TIKVAH-ETHIOPIA
1.39M subscribers
54.7K photos
1.36K videos
198 files
3.63K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አብን ጠርቶት የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ሰርዟል!

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ /አብን/ የአመራሮቹን እና የአባላቱን እስር አስመልክቶ የካቲት 22 ቀን 2012 ዓ/ም በተመረጡ የአገሪቱ ከተሞች ለማካሄድ ጠርቶት የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ መሰረዙን አስታውቋል። ሰልፉ "የመንግስት በኩል የታየውን በጎ ጅምርና ሌሎች ተደራራቢ የፖለቲካ ተግባራትን ከግምት ውስጥ በማስገባት እንደማይካሄድ" ስለመወሰኑ ነው ያስታወቀው።

https://telegra.ph/NAMA-02-28

#AlAin
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GERD

የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ድርድር ዙሪያ መንግስት ግልጽ፣ በቂ እና ወቅታዊ መረጃ ለህዝብ እንዲሰጥ እና በፕሮጀክቱ ዙሪያ በሚደረግ ድርድር የሀገራችንን ብሄራዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲሰራ አሳስቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦቻችን የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ካለባቸው ሀገራት ከመጣችሁና ትኩሳት ፣ ሳልና የመተንፈስ ችግር ካጋጠማችሁ ላስቸኳይ የህክምና እርዳታ 8335 እንድትደውሉ የጤና ሚኒስቴር አደራ ብሏችኃል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ያለባቸው ሀገራት፦

China
South Korea
Cruise ship (Diamond Princess)
Italy
Iran
Japan
Singapore
Hong Kong
United States
Germany
Kuwait
Thailand
France
Bahrain
Taiwan
Malaysia
Spain
Australia
United Kingdom
Vietnam
United Arab Emirates
Canada
Macau
Iraq
Russia
Oman
Switzerland
Austria
Croatia
Greece
India
Philippines
Finland
Israel
Lebanon
Pakistan
Sweden
Afghanistan
Algeria
Belarus
Belgium
Brazil
Cambodia
Denmark
Egypt
Estonia
Georgia
Lithuania
Nepal
Netherlands
New Zealand
Nigeria
North Macedonia
Norway
Romania
Sri Lanka

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የዓለም ደረጃ!

በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች [UAE] የሚገኘው የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ ማእከል ሁለት ሺህ ዩኒቨርሲቲዎችን አወዳድሮ ባወጣው ደረጃ መሠረት አምስት የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ተካትተዋል።

ማእከሉ ደረጃውን ለማውጣት ዩኒቨርሲቲዎቹ በየአገራቸው ያላቸውን ደረጃ፣ የሚሰጡትን የትምህርት ጥራት፣ ራሳቸው ያስተማሯቸውን ተማሪዎች የመቅጠር ምጣኔ፣ የፋኩሊቲያቸው ጥራት እንዲሁም በጥናት እና ምርምር ዘርፍ ያላቸው ብቃት በመስፈርትነት ተጠቅሟል።

በዚሁ መሠረት ከሁለት ሺህ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል፦

አዲስ አበባ (1 ሺህ 040ኛ) ፣ ጎንደር (1 ሺህ 547ኛ) ፣ መቐለ (1 ሺህ 588ኛ) ፣ ጅማ (1 ሺህ 786ኛ) እና ባሕር ዳር (1 ሺህ 780ኛ) ደረጃ በመያዝ የተካተቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሆነዋል።

በዓለም አቀፍ ደረጃ የአሜሪካኖቹ ሀርቫርድ ፣ ማሳቹስቴትስ ኢንስቲትዩት ኦፍ ቴክኖሎጂ እና ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ከአንደኛ እስከ 3ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ከ1 እስከ 10ኛ ደረጃ ካሉ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ከእንግሊዞቹ የኦክስፎርድ (4ኛ) እና የካምፕሪጅ (5ኛ) ዩኒቨርሲዎች በስተቀር በሙሉ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው፡፡

[የዓለም ዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ ማእከል፣EBC]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

መቼ ነው ማስክ ማድረግ ያለብኝ ?

