አሳልፏል!

#PMOEthiopia
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ትምህርት ሚኒስቴር በጦርነት እና ግጭት ውስጥ ሆነው ተፈትነዋል ተብለው የተለዩ እና የ12ኛ ክፍል " የማለፊያ ውጤት ያላመጡ " ተማሪዎች በዚህ ዓመት በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እንደ መደበኛ ተማሪ ሆነው መፈተን እንደሚችሉ አስታወቀ፡፡ ከዩኒቨርስቲዎች ጋር ውይይት በማድረግ ተጨማሪ የቅበላ አቅም እንዲኖር ከስምምነት ላይ መደረሱን እና ተጨማሪ የቅበላ አቅም በፍትሀዊነት በጦርነቱ…
#ውሳኔ

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2013 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስደው የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያላመጡ ተማሪዎችን አስመልክቶ ውሳኔ መተላለፉን አሳውቋል።

ከውሳኔዎቹ አንደኛው ከዚህ በፊት በተላለፈው የመቁረጫ ነጥብ መሰረት ወደ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች መግባት ከቻሉት የክልሉ ተማሪዎች በተጨማሪ 4339 ተማሪዎች በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ቅበላ እንዲያገኙ ተወስኗል ብሏል።

እነዚህ 4339 ተማሪዎች እንዴት እና በምን አግባብ ቅበላ ሊያገኙ እንደቻሉ (የተበላሸ ውጤታቸው ተስተካክሎ ወይስ ሌላ ስለሚለው) ቢሮው ዝርዝር ማብራሪያ አልስጠም።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሌላ ተላልፏል ያለው ውስኔ ፥ በ2013 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ወደ መንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመግቢያ ነጥብ ያላሟሉ የክልሉ #ሁሉም_ዞኖች ተማሪዎች በ2014 ዓ.ም በሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በመደበኛ ተማሪነት (as regular students) መፈተን እንደሚችሉ ነው።

ቢሮው ፤ ትምህርት ሚኒስቴር የውጤት መቁረጫ ነጥብ ተወስኖ እና ያለፉት ተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምርጫ ፎርም የሚሞላበት የመጨረሻው ቀን ከተወሰነ በኋላ ከአማራ ክልል በተነሳ ቅሬታ መነሻነት ቅሬታውን አዳምጦ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ጊዜው እንዲራዘም ማድረጉ ትልቅ መደማመጥ የተስተዋለበት ነበር ሲል ገልጿል።

" ይህም ለቀጣይ በመደማመጥ ላይ የተመሰረተ የሀገር ግንባታ ጉዟችን አንድ ማሳያ ነው ብለን እናስባለን " ሲል አክሏል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ከተፈጠረው ችግር አኳያ ውሳኔው ያላረካቸው አካላት ሊኖሩ እንደሚችሉ ይገመታል ያለ ሲሆን የክልሉ ተማሪዎች በመደበኛ ተማሪነት የመፈተን እድሉን በድጋሜ ማግኘታቸውን እንደ ትልቅ አጋጣሚ አድርገው ለውጤታማነት እንዲጠቀሙበት አሳስቧል።

@tikvahethiopia