የኮሮና ስርጭት ካለባቸው የተለያዩ ሀገራት በተለይም ደግሞ ከቻይና የሚመጡ መንገደኞች ቢያንስ ለ14 ቀናት የፊት ማስክ በማድረግ እና አስፈላጊውን የጥንቃቄ እርምጃ እንዲወስዱ ይመከራል። እንዲሁም ከነዚህ ሰዎች ጋር ቀጥተኛ የሆነ ንክኪ ከማድረግ በመቆጠብ እንዲሁም በኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ወይም በጤና ሚኒስቴር ህብረተሰቡ እንዲጠቀም ሲታወጅ!

#EPHI
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ውድ ቤተሰቦቻችን ራሳችሁን ከኮሮና ቫይረስ ለመጠበቅ ማድረግ የሚገባችሁን ጥንቃቄዎች ከኤፍ ቢ ሲ ድረገፅ፦

- በሕይዎት ካሉም ሆነ ከሞቱ የቤትና የዱር እንስሳት ጋር ንክኪ አለማድረግ

- ያልበሰሉ የእንስሳት ተዋፅኦ የሆኑ ምግቦችን ከመመገብ መቆጠብ

- የትኩሳትና የሳል ምልክት ከሚያሳዩ ሰዎች ጋር ንክኪ አለማድረግ፣

- እጅን በሳሙናና ውሃ መታጠብ በተለይ ደግሞ ከታመሙ ሰዎች ወይም ከአካባቢያቸው ጋር ንክኪ ከፈጠሩ፣

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከማጂ ወረዳ ቲክቫህ ቤተሰቦች፦

በምዕራብ ኦሞ ዞን ውስጥ የማጂ ወረዳ ባለሥልጣን በመታሠሩ ባለሥልጣኑ መታሠሩ አግባብ አይደለም በማለት የቱም ከተማና የአካባቢው ህዝብ ተቃውሞ ማሰማቱን የቲክቫህ ቤተሰቦች አሳውቀዋል።

ከ19/6/2012 እስከ 20/6/2012 ማለዳ ድረስ በርካታ የተኩስ ድምፅ ነበር የሚሉት ቤተሰቦቻችን አርፍዶም በከተማዋ የጎማ ቃጠሎም ታይቷል፤ 2 ሰዎችም በተተኮሰ ጥይት ሞቷል ብለውናል።

ቲክቫህ አትዮጵያ ከማጂ ቤተሰቦቹ የሚመጡ መልዕክቶችን እንዲሁም ስለከተማው ሁኔታ ተጨማሪ መረጃ አሰባስቦ ያጋራችኃል። #TikvahFamily #MajiWoreda

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ProsperityParty

ብልጽግና ፓርቲ [Prospertity Party] በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በቅርቡ እንደሚከፍት የፓርቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙት ኃላፊ ገለጹ፡፡

የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወሉ አብዲ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ብልጽግና አገር አቀፍ ፓርቲ በመሆኑ ከትግራይ ክልል ጋር በሚኖረው ሕገ መንግሥታዊ ግንኙነት መሠረት አደረጃጀቱን በማስፋት በቅርቡ በክልሉ በሁሉም ዞኖች፣ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ጽሕፈት ቤቶችን ይከፍታል፡፡

ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል ነባራዊ ሁኔታ እስካሁን ትርጉም ባለው መልኩ እንቅስቃሴ እንዳልተደረገ የገለጹት አቶ አወሉ፤ ነገር ግን አሁን በአዲስ መልክ የትግራይ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ተቋቁሞ ሥራውን እየሰራ ስለሆነ በቅርብ ጊዜ በክልል፣ በዞኖች፣ በወረዳና በቀበሌ ደረጃ እንቅስቃሴ ይደረጋል ብለዋል።

ምንጭ፦ አዲስ ዘመን ጋዜጣ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#MinistryOfCultureAndTourism

በቅርቡ ከኔዘርላንድስ የተመለሰው የ18ኛው ክፍለ ዘመን ዘውድ በነገው እለት ለትግራይ ክልል ጨለቆት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን ተመላሽ ይደረጋል። በዕለቱ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የመገናኛ ብዙሃን በተገኙበት በብሔራዊ ሙዚየም ቅጥር ግቢ የርክክብ ሥነ ሥርዓትና ሽኝት እንደሚካሄድ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል።

ለተጨማሪ መረጃ ፦ 0911360902
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ከእስር ተፈተዋል!

የኢትዮጵያ መንግስት ክሳቸው አንዲቋረጥ ካደረገላቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋ በዛሬው ዕለት ከእስር ተፈተው ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸው ተሰምቷል።

PHOTO : JANO BAND
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለሚመለከተው አካል፦

ይህ አዲስ አበባ ከተማ ወሎ ሰፈር አደባባዩ ላይ ያለዉ የድልድይ አካል ቢወድቅ ከስር ባሉ በተላላፊዎች ላይ ጉዳት ስለሚያስከትል ይታሰብበት!

#DrivinginAddis #EliasMeseret

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ProsperityParty ብልጽግና ፓርቲ [Prospertity Party] በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በቅርቡ እንደሚከፍት የፓርቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙት ኃላፊ ገለጹ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወሉ አብዲ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ብልጽግና አገር አቀፍ ፓርቲ በመሆኑ ከትግራይ ክልል ጋር በሚኖረው ሕገ መንግሥታዊ…
#TPLF #ProsperityParty

ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቢሮ እንደሚከፍት ያስታወቀ ቢሆንም የክልሉ መንግስት ግን የሚያዉቀዉ ነገር እንደሌለ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸዉ ረዳ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የተናገሩት፦

ብልጽግና ፓርቲ ለትግራይ ክልል የተሾሙ ግለሰቦች እንዳሉ ሰምቻለሁ እነማን እንደተሾሙ ግን ወደ ፊት የሚሆነዉን የምናይ ይሆናል፡

ብልጽግና በትግራይ ክልል ብዙ ደጋፊ አለው ብዬ አላምንም፤ ማንኛዉም ፓርቲ ህጋዊ እስከሆነ ድረስ ግን በትግራይ ክልል የመንቀሳቀስ መብት አለዉ።

#EthioFM #አባቱመረቀ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#attention አሁንም በአንዳድን የማንቡክ አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ እንደሚሰማ እየተገለፀልን ከቤተሰቦቻችን እየተገለፅልን ነው። በአካባቢው የተፈጠረውንና እየተፈጠረው ያለውን ዝርዝር ጉዳይ ከቤተሰቦቻችን ጠይቀን፤ ተጨማሪ መረጃዎችን አካተን እንድታነቡት እናደርጋለን። ለሁሉም ግን የሚመለከታችሁ አካላት [የፀጥታ ኃይሉ] የአካባቢውን ደህንነት እንድታስጠብቁ የቲክቫህ ማንቡክ ቤተሰቦች አሳስበዋል።…
#UPDATE

በዳንጉር ወረዳ ተስተውሎ የነበረው የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር መዋሉን የመከተል ዞን አስታወቀ፡፡ የፀጥታ ችግሩ 3 ሰዎችን ለህልፈት፣ 7ቶችን ደግሞ ለከባድና ቀላል የመቁሰል አደጋ ሰለባ ከማድረግ ባለፈ የተወሰኑ ቤቶች እንዲቃጠሉ ምክንያት መሆኑንም ተገልጿል።

በፀጥታ ኃይሎች ፣ በሀገር ሽማግሌዎች እና በሐይማኖት አባቶች የተቀናጀ ስራ የተስተዋለው የፀጥታ ችግር በቁጥጥር ስር መዋሉንና ህብረተሰቡን የማረጋጋት ስራ እየተሰራ ነው ተብሏል። በአካባቢው የህግ የበላይነትን ለማስከበር እየተሰራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ችግሩ ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይዘመትም በተቀናጀ መልኩ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን፤ ህብረተሰቡ ያቆየውን አብሮ የመኖር እሴት አክብሮ ለዘላቂ ሰላም መስፈን የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል፡፡

[የክልሉ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከማጂ ወረዳ ቲክቫህ ቤተሰቦች፦ በምዕራብ ኦሞ ዞን ውስጥ የማጂ ወረዳ ባለሥልጣን በመታሠሩ ባለሥልጣኑ መታሠሩ አግባብ አይደለም በማለት የቱም ከተማና የአካባቢው ህዝብ ተቃውሞ ማሰማቱን የቲክቫህ ቤተሰቦች አሳውቀዋል። ከ19/6/2012 እስከ 20/6/2012 ማለዳ ድረስ በርካታ የተኩስ ድምፅ ነበር የሚሉት ቤተሰቦቻችን አርፍዶም በከተማዋ የጎማ ቃጠሎም ታይቷል፤ 2 ሰዎችም በተተኮሰ ጥይት ሞቷል…
#UPDATE

በማጂ ወረዳ ተቃውሞ የሰዎች ህይወት አልፏል!

በደቡብ ክልል ምዕራብ ኦሞ ዞን ማጂ ወረዳ ቱም ከተማ በዛሬው ዕለት በተደረገ ተቃውሞ ላይ የጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት ስድስት ሰዎች መገደላቸውን የሕክምና ተቋም ኃላፊ ለጀርመን ድምፅ ተናገሩ።

የዞኑ ባለሥልጣናት እና የዐይን እማኞችም ጸጥታ ኃይሎች በተኮሱት ጥይት ከተገደሉት በተጨማሪ ሌሎች ከአስር በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን አረጋግጠዋል።

ሰልፉ የተደረገዉ አዲስ በተዋቀረው በምዕራብ ኦሞ ዞን የምትገኘው የማጂ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና የጸጥታ ቢሮ ኃላፊ መታሰራቸውን በመቃወም ነበር።

«አስራ አንድ ሰው [በጥይት] ተመቷል። ሶስቱ ሴቶች ናቸው። ትልልቅ ሰዎች እና ሕፃናትም አሉበት» የሚሉት የዐይን እማኙ «ሰልፍ ሲደረግ መንገድ ይዘጋል። መንገድ ሲዘጋ መከላከያ እና ልዩ ኃይል መጣ። ከዚያ በአካባቢው በተሰበሰበው ሕዝብ ላይ ምንም ነገር ሳያማክር ተኩስ ጀመረ» ሲሉ መነሾውን አብራርተዋል።

More : https://telegra.ph/Maji-02-28

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የማጂ ወረዳ ጤና ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ከበደ አኩ፦

"ቱም በተባለችው ከተማ በተደረገው ሰልፍ ስድስት ሰዎች በጸጥታ አስከባሪዎች ተገድለዋል። ዛሬ ጠዋት በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የነበሩ አራት ሰዎች በልዩ ኃይል እና በመከላከያ ሠራዊት በተተኮሰ ጥይት ተመተው እኛ ጋ ተኝተዋል። የሞቱት ሬሳቸው ሳይነሳ እዚያው ነው ያለው። የሞቱት ወደ ስድስት የሚሆኑ ሰዎች ናቸው። በአራት ጥይት የቆሰሉ አንድ ሰው ለተጨማሪ ሕክምና ወደ ማጂ ተልከዋል።"

#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከማጂ ወረዳ ቲክቫህ ቤተሰቦች፦ በምዕራብ ኦሞ ዞን ውስጥ የማጂ ወረዳ ባለሥልጣን በመታሠሩ ባለሥልጣኑ መታሠሩ አግባብ አይደለም በማለት የቱም ከተማና የአካባቢው ህዝብ ተቃውሞ ማሰማቱን የቲክቫህ ቤተሰቦች አሳውቀዋል። ከ19/6/2012 እስከ 20/6/2012 ማለዳ ድረስ በርካታ የተኩስ ድምፅ ነበር የሚሉት ቤተሰቦቻችን አርፍዶም በከተማዋ የጎማ ቃጠሎም ታይቷል፤ 2 ሰዎችም በተተኮሰ ጥይት ሞቷል…
የምዕራብ ኦሞ ዞን የሚሊሺያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰለሞን መኮንን፦

"በቱም ከተማ የተገደሉት ሰዎች ሁለት (2) ብቻ ናቸው። ችግሮችን ለማረጋጋት ዛሬ ቱም ማዕከል ላይ ልዩ ኃይል እና መከላከያ ሰራዊት ወደ ከተማው ከገባ በኋላ በተተኮሰው ጥይት አንድ ሴት፤ አንድ ወንድ ሞተዋል የሚል መረጃ አለን። አስር ወንዶች፤ ሁለት ሴቶች ቆስለዋል የሚል መረጃ ነው በስልክ እየደረሰን ያለው"

#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቻይና ውሃን የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰቦች፦ እኛ ጥያቄያችን ገንዘብ ሳይሆን ወደሀገራችን መመለስ ነው፤ እኛ ገንዘብ አንፈልግም መንግስት ዜጎቻችን ናችሁ የሚለን ከሆነ በአስቸኳይ ወደሀገራችን ይመልሰን ሲሉ እየጠየቁ ነው። ባለፉት ሳምንታት በተደጋጋሚ ጥያቄያችንን እያቀረብን ቢሆንም መፍትሄ አልተገኘልንም ብለዋል። @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

በዉሃን የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት 'ወደ አገራችን መልሱን' የሚለውን የተማፅኖ ደብዳቤ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ለጤና ጥበቃ ሚኒስቴር መላካቸውን ጠቁመዋል።

የቻይና መንግሥት በወረርሽኙ ምክንያት መውጣትም ሆነ መግባት ከከለከለባት የዉሃን ከተማ መውጣት የሚችሉበትን ሁኔታ ቢያመቻች አብዛኞቹ ተማሪዎች ወጪያቸውን ራሳቸው ሸፍነው ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንደሚፈልጉ ኅብረቱ ለተማሪዎቹ አሰራጭቶት በነበረው መጠይቅ ለማረጋገጥ ችሏል።

ምንም እንኳ የሀገሪቱ [የቻይና መንግሥት] አስፈላጊ ነገሮችን እያቀረበላቸው ቢሆንም ተማሪዎች ከባድ የሥነ ልቦና ጫና ላይ በመሆናቸው የግድ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ደብዳቤ ለመፃፍ መገደዳቸውን ተናግረዋል።

#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

የኮሮና ቫይረስ [#COVID19] መተላለፊያ መንገዶች እንድታውቋቸው፦

የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የመተንፈሻ አካል የሚያጠቃ በሽታ ነው። ዋናው የመተላለፊያ መንገድ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች በሚያስሉበት እና በሚያስነጥሱበት ወቅት ትንፋሽ ጋር በሚወጡ ፈሳሾች ጋር በሚደረግ ንክኪ ነው።

እንዴት መከላከል ይቻላል?

- በሚያስነጥሱበት ወይም በሚያስሉበት ወቅት አፍና አፍንጫዎን በክንድ ወይም በሶፍት መሸፈን

- አይን፣ አፍንጫ እና አፍን ባልታጠበ እጅ አለመንካት

- በውሃ እና በሳሙና መታጠብ፣ አልኮል ነክ በሆኑ የንፅህና መጠበቂያዎች እጅዎን በአግባቡ ማሸት

- የተጠቀሙበትን ሶፍት በፍጥነት በጥንቃቄ መክደኛ ወዳለው የቆሻሻ ማጠራቀሚያ መጣል

#ጤናሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19 #ETHIOPIA

ከጤና ሚንስትር ዴኤታ ዶ/ር ሊያ ታደሰ የተገኘ መረጃ፦

ዛሬ በለይቶ ማቆያ ማእከል ውስጥ አንድ የተጠረጠረ ቻይናዊ እንደሚገኝ ተሰምቷል። ግለሰቡ እ.ኤ.አ. ፌብሩዋሪ 22 ከቤጂንግ የመጣ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በወቅቱ ምንም ምልክቶች እንዳልታዩበት፤ በቤት ውስጥ ተገልሎ የቆየ ነበር፡፡ ዛሬ ትኩሳት ፣ ሳል እና የጉሮሮ መቁሰል ገጥሞት ክትትል እየተደረገለት ይገኛል፡፡ የግለሰቡ ናሙና ውጤት ዛሬ ማታ ይፋ ይደረጋል።

የበሽታው ስርጭት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 20 የተጠረጠሩ ኬዞች የነበሩ ሲሆን ሁሉም ከቫይረሱ ነፃ ናቸው። በአሁኑ ወቅት በአገራችን በኮሮና ቫይረስ መያዙ የተረጋገጠ ግለሰብ የለም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